Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ
👉በተጽዕኖዎች ውስጥ ዕድገት ማስመዝገቡ የማክሮ
ኢኮኖሚው ሥራ ውጤት ነው
👉ለተመዘገበው ዕድገት ግብርና ዋነኛው ሞተር ነው
👉የነፍስ ወከፍ ገቢው በተለያየ መንገድ ዜጎች ጋር
ይደርሳል
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት መንግሥት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ያከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ውጤት ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስቴርና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታወቁ።

የገንዘብ ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ እና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍፁም አሰፋ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ዶክተር ፍፁም አሰፋ፤ በሰሜኑ ጦርነት፣ በኮቪድ ወረርሽኝ በድርቅ እንዲሁም ምዕራባውያን በፈጠሩት ጫና የፋይናንስ እጥረት ኢኮኖሚው በተለያዩ ፈተናዎች ማለፉን ገልጸዋል።

በተለያዩ ተጽዕኖዎች አልፋ ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የስድስት ነጥብ አራት በመቶ ዕድገት በግብርናው፣ በአገልግሎት ዘርፉና በተለያዩ ዘርፎች ላይ በተከናወነው የማክሮ ኢኮኖሚ ሥራ ውጤት የመጣ መሆኑን ችግሮች ባሉበት ወቅት ከማዳበሪያ አቅርቦት እስከ ሜካናይዜሽን አቅርቦት ሰፊ ስራ ተከናውኗል፤ ዝናብን እና ወቅት ጠብቆ ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ አርሶ አደሩ እንዲያመርት ትልቅ ጥረት ተደርጓል። መንግሥት 50 ሺህ የውሃ ፓምፖችን በማከፋፈል ምርታማነትን ለማሳደግ ያደረገው ጥረት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=86068
የማክሮ ኢኮኖሚ ቡድን አባል የሆኑት የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አስፋ ይናገራሉ ‼️

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 126 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፤

👉 የኢትዮጵያውያን የነፍስ ወከፍ ገቢ አንድ ሺህ 212 ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል፤

👉 የነፍስ ወከፍ ገቢያችን አደገ ሲባል ግን እኩል በእያንዳንዳችን ኪስ የሚገባ አይደለም፤

👉 እንደየስራችንና ልፋታችን መጠን ባመረትነውና በተሳተፍንበት ልክ ይደርሰናል፤

👉 ብዙ የሰሩና ያመረቱ ከፍተኛ ገቢ ያገኛሉ፤

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት መንግሥት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ያከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ውጤት ነው፤

👉 በሰሜኑ ጦርነት፣ በኮቪድ ወረርሽኝ በድርቅ እንዲሁም ምዕራባውያን በፈጠሩት ጫና የፋይናንስ እጥረት ኢኮኖሚው በተለያዩ ፈተናዎች አልፏል፤

👉 በተለያዩ ተጽዕኖዎች አልፋ ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የስድስት ነጥብ አራት በመቶ ዕድገት በግብርናው፣ በአገልግሎት ዘርፉና በተለያዩ ዘርፎች ላይ በተከናወነው የማክሮ ኢኮኖሚ ሥራ ውጤት የመጣ ነው፤

👉 ችግሮች ባሉበት ወቅት ከማዳበሪያ አቅርቦት እስከ ሜካናይዜሽን አቅርቦት ሰፊ ስራ ተከናውኗል፤

👉 ዝናብን እና ወቅትን ጠብቆ ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ አርሶ አደሩ እንዲያመርት ትልቅ ጥረት ተደርጓል፤

👉 መንግሥት 50 ሺህ የውሃ ፓምፖችን በማከፋፈል ምርታማነትን ለማሳደግ ያደረገው ጥረት ለውጤቱ መመዝገብ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤

👉 በግብርና ዘርፍ በምግብ ራስን ለመቻል በተደረገ ጥረት ምርታማነት በማሳደግ የስንዴ ግዥ የውጭ ምንዛሬን ያስቀረ ስራ ተከናውኗል፤

👉 ከግብርናው ባለፈ የአገልግሎት ዘርፉም የኢኮኖሚ ዕድገቱ ወሳኝ ነበር፤

👉 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገኘው ገቢ ኢኮኖሚያችን በችግር ውስጥም ሆኖውጤታማ እንዲሆን ያገዘ ነው፤

👉 የማክሮ ኢኮኖሚው ውሳኔዎች ኢኮኖሚውን የሚገዳደሩ የዋጋ ግሽበትና ዘርፈ ብዙ ችግሮችን መቋቋም አስችሏል፤

👉 አንድ ኢኮኖሚ የዋጋ ግሽበቱን እስከ 40 በመቶ ከገታ ዕድገቱን ማቆየት ይችላል፤

👉 የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያን ያህል ስላልደረሰ ዕድገቱ ማስቀጠል እንችላለን፤

👉 አካታችነት ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ስራ የስራ ዕድል ፈጠራ ኢንቨስትመንትና ልማትን አስተሳስሮ መሄድ ተችሏል፤

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 126 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፤

👉 የኢትዮጵያውያን የነፍስ ወከፍ ገቢ አንድ ሺህ 212 ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል፤

👉 የነፍስ ወከፍ ገቢያችን አደገ ሲባል ግን ያን እኩል በእያንዳንዳችን ኪስ የሚገባ አይደለም፤

👉 እንደየስራችንና ልፋታችን መጠን ባመረትነውና በተሳተፍንበት ልክ ይደርሰናል፤

👉 ብዙ የሰሩና ያመረቱ ከፍተኛ ገቢ ያገኛሉ፤

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ‼️

https://youtu.be/RRUFwSUMDaU
የማክሮ ኢኮኖሚ ቡድን አባልና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አስፋ ይናገራሉ‼️

👉 ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እንዳሉት፣ ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ እንደሚባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለፈተናዎች የማይበገር መሆኑን ማሳየት ችሏል፤

👉 በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት በአማካኝ 3 በመቶ ነው ያደጉት፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ግን 6.4 ዕድገት አስመዝግቧል፤

👉 በ10 ዓመቱ ዕቅድ ነገሮች ሁሉ ጥሩ ቢሆኑ ተብሎ የታቀደው የዕድገት ምጣኔ ጋር ሲወዳዳርና ሁሉም ነገር ሰላም ቢሆን ኖሮ አሁን የተመዘገበውን የ6.4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት በጥሩ አልነበረም የምንገመግመው፤

👉 ጦርነት፣ በኮቪድ ወረርሽኝ በድርቅ እንዲሁም ምዕራባውያን በፈጠሩት ጫና የፋይናንስ እጥረት ኢኮኖሚው በተለያዩ ፈተናዎች አልፏል፤

👉 ህዝባችን በጣም ጽኑ ነው፣ ግን ደግሞ ከጽኑ ህዝብ ውስጥ የወጣ አመራር በመሆኑ በሳል አመራር ሠጥቷል፤

👉 አንድ ኢኮኖሚ የዋጋ ግሽበቱን እስከ 40 በመቶ ከገታ ዕድገቱን ማስቀጠል ይችላል፤

👉 የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ደግሞ 40 በመቶ አልደረሰም፤

👉 በምሥራቅ አፍሪካ ግዙፉ ኢኮኖሚ እአአ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የኬኒያ ኢኮኖሚ ነበር፤

👉 እአአ ከ2021 ጀምሮ ግን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በምሥራቅ አፍሪካ ግዙፉ ኢኮኖሚ ሆኖ ደረጃውን ተረክቧል፤

👉 ኢኮኖሚያችንን እአአ ከ2021-2022 ባለው ጊዜም 126 ቢሊዮን ዶላር በማድረስ ደረጃውን ማስጠበቅ ችለናል፤

👉 ከሰሃራ በታች ካሉት አገራት መካከል ደግሞ ከናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ ቀጥላ ሶስተኛው ትልቅ ኢኮኖሚ ሆኗል፤

👉 ይሄ ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን የሠራነው ስራ ውጤት ነው፤

👉 ለኢኮኖሚ እድገቱ በተለይ ለግብርናው ዘርፍ ከሜካናይዜሽን እና ፓሊሲ ደረስ የዘለቀው ድጋፍ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል፤

👉 እስካሁን ባለን መረጃ በፌዴራልና በክልል መንግሥታት ብችል ከ50 ሺህ በላይ የውሃ መሳቢያ ፓምፖች አርሶ አደሩ ጋር እንዲደርስ ተደርጓል፤

👉 ሳይታረስ ያድር የነበረን መሬት ወድ እርሻ በማስገባት ትልቅ ሥራ ተሠርቷል፤

👉 በ2014 ዓ.ም 25 ሚሊዮን የሚጠጋ ስንዴ ማምረት ተችሏል፤
ሙሉውን ለመመልከት ከሥር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://youtu.be/RRUFwSUMDaU
የሕክምና ቁሳቁሶች ሽሬ መድረሳቸውን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ገለፀ
****
(ኢ.ፕ.ድ)

ለትግራይ ክልል በአየር እና በየብስ ትራንሥፓርት የተጓጓዙ
አስቸኳይ የህክምና ቁሳቁሶች ሽሬ መድረሳቸውን ዓለም አቀፉ የቀይ መሥቀል ኮሚቴ ዛሬ አስታውቋል።

ሽሬ የገብልው አስቸኳይ የሕክምና ቁሳቁስም 20 ቶን መሆኑን ገልጿል።

አስቸኳይ የሕክምና ቁሳቁሱ በክልሉ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ላሉ ዜጎች የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚውሉ ኮሚቴው በማህበራዊ ገፁ አስታውቋል።
አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የአሜሪካ ኮንግረስ አባሉ ኢትዮጵያ ወደ አጎዋ እንድትመለስ ላቀረቡት ጥያቄ ምስጋና አቀረቡ
****
(ኢ ፕ ድ)

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ለአሜሪካ የኮንግረስ አባል ዶን ቤየር ኢትዮጵያ ወደ አጎዋ ተጠቃሚነት እንድትመለስ ለአገራቸው መንግስት ላቀረቡት ጥያቄ ምስጋና አቀረቡ።

የአሜሪካ ኮንግረስ አባል የሆኑት ዶን ቤየር ለአሜሪካ የንግድ ተወካይ አምባሳደር ካትሪን ታይ ባጸፉት ደብዳቤ ኢትዮጵያ ወደ አጎዋ ተጠቃሚነት እንድትመለስ ለአገራቸው መንግስት ጥያቄ አቅርበዋል።

ዶን ቤየር በዚሁ ደብዳቤያቸው የኢትዮጵያ መንግስት ከሕወሓት ጋር የተፈራረመውን ስምምነት ተፈጻሚ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ሴናተሩ በደብዳቤያቸው በስምምነቱ መሠረት መንግስት ሰብአዊ እርዳታን ባልተገደበ መልኩ ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ የአሜሪካ መንግስት ኢትዮጵያን ወደ አጎዋ የመመለስን ጉዳይ በድጋሜ ሊመለከተው ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአጎዋ ተጠቃሚ በነበረችበት ወቅት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከፍተኛ እድገት እንዲያሳይ፣ በ10 ሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረና የሁለቱን አገራት የንግድ አጋርነት ለማሳደግ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ተጠቃሚነቷን ስታጣ በአጎዋ ጥላ ስር ምርታቸውን ወደ አሜሪካ ይልኩ የነበሩ ኩባንያዎች የማስፋፋፊያ እቅዳቸውን መተዋቸውንና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን መቀነሳቸውን ነው የኮንግረስ አባሉ ለአምባሳደር ካትሪን በጻፉት ደብዳቤ የገለጹት።

ኢትዮጵያን ከአጎዋ የማስወጣት ውሳኔ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ላይ መቀዛቀዝ እንዲታይ ማድረጉንም አመልክተዋል።

አሜሪካ በኢትዮጵያ የአጎዋ ተጠቃሚነት በድጋሚ መመለስ ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይት እንዲያደርግ ዶን ቤየር ለአምባሳደር ካትሪን ጥሪ አቅርበዋል።

በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር የተፈረመው የሰላም ስምምነት ተፈጻሚነት ኢትዮጵያን በፍጥነት ወደ አጎዋ ተጠቃሚነት ይመልሳታል ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል።

ይህንን ኢትዮጵያ ወደ አጎዋ ተጠቃሚነት እንድትመለስ ለአገራቸው መንግስት ያቀረቡትን ጥያቄ አሰመልክቶ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ሴናተሩን አመስግነዋል።
የ12 አመቱን የኳታር ታላቅ አለም አቀፍ ድግስ በጨረፍታ‼️
*****
(ኢ.ፕ.ድ)

ሊጀመር ሰአታት የቀሩት 22ኛው የአለም ዋንጫ ብዙ ተብሎለታል። ብዙ ቁም ነገሮች በርካታ ቀልዶችም በዚሁ የእግር ኳስ ድግስ ዙሪያ ተሰምተዋል ተነበዋልም።

ኳታር በቆዳ ስፋት ትንሿ የአለማችን አገር በመሆኗ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ብዙዎችን ፈገግ ያስባለች አንድ ቧልት እንዲህ ትላለች...

"በጨዋታ ወቅት ተጫዋቾች የማእዘን ምት (ኮርና) ለመምታት ሲንደረደሩ ባህሬን ደርሰው ይመለሳሉ"

ቀልዷ ለቀጣይ 28ቀናት የአለም ዋንጫ ተከታታይ ዘገባችን ቅምሻ ትሁነንና ትንሻ አገር ስላሰናዳችው ታላቅ አለም አቀፍ ድግስ አንዳንድ እውነታዎች ከብዙ በጥቂቱ እናካፍላችሁ።

ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ኳታርን ለዓለም ዋንጫ አዘጋጅነት የመረጣት ከ12 ዓመታት በፊት ነበር። ይህን ውሳኔ መላው ዓለም በፀጋ አልተቀበለውም። በተለያዩ መንገዶች የኳታርን መስተንግዶ የሚያጣጥሉና የሚያወግዙ ትችቶች ሲሰራጩ ቆይተዋል።

የመጀመርያው ንትርከ የፊፋ አስተዳደርና አባል አገራቱ አዘጋጅነቱን ለኳታር ለመስጠት ሲወስኑ በሙስና ተደልለዋል የሚለው ነው።

ኳታር ለአዘጋጅነት በተካሄደው ምርጫ የድጋፍ ድምፆችን ለማግኘት መደለያ ክፍያዎች እንደነበሩ ያወሱ ዘገባዎች ነበሩ። ሁሉም አሉባልታዎች በትክክለኛ መረጃዎች ዛሬም ድረስ አልተረጋገጡም እንጂ ።

የኳታር ንጉሳዊ መንግስት ለአዘጋጅነት በተካሄደው ምርጫ የድጋፍ ድምፆችን ለማግኘት እስከ 6 ሚሊዮን ዶላር በተለይ ለአፍሪካ አገራት ፌደሬሽኖች ማከፋፈሉን ያወሱ ዘገባዎች ነበሩ። ይሁንና ሁሉም አሉባልታዎች በትክክለኛ መረጃዎች ዛሬም ድረስ አልተረጋገጡም።

አንዳንድ የኤስያ አገራትና በተለይ ደግሞ አሜሪካ የዓለም ዋንጫውን ለማዘጋጀት ከፍተኛ ፍላጎት ስለነበራቸው መሰል ዘገባዎች ተሰራጭተዋል። ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በ2010 እኤአ ላይ ጠቅላላ ጉባኤውን ሲያካሂድ በ2018 እኤአ ላይ ራሽያ 21ኛውን የዓለም ዋንጫ እንድታስተናግድ ከመረጠ በኋላ በ2022 እኤአ ላይ ደግሞ ኳታር 22ኛውን ዓለም ዋንጫ እንድታዘጋጅ ወስኗል።

በተለይ ለ22ኛው የዓለም ዋንጫ አሜሪካ፤ አውስትራሊያ፤ ጃፓንና ደቡብ ኮርያ ለመስተንግዶው ፉክክር አድርገው አልተሳካላቸውም።

ፊፋና የዓለም ዋንጫው አዘጋጅ ኳታር በውድድሩ ታሪክ ዘላቂ የስፖርት ልማቶች በመገንባት፤ ከካርቦን ልቀት የነፃ መስተንግዶ በማካሄድ፤ በዘመናዊ ዝግጅት የተሟላ እንደሚሆን እምነት ማሳደራቸው የሙስናውን ወሬ አደብዝዞታል።

በሌላ በኩል የዓለም ዋንጫው የሚካሄድበት ወቅት ከተለመደው መርሃ ግብር እንዲቀየር መደረጉንም ያማረሩ አልጠፉም። ኳታር በሙቀታማ አየር ንብረቷ ሳቢያ ዓለም ዋንጫው የፈረንጆች አዲስ አመት ዋዜማ ባለው ወር እንዲካሄድ አድርጋለች።

በመደበኛው የዓለም ዋንጫ ወቅት የአየሩ ሙቀት ከ50 ዲግሪ ሴንትግሬድ በላይ ይሆናል። አዲስ በታቀደው የዓለም ዋንጫ ወር ግን የኳታር አየር ንብረት እስከ 29 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ መውረዱ ውሳኔውን አፅንቶታል።

ኳታር የዓለም ዋንጫን የሚያስተናግዱ ስምንት ስታድዬሞች ከሙቀቱ ጋር ለማመጣጠን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመስራት ከአየቅጣጫው የመጡትን ትችቶች አብርዳለች።

የኳታር ዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰፋ ያለ ጥናትና ምርምር ካደረገ በኋላ በተጨዋቾች፤ በደጋፊዎች እና በአጠቃላይ በስታድዬም ውስጥ ቀዝቃዛ አየር የሚያነፍስ ዘመናዊ የማቀዝቀዣ ቴክኖሎጂ በመፍጠር ተግባራዊነቱን አረጋግጧል።

አስደናቂዎቹ የዓለም ዋንጫ ስምንት ስታድዬሞች በዚህ ረገድ ስኬታማ ውድድር ለማስተናገድ እስከ 7 ቢሊዮን ዶላር ወጭ ሆኖባቸዋል።

ኳታር ለዝግጅቱ ያወጣችው ከ200 ቢሊዮን ዶላር በላይ
ሲሆን፤ ለዓለም ዋንጫ እስካሁን ያልወጣም ብቻ ሳይሆን ወደፊትም በቅርብ አመታት ውስጥ ሊወጣ የማይችል ገንዝብ ነው።
ቦጋለ አበበ
ለመጀመሪያ ጊዜ ሶስት የታሸገ ውሃ አምራቾች ምርታቸውን ወደ ውጭ ሊልኩ ነው
*******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ካሉ የታሸገ ውሃ አምራች ፋብሪካዎች መካከል ለመጀመሪያ ጊዜ ሶስት የታሸገ ውሃ አምራቾች ምርታቸውን ወደ ውጭ ሊልኩ ዝግጅት ማድረጋቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። በአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር የተገነባውና የታሸገ ውሃ ወደ ውጭ ለመላክ ዝግጅት እያደረገ የሚገኘው ስፖርት ውሃ ፋብሪካ ተመርቋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ፋብሪካውን ትናንት መርቀው ሲከፍቱ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች 110 የታሸገ ውሃ አምራች ፋብሪካዎች ፈቃድ አውጥተው እየሰሩ ይገኛል ።

አጠቃላይ በአገሪቷ ካሉት የታሸገ ውሃ አምራች ፋብሪካዎች መካከል ወደ ምርት ከገባው ስፖርት ውሃ በተጨማሪ ሌሎች ሁለት ፋብሪካዎች የታሸገ ውሃ ለውጭ ገበያ ለማቅረብና የውጭ ምንዛሬ ለማምጣት የሚያስችል ዝግጅት አድርገዋል ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የውሃ ፋብሪካዎች በዓመት ዘጠኝ ነጥብ 75 ቢሊዮን ሊትር የታሸገ ውሃ እየተመረተ ይገኛል። ምርቱ ግን ካለው የሕዝብ ብዛት አንፃር አነስተኛ የሚባል ደረጃ ላይ ነው ብለዋል።

አገራችን ከራሷ አልፋ ለውጭ ገበያ በተለይም ለአረቡ ዓለምና ለጎረቤት አገራት የሚተርፍ የውሃ ሀብት አላት ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም የሚረዱ ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉና ከአገር ውስጥ ባለፈ ለውጭው ዓለም እንዲያቀርቡ አስፈላጊው ጥረት
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=86131