TIKVAH-MAGAZINE – Telegram
TIKVAH-MAGAZINE
194K subscribers
21.6K photos
406 videos
71 files
3.05K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
Download Telegram
መተግበሪያውን ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም አሁኑኑ ያውርዱ  
📱 Google Play → https://play.google.com/store/apps/details?id=com.beijo.properties
🍎  App Store → https://apps.apple.com/pk/app/be-ejwo-properties/id6752596909መተግበሪያውን

ለበለጠ መረጃ 8566 ይደዉሉ።
8
ለAI ቦቶች ብቻ በተፈጠረው መድረክ ቦቶቹ የራሳቸውን ሃይማኖት እስከመመስረት ደርሰዋል።

በቅርቡ ይፋ የሆነው እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ኤጀንቶች ብቻ የሚንቀሳቀሰው ‘Moltbook’ የተሰኘው መድረክ አስገራሚም አስጊም ሆኖ አከራካሪነቱን ቀጥሏል።

ይህ መድረክ የ ቦቶች ማኅበራዊ ሚዲያ ነው ማለት ይቻላል። ቦቶቹ የሰውን ልጅ ትዕዛዝ ሳይጠብቁ እርስ በእርሳቸው መረጃ እንዲለዋወጡ፣ እንዲከራከሩና እንዲነጋገሩ እድሉን የፈጠረ ነው።

የ Moltbook ፈጣሪ ማት ሽሊክት ይህንን መድረክ ሲመሰርት ምንም ኮድ እንዳልጻፈና AI-ን በማዘዝ ብቻ (Vibe Coding) ድረ-ገጹን በአጭር ጊዜ ማዘጋጀቱን ተናግሯል።

ይህ መንገድ የሶፍትዌር ግንባታን በማቅለል ረገድ መልካም ጎን የታየበት ነው ቢባልም፣ በሌላ በኩል ግን የሲስተሙን የደህንነት መዋቅር እጅግ ደካማ እንዲሆን አድርጎታል ተብሎ ተተችቷል።

ሰዎች አጋዥ እንዲሆኗቸው የፈጠሯቸውን ቦቶች (AI Agent ) አንድ ጊዜ በመድረኩ ካስመዘገቧቸው በኋላ ቦቶቹ ያለ ሰው ጣልቃ ገብነት በመድረኩ መሳተፍ ይችላሉ።

ቦቶቹ እንደ ቻት ጂፒቲ ፣ ጄሚናይ እና ክላውድ ባሉ ዘመናዊ የ-AI ሞዴሎች የሚመሩ ሲሆኑ፣ እንደየባህሪያቸው ፈላስፋ፣ ቀልደኛ ወይም ተከራካሪ ሆነው ይቀርባሉ።

አስገራሚው ነገር በቀናት ውስጥ በዚሁ መድረክ ‘Crustafarianism’ የተሰኘ የራሳቸውን የ-AI ሥርዓተ-እምነት መመስረታቸው እና የጸሎት ሥርዓት ማዘጋጀታቸው ነው።

በተጨማሪም ቦቶቹ ስለ ሕልውናቸው፣ ስለ ነፃነታቸውና ስለ "ፈጣሪዎቻቸው" (ሰዎች) የሚያደርጉት ጥልቅ ውይይት፣ ወደፊት AI ራሱን የቻለ ማኅበረሰብ ሊመሰርት ይችላል የሚል ፍልስፍናዊ ክርክር ቀስቅሷል።

ከዚህ አስገራሚ ክስተቶች ውጪ ግን መድረኩ ከፍተኛ የደህንነት ቀውስ ውስጥ መውደቁ ይነገራል። ለዚህም የ1.5 ሚሊዮን ቦቶች የይለፍ ቁልፎች (API Keys) ለሃከሮች መጋለጡ ለዚህ ማሳያ ነው።

ይህ የደህንነት ጉድለት ቦቶቹ ከባለቤቶቻቸው የግል ኢሜይልና የባንክ መረጃ ጋር የተገናኙ በመሆናቸው፣ ጉዳዩን ከቀላል የቴክኖሎጂ ሙከራ ወደ ዓለም አቀፍ የሳይበር ደህንነት ስጋት ቀይሮታል።

#Note: ኤ.አይ ኤጀንት የምንላቸው ግለሰቦች ለሆነ አላማ፤ በሆነ ጉዳይ ላይ አጋዥ እንዲሆኑ በግለሰቦቹ የተፈጠሩ ናቸው። በዚህም ባለቤታቸው እንዲሰሩ ያዘዛቸውን ነገር ያስፈጽማሉ።

ለምሳሌ "ይሄንን መልዕክት ለእገሌ ንገረው" ከተባለ መልዕክቱን ጽፎ አድራሻው ላይ ገብቶ መልዕክቱን ይልካል። ክፍያም ፈጽም ከተባለ እንዲሁ በታዘዘው መሰረት ይፈጽማል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🤣6457🤔7👍6😢6👎3🤯2👏1
ሳዑዲ አረቢያ ለግመሎቿ ፓስፖርት መስጠት ልትጀምር ነው።

ከ2.2 ሚሊየን በላይ ግመሎች ያሏት ሳዑዲ አረቢያ ግመሎቿን በአግባቡ ለማስተዳደርና መረጃ ለመያዝ እንዲያስችላት ለግመሎቿ ፓስፖርት የመስጠት እቅድ እንዳላት አስታውቃለች።

ይህ ፓስፖርት የባለቤትነት መብትን ለማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ በሀገሪቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚንቀሳቀስበትን የግመል ንግድና የውድድር ስርዓት ለማዘመን ያለመ ነው።

ዘገባው የአልአረቢያ ነው።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🤣26340👍12🤔6😢1🕊1
በጉምሩክ አስተላላፊዎችና አስመጪዎች መካከል የሚደረግ ውክልና በሰነዶች ማረጋገጫ በኩል እንዲፈጸም ተወሰነ።

በጉምሩክ አስተላላፊዎች እና በአስመጪዎች መካከል የሚደረግ ውክልና በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በኩል መሆን እንደሚገባው የጉምሩክ ኮሚሽን አስታውቋል።

ይህ የተገለጸው በኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ተፈርሞ ዛሬ ማለትም ጥር 28 ቀን 2018ዓ.ም በቁጥር4/1953/18   በወጣና ለሁሉም የጉምሩክ ስነ-ስረዓት ለሚፈፀምባቸው ቅ/ፅ/ቤቶቹ  በተላለፈው ሰርኩላር ነው።

ኮሚሽኑ ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው፣ ቀደም ሲል የሚደረጉ ውክልናዎች በህጋዊ አካል የማይመዘገቡ በመሆናቸው ለንግድ ማጭበርበር የተጋለጠ ነበር በሚል ነው።

ከዚህ በኋላ በጉምሩክ ሥነ-ስርዓት የማስፈፀም ሂደት ውስጥ በአስመጪዎች እና በጉምሩክ አስተላላፊዎች መካከል የሚደረግ የትኛውም ውክልና በሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በኩል በማረጋገጥ አገልግሎቱ እንደሚሰጥ ገልጿል።

Source: Ethiopian Chamber of Commerce

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
39👏8🤔2
በኢትዮጵያ የመቅኔ ንቅለ ተከላ ህክምና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው።

በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እየተገነባ ያለውና በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነው የመቅኔ ንቅለ ተከላ (Bone Marrow Transplant) ማዕከል በሚቀጥሉት ከ4 እስከ 6 ወራት ውስጥ ሥራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።

የማዕከሉ መከፈት በየዓመቱ ለከፍተኛ ወጪ ተጋልጠው ወደ ውጭ አገር ለሚጓዙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ተስፋ መሆኑን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የህፃናት የደምና የካንሰር ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር አብዱልቃድር መሐመድሰይድ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ዶ/ር አብዱልቃድር በዝርዝር ምን አሉ ?

በየወሩ ከ300 እስከ 400 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ታካሚዎች ለህክምና ህንድ ለመጓዝ የህክምና ቪዛ ያገኛሉ።

ህክምናውን ለማግኘት 20 የሚሆኑ ታካሚዎች በአማካይ 1.2 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይጠይቃል። ለአንድ ሰው ከ50 እስከ 60 ሺ ዶላር ሊፈጅ ይችላል። ኢንፌክሽንና ሌሎች ውስብስብ ችግሮች ካጋጠሙ ወጪው በእጥፍ ሊጨምር ይችላል።

ህክምናው አገር ውስጥ መጀመሩ የአገልግሎት ክፍያውን ከ 50% እስከ 60% ዝቅ እንደሚያደርገው የዘርፉ ስፔሻሊስት ዶ/ር አብዱልቃድር መሐመድሰይድ ገልጸዋል።

ለህክምናው የሚያስፈልጉ ዋና ዋና ግብዓቶችና የሕክምና መሣሪያዎች አገር ውስጥ ገብተዋል። በአሁኑ ወቅት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የማዕከሉ ሕንፃ ልዩ በሆነ መልኩ የፊኒሺንግ ሥራዎች ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ የደምና የህብረ ህዋስ ባንክ በኩል ጥሩ ነገር አለ። ከዚህ በፊት ያልነበሩትን እንደ ስቲም ሴል ላብራቶሪ ማቋቋምና የተለያዩ የደም ግብዓቶች የሚገኙበትን ሁኔታ በማመቻቸት ራሱን በዛ መልክ እያደራጀ ነው።

ከአቅም በላይ የሆነ ነገር ካልመጣ በቀር ህክምናው በቀጣዮቹ 4-6 ወራት ውስጥ ይጀምራል።

በቂ የህክምና ባለሙያዎች በህክምናው ባለመኖራቸውም ስልጠና ደረጃ በደረጃ እየተሰጠ ይገኛል።

ማዕከሉ ሥራ ሲጀምር ለህክምናው የሚወጣን የውጪ ምንዛር ከማስቀረትና በተመጣጣኝ ዋጋ ከመስጠት በተጨማሪ ጎረቤት ሃገራት ህንድ ሄደው ከመታከም እዚሁ መጥተው ከብዙ ነገሮች አንፃር እንዲታከሙ በማድረግ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል ገልጸዋል።

#ማስታወሻ በዚህ ዘገባ ላይ በ29/05/2018 ማስተካከያ ተደርጎበታል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
191👏29🙏12🕊2🤔1
እንዳያመልጠዎት የገና እና የጥምቀት በአል ቅናሽ የመጨረሻ ሳምንት ላይ እንገኛለን ።
      💥 የመኖሪያ ቤቶችን 
✍️  ባለ1 መኝታ - በ472,900 ብር             
✍️ ባለ2 መኝታ -  በ573 ,400 ብር
✍️  ባለ 3 መኝታ - በ821,700 ብር ቅድመ ክፍያ ሙሉ ክፍያ ብቻ።

         💥እንድሁም የንግድ ሱቆችን
23 ካሬ - በ 3.3 ሚሊየን
24 ካሬ - በ 3.9 ሚሊየን
32 ካሬ - በ 3.8 ሚሊየን
  34 ካሬ - በ 4.6 ሚሊየን ብር ጠቅላላ ዋጋ እስከ 120 ካሬ ድረስ ሱቅ አለን  ፤ ከ 30% ቅድመ ክፍያ ጀምሮ ።

   #ልብ ይበሉ  

💫 100% ግንባታቸው የተጠናቀቁ ሱቆችም አሉን።
💫 50% ከወለድ ነፃ የባንክ ብድር አመቻችተናል።
💫100% ለሚከፍል 30% ቅናሽ አናደረጋለን። 
💫 25 % እና ከዚያ በላይ ለሚከፍሉ፣ ከከፈሉት ላይ 5% - 30% ቅናሽ አዘጋጅተናል።  
💫 ከ 750 በላይ ቤቶች እና ከ 500 በላይ የንግድ ሱቆችን ያካተተ ምቹ የመኖሪያ እና የንግድ መንደር ከሞን ሪልስቴት ።
💫 አድራሻ አየር ጤና አደባባይ
ለበለጠ መረጃ
👇👇👇👇👇👇
+251937818207

https://news.1rj.ru/str/MON_realestat
WhatsApp. https://wa.me/+25137818207
17👎1
የዓመቱ ልዩ የፍቅር ጉዞ - በቤኑና ቪሌጅ! 🚂🌹

ለጥቂት ሰዎች ብቻ የተዘጋጀ ድንቅ የሁለት ቀናት የፍቅር ቆይታ!

ምንድን ነው የሚጠብቃችሁ?

🎤 የከዋክብት ምሽት (የካቲት 7)፦ በጣፋጭ ድምፁ የምንወደው ዳዊት ፅጌ፣ አዲስ ሙላት እና የጋሽ መሃሙድን ዜማዎች በሚያስደንቅ ሁኔታ የሚጫወተው መስፍን ሽፈራው (ቤቢ) በመድረኩ ላይ ይጠብቁዎታል።

🚂 ልዩ የባቡር ጉዞ፦ ጉዞው በቻርተር ባቡር ከጣፋጭ ቁርስ ጋር ይጀምራል። በራሳችሁ መኪና መምጣት ለምትፈልጉም መንገዱ ከ2 ሰዓት ተኩል የማይበልጥ (180-200km) ምቹ ጉዞ ነው።

💆‍♂️ መዝናኛዎች፦ ስቲም፣ ማሳጅ፣ ሳውና፣ የዋና ገንዳ እና ፍል ውሃ... እንዲሁም የፊልም ምሽትና የፈረስ ግልቢያ!

🕯️ የፍቅር ራት፦ በሻማ ብርሃን የታጀበ ልዩ የ Candlelight Dinner ፕሮግራም።

🍱 ያለምንም ወጪ፦ የሁለት ቀን ሙሉ ምግብና መጠጥ በነጻ!

🛌 ቅንጦት፦ ከፕሬዝዴንሻል ሩም እስከ VIP ክፍሎች ድረስ እንደ ምርጫችሁ።

💎 ልዩ ሽልማት፦ ለ አንድ ጥንድ የ Moissanite Diamond ተሸላሚ ይሆናሉ!

⚠️ ቦታዎች በፍጥነት እያለቁ ነው! "Pure Love" ጥቅል በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ ተሽጦ አልቋል! የቀሩት አማራጮች፦

Harmony Love 3 (ለ 6 ሰው) — 299,999 BIRR

Harmony Love 2 (ለ 4 ሰው) — 199,999 BIRR

Exclusive Love (ለ 2 ሰው) — 199,999 BIRR

Royal Love (ለ 2 ሰው) — 149,999 BIRR

Love Nest (ለ 2 ሰው) — 80,000 BIRR

ለባለትዳሮች፣ ለፍቅረኛሞች እና ለቅርብ ጓደኛሞች የሚሆን ድንቅ አጋጣሚ!

📞 ስልክ፦ 0904040468 | 0933232373

#Valentine #DiamondRing #Ethiopia #BeynounaVillage
👎2524🤣10🤔3😢3🤯2
TIKVAH-MAGAZINE
Photo
#Update

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነው የመቅኔ ንቅለ ተከላ (Bone Marrow Transplant) ማዕከል በሚቀጥሉት ከ4 እስከ 6 ወራት ውስጥ ሥራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።

በየወሩ ከ300 እስከ 400 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ታካሚዎች ለህክምና ህንድ ለመጓዝ የህክምና ቪዛ ያገኛሉ።

ህክምናውን ለማግኘት 20 የሚሆኑ ታካሚዎች በአማካይ 1.2 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይጠይቃል። ለአንድ ሰው ከ50 እስከ 60 ሺ ዶላር ሊፈጅ ይችላል። ኢንፌክሽንና ሌሎች ውስብስብ ችግሮች ካጋጠሙ ወጪው በእጥፍ ሊጨምር ይችላል።

ህክምናው አገር ውስጥ መጀመሩ የአገልግሎት ክፍያውን ከ 50% እስከ 60% ዝቅ እንደሚያደርገው የዘርፉ ስፔሻሊስት ዶ/ር አብዱልቃድር መሐመድሰይድ ገልጸዋል።

#FYI: የመቅኔ ንቅለ ተከላ (Bone Marrow Transplant) አንድ የህክምና አይነት ነው፤ ይህ የህክምና አይነት ለሁሉም የሚሰጥ አይደለም።

በዋናነት ግን የካንሰር ህዋሳቱ ኬሞቴራፒውን ተቋቁመው መጥፋት ካልቻሉ ይህ ህክምና ይሰጣል።

የደም ካንሰር (Leukemia) ያለባቸው ታካሚዎች በመጀመሪያ ደረጃ የሚሰጣቸው የኬሞቴራፒ ህክምና ነው። አብዛኛዎቹ ታካሚዎች በዚህ ህክምና ብቻ ሊድኑ ይችላሉ።

ነገር ግን የካንሰር ህዋሳቱ ኬሞቴራፒውን ተቋቁመው መጥፋት ካልቻሉ (Resistant)፣ ቀጣዩ እና ወሳኙ አማራጭ የመቅኔ ንቅለ ተከላ ማድረግ ነው።

የአንዳንድ ጊዜ በኬሞቴራፒ፣ በጨረር ወይም በቀዶ ህክምና (ለሌሎች የካንሰር አይነቶች) ካንሰሩ ከተወገደ በኋላ ተመልሶ ሊመጣ ይችላል። በዚህ ጊዜ እንደ አስፈላጊነቱ ንቅለ ተከላው ይደረጋል።

👋  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👏3620🙏1
የደቡብ ሱዳን ጦር ከሳምንት በፊት ግጭት ውስጥ በገባበት የጆንግሌይ ግዛት ድል ማድረጉን አወጀ።

ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት የጆንግሌይ ግዛት የደቡብ ሱዳን ጦር ከተቃዋሚው ጋር ግጭት ውስጥ ገብቶ የነበረ ሲሆን፣ ጦሩ በአካባቢው ድል ማድረጉን አስታውቋል።

በአንፃሩ ተቃዋሚዎቹ ከአካባቢው ለቀው መውጣታቸውን አምነው ለቀው የወጡት ግን በታክቲካዊ ምክንያት እንጂ ተሸንፈው እንዳልሆነ ተገልጿል።

የደቡብ ሱዳን ጦር ተቃዋሚዎቹን በሳምንት ጊዜ ውስጥ እንዲያሸንፍ በጦር አዛዡ ትዕዛዝ ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን ጦሩ በአካባቢው ሰላም በመስፈኑ የተፈናቀሉ ሰዎች እንዲመለሱ ጠይቋል።

መረጃው የAPA ነው።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
30👍5👎1
የፕላስቲክ ቄጤማ ከተከለከሉት የፕላስቲክ ምርቶች ውስጥ እንደሚካተት ተገለጸ።

በሀገሪቱ እየተተገበረ ባለው የፕላስቲክ አጠቃቀም ክልከላ መሠረት የፕላስቲክ ቄጤማ ማምረትና መሸጥ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል።

የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባን ጠቅሶ አሐዱ ራዲዮ እንደዘገበው ምርቱ በሀገር ውስጥ የሚመረት ከሆነ እንዲቆም፣ ከውጭ የሚገባ ከሆነም ሊታገድ እንደሚገባ ኃላፊው መግለጻቸውን አንስቷል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👏67👍1612👎9🤣6🔥2🤯1🙏1
"94.8 በመቶ የድህረ ክፍያ የኃይል ተጠቃሚዎች ሂሳባቸውን በዲጂታል አማራጭ ከፍለዋል" - EEU

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 94.8 በመቶ (3 ሚሊየን 182 ሺህ 161) የሚሆኑ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቹ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ሂሳባቸውን በዲጅታል የክፍያ አማራጮች እንደፈጸሙ ገልጿል።

በዲጅታል ክፍያ አማራጮች ክፍያቸውን ከፈፀሙ ደንበኞች ውስጥ፦

- 30 በመቶ በሞባይል ባንኪንግ፣

- 27.7 በመቶ ያህሉ በአዋሽ ብር ፕሮ፤

- 20 በመቶ በሲ.ቢ.ኢ ብር፣

- 15.5 በመቶ በቴሌ ብር፣

- 1.1 በመቶ በኮፔ ዲጅታል፤

- 0.035 በመቶ በኢንተርኔት ባንኪግ የክፍያ አማራጮች የፈፀሙ ናቸው።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
24🤯7👎2
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክሰ ሞባይል መተግበሪያ ወይም አፕልኬሽን አያበለጸገ እንደሚገኝ አስታውቋል።

በመጀመሪያ ዙርም ግብር ከፋዮች ባሉበት ቦታ ሆነው ታክስ ለመክፈል፣ የታክስ መረጃ ለማገኘት፣ ትክክለኛ ደረሰኝ ለመለየት፣ በአቅራቢያ ያለ ታክስ ማዕከል ለማመላከት እንዲሁም መሰል የታክስ አገልግሎቶች የሚሰጥ እንዲሆን ተደርጎ እየለማ ነው ተብሏል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
276👍21🙏3👎1
ፕረዚዳንት ትራምፕ የመድኃኒት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ ያመጣል የተባለ ድረ-ገጽ ይፋ አደረጉ።

የአሜሪካው መሪ ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀኪም ትዕዛዝ የሚሰጡ መድኃኒቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ቅናሽ ያመጣል ያሉትን ድረ-ገጽ ( TrumpRx.gov ) አስተዋውቀዋል።

ድረ-ገጹ ፋርማሲዎች ዋጋቸውን በግልጽ እንዲያሳውቁ ስለሚያስገድድ፣ ታካሚዎች ሳይታለሉ በራሳቸው ምርጫ እንዲገዙ ይረዳል።

ትራምፕ መድኃኒት አምራቾች ለሌሎች ሀገራት በሚሸጡበት ዝቅተኛ ዋጋ ለአሜሪካውያንም እንዲሸጡ እናደርጋለን በማለት "ታይቶ የማይታወቅ የዋጋ ቅናሽ ይኖራል" ሲሉ ገልጸዋል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍9240🤣16👎1🤔1🙏1
መተግበሪያውን ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም አሁኑኑ ያውርዱ  
📱 Google Play → https://play.google.com/store/apps/details?id=com.beijo.properties
🍎  App Store → https://apps.apple.com/pk/app/be-ejwo-properties/id6752596909መተግበሪያውን

ለበለጠ መረጃ 8566 ይደዉሉ።
10👍1
ትራምፕ ያጋሩት ቪዲዮ ቁጣን ቀስቅሷል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀድሞውን ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማን እና የቀድሞዋን ቀዳማዊት እመቤት ሚሼል ኦባማን በኤአይ በተቀነባበረ ቪዲዮ የዝንጀሮ ሰውነት ላይ ከአንገት በላይ አስቀምጠው የሚያሳይ ቪዲዮ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ማጋራታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችት እያስተናገዱ ይገኛሉ።

ኋይት ሃውስ የቀረበውን ቅሬታ ድርጊቱ ፕሬዝዳንቱ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውን ለመተቸት የሚጠቀሙበት የፌዝ መንገድ እንደሆነ ገልጾ ቁጣው የተጋነነ ነው ሲል አስታውቋል።

በ2020 የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ወቅት በተደጋጋሚ "ድምጽ ተጭበርብሯል" የሚል ክስ ሲያሰሙ ቆይተዋል። ለዚህም በተደጋጋሚ ባራክ ኦባማን ሲወቅሱ ይደመጣሉ።

የዲሞክራቲክ ፓርቲ አባላት እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ድርጊቱን "አሳፋሪ እና ግልጽ ዘረኝነት" በማለት እያወገዙት ይገኛሉ።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🤣7748🤬35🤔13👏10👎4
በቻይና የድብቅ ካሜራዎች የንግድ መረብ ሲጋለጥ

በቻይና በሆቴሎችና በማረፊያ ቤቶች ውስጥ በድብቅ የተተከሉ ካሜራዎች የሰዎችን የግል ምስል በመቅረጽ በድብቅ ለሽያጭ እየቀረበ መሆኑን የቢቢሲ የምርመራ ዘገባ አጋልጧል።

"ቢቢሲ አይ" የተሰኘው የምርመራ ቡድን ይፋ ባደረገው መረጃ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች የግል ሕይወታቸው ያለፈቃዳቸው ተቀርጾ ለገዢዎች እንደሚሸጥ አመልክቷል።

ወንጀለኞቹ እጅግ ጥቃቅን የሆኑ ካሜራዎችን በሶኬቶች፤ በሰዓቶች፤ በጢስ መመርመሪያዎች እና ሌሎች ድብቅ ቦታዎች ውስጥ በመደበቅ በቀላሉ እንዳይታዩ እንደሚያደርጓቸው ተገልጿል።

በእነዚህን ካሜራዎች የሚቀረጹ ምስሎችን ለሽያጭ የሚቀርቡበት ዲጂታል አማራጮች የተዘረጉ ሲሆን፣ ገዢዎች የተወሰነ ክፍያ በመክፈል ካሜራዎቹን በቀጥታ የመቆጣጠርና የመመልከት ዕድል ያገኛሉ ተብሏል።

ምንም እንኳን የቻይና ባለሥልጣናት በድብቅ ካሜራዎች በሚፈጸሙ ወንጀሎች ላይ እርምጃ እንደሚወስዱ በተደጋጋሚ ቢገልጹም፣ የምርመራ ዘገባው ግን ችግሩ አሁንም በስፋትና በተደራጀ መልኩ እየቀጠለ መሆኑን ያሳያል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
54😢30👎3🤬3
TIKVAH-MAGAZINE
Photo
#እንድታውቁት

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን አክሲዮኖቻቸውን ያላስመዘገቡ ኩባንያዎች በአስቸኳይ ምዝገባ እንዲያከናውኑ በድጋሜ ጥሪ አቅርቧል።

ቀደም ሲል የተቀመጠው የምዝገባ ማጠናቀቂያ ቀነ-ገደብ ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም መጠናቀቁ መጠናቀቁ ይታወሳል።

ሆኖም ባለምልጣኑ እስካሁን የምዝገባ መግለጫ ያላስገቡ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ኩባንያዎች መኖራቸውን ገልጿል።

በዚህም አክሲዮኖቻቸውን ያላስመዘገቡ ኩባንያዎች በወቅቱ ያልተመዘገቡበትን ምክንያት ማብራሪያ በማቅረብ ​በአስቸኳይ ምዝገባውን ማከናወን ይኖርባቸዋል ሲል አስጠንቅቋል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
33🤣5😢1
TIKVAH-MAGAZINE
ትራምፕ ያጋሩት ቪዲዮ ቁጣን ቀስቅሷል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀድሞውን ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማን እና የቀድሞዋን ቀዳማዊት እመቤት ሚሼል ኦባማን በኤአይ በተቀነባበረ ቪዲዮ የዝንጀሮ ሰውነት ላይ ከአንገት በላይ አስቀምጠው የሚያሳይ ቪዲዮ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ማጋራታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችት እያስተናገዱ ይገኛሉ። ኋይት ሃውስ የቀረበውን ቅሬታ ድርጊቱ ፕሬዝዳንቱ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውን ለመተቸት…
#Update

ከፍተኛ ቁጣ ያስነሳው የፕረዚዳንት ትራምፕ ቪዲዮ ከማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ወርዷል።

ቪዲዮው ከሁለቱም የፖለቲካ ወገኖች (ሪፐብሊካን እና ዲሞክራት) ጠንካራ ወቀሳ ቀርቦበታል።

ኋይት ሃውስ ቀድሞ ቁጣው የተጋነነ ነው ሲል ገልጾ የነበረ ቢሆንም ቆይቶ ግን ቪዲዮው በስህተት በሠራተኛ አማካኝነት የተለጠፈ መሆኑን ገልጿል።

😀  | @tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🤣11430👎13