አንድን ግለሰብ በመግደል አስከሬኑን ቆራርጠው መጸዳጃ ቤት ውስጥ የጣሉት ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ
678 ሺህ ብር የሚያወጣ በዱቤ የተሸጠን በቆሎ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል የንብረቱን ባለቤት በመግደል አስከሬኑን በመቆራረጥ መጸዳጃ ቤት ውስጥ የጣሉት ሁለት ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ፡፡
ድርጊቱ የተፈጸመው በሀዲያ ዞን ዱና ወረዳ መሆኑን የደቡብ ክልል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡
ከተከሳሾቹ አንዱ የንብረቱን ባለቤት በጥይት ከገደለ በኋላ አስከሬኑን ሁለቱም ተከሳሾች ቆራርጠው በማዳበሪያ በመጠቅለል መጸዳጃ ቤት ውስጥ መክተታቸው ተገልጿል፡፡
የወረዳው ፖሊስም ለአራት ቀናት ያህል ባደረገው ፍለጋ÷ አገልግሎት መሥጠት ባቆመ አሮጌ መጸዳጃ ቤት ውስጥ የሟችን የተቆራረጠ አስከሬን ማግኘቱን አስታውቋል።
ወንጀሉን የፈጸሙት በድለላ ሥራ የሚተዳደርና በሟች ግቢ ውስጥ ቤት ተከራይቶ የሚኖር አቶ ፈለቀ በቀለና በጫኝና አውራጅ የቀን ሥራ የሚተዳደር አቶ ሳሙኤል አበራ የተባሉ ግለሰቦች መሆናቸው ተመልክቷል፡፡
በዚህም 1ኛ ተከሳሽ አቶ ፈለቀ በቀለ ከግል ተበዳይ አቶ አባተ ኢቶሬ ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም ግምቱ 678 ሺህ ብር የሆነ 230 ኩንታል በቆሎ ተቀብሎ በዱቤ ማሻሻጡም ነው የተገለጸው፡፡
ይህንኑ ገንዘብ ለግል ጥቅሙ ለማዋል በማሰብም በመጠጥ ተገፋፍቶ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 4 ሠዓት እስከ 8 ሠዓት ባለው ጊዜ የግል ተበዳይን ወደ ቤቱ በመጥራት በጥይት መግደሉ ተረጋግጧል፡፡
ከ2ኛ ተከሳሽ አቶ ሳሙኤል አበራ ጋር በመሆንም የሟችን አስከሬን ቆራርጠው በሦስት ማዳበሪያ በማድረግ መጸዳጃ ቤት ውስጥ መክተታቸውን 1ኛ ተከሳሽ አረጋግጧል፡፡
የሀድያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ሁለቱም ተከሳሾ በሞት እንዲቀጡ ወስኗል፡፡
ፋና
678 ሺህ ብር የሚያወጣ በዱቤ የተሸጠን በቆሎ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል የንብረቱን ባለቤት በመግደል አስከሬኑን በመቆራረጥ መጸዳጃ ቤት ውስጥ የጣሉት ሁለት ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ፡፡
ድርጊቱ የተፈጸመው በሀዲያ ዞን ዱና ወረዳ መሆኑን የደቡብ ክልል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡
ከተከሳሾቹ አንዱ የንብረቱን ባለቤት በጥይት ከገደለ በኋላ አስከሬኑን ሁለቱም ተከሳሾች ቆራርጠው በማዳበሪያ በመጠቅለል መጸዳጃ ቤት ውስጥ መክተታቸው ተገልጿል፡፡
የወረዳው ፖሊስም ለአራት ቀናት ያህል ባደረገው ፍለጋ÷ አገልግሎት መሥጠት ባቆመ አሮጌ መጸዳጃ ቤት ውስጥ የሟችን የተቆራረጠ አስከሬን ማግኘቱን አስታውቋል።
ወንጀሉን የፈጸሙት በድለላ ሥራ የሚተዳደርና በሟች ግቢ ውስጥ ቤት ተከራይቶ የሚኖር አቶ ፈለቀ በቀለና በጫኝና አውራጅ የቀን ሥራ የሚተዳደር አቶ ሳሙኤል አበራ የተባሉ ግለሰቦች መሆናቸው ተመልክቷል፡፡
በዚህም 1ኛ ተከሳሽ አቶ ፈለቀ በቀለ ከግል ተበዳይ አቶ አባተ ኢቶሬ ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም ግምቱ 678 ሺህ ብር የሆነ 230 ኩንታል በቆሎ ተቀብሎ በዱቤ ማሻሻጡም ነው የተገለጸው፡፡
ይህንኑ ገንዘብ ለግል ጥቅሙ ለማዋል በማሰብም በመጠጥ ተገፋፍቶ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 4 ሠዓት እስከ 8 ሠዓት ባለው ጊዜ የግል ተበዳይን ወደ ቤቱ በመጥራት በጥይት መግደሉ ተረጋግጧል፡፡
ከ2ኛ ተከሳሽ አቶ ሳሙኤል አበራ ጋር በመሆንም የሟችን አስከሬን ቆራርጠው በሦስት ማዳበሪያ በማድረግ መጸዳጃ ቤት ውስጥ መክተታቸውን 1ኛ ተከሳሽ አረጋግጧል፡፡
የሀድያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ሁለቱም ተከሳሾ በሞት እንዲቀጡ ወስኗል፡፡
ፋና
በዲማ ወረዳ ለግዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የሁለት የአካባቢ ሚሊሻዎች ሕይወት ማለፉን የወረዳው መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ገለፀ።
በጋምቤላ ክልል በአኙዋ ብሔረሰብ ዞን በዲማ ወረዳ ለግዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የሁለት የአካባቢ ሚሊሻዎች ሕይወት ሲያልፍ አንድ ሚሊሻ መቁሰሉን የዲማ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኡኬሎ ኡጁሉ ገልፀዋል።
እንደ ሃላፊው ገለፃ ሰኔ 24 ዕለት ከጥዋቱ 2 :00 ላይ ለግዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በካችና ቀበሌ አካባቢ ገብተው በከፈቱት ተኩስ በሰዓቱ ፀጥታ በማስከበር ላይ የነበሩ ሁለት የአካባቢ ሚሊሻዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ አንድ ሚሊሻ ደሞ ቆስሎ በህክምና ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ኡኬሎ አያይዘውም ሰኔ 23 ዕለትም ከቀኑ 3:00 አካባቢ ከካችና ቀበሌ ወደ ናምካዶ ቀበሌ በመጓዝ ላይ የነበረው አንድ ሞተረኛ በጥይት ተመትቶ ጉዳት እንደደረሰ ገልፀዋል።
ሃላፊው አክለውም በወረዳው ላይ የተሻለ ሰላም ቢኖርም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በመንገድ ላይ ዝርፊያ የተሠማሩ ሽፍቶች በተደጋጋሚ ጥቃት እየፈፀሙ መሆኑን ገልፀው የወረዳው መንግስት ጥቃቱን ለማስቆም ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት የአቅሙን ያህል እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ምንጭ- ዲማ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
በጋምቤላ ክልል በአኙዋ ብሔረሰብ ዞን በዲማ ወረዳ ለግዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የሁለት የአካባቢ ሚሊሻዎች ሕይወት ሲያልፍ አንድ ሚሊሻ መቁሰሉን የዲማ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኡኬሎ ኡጁሉ ገልፀዋል።
እንደ ሃላፊው ገለፃ ሰኔ 24 ዕለት ከጥዋቱ 2 :00 ላይ ለግዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በካችና ቀበሌ አካባቢ ገብተው በከፈቱት ተኩስ በሰዓቱ ፀጥታ በማስከበር ላይ የነበሩ ሁለት የአካባቢ ሚሊሻዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ አንድ ሚሊሻ ደሞ ቆስሎ በህክምና ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ኡኬሎ አያይዘውም ሰኔ 23 ዕለትም ከቀኑ 3:00 አካባቢ ከካችና ቀበሌ ወደ ናምካዶ ቀበሌ በመጓዝ ላይ የነበረው አንድ ሞተረኛ በጥይት ተመትቶ ጉዳት እንደደረሰ ገልፀዋል።
ሃላፊው አክለውም በወረዳው ላይ የተሻለ ሰላም ቢኖርም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በመንገድ ላይ ዝርፊያ የተሠማሩ ሽፍቶች በተደጋጋሚ ጥቃት እየፈፀሙ መሆኑን ገልፀው የወረዳው መንግስት ጥቃቱን ለማስቆም ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት የአቅሙን ያህል እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ምንጭ- ዲማ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
እለታዊ ዜና፡ የ #አማራ_ክልል የገጠመው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ለዘመናት የተሰበከው የልዩነት ሃሳብ ውጤት መሆኑን አቶ ደሳለኝ ጣሰው ገለፁ
የአማራ ክልል የገጠመው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር በድንገት የተከሰተ ሳይሆን ለዘመናት የተሰበከው የልዩነት ሃሳብ ውጤት በመሆኑ ችግሮችን ገምግሞ እና አርሞ መውጫ በሮችን ማዘጋጀት ተገቢ ነው ሲሉ የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኅላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ገለፁ፡፡
ኃላፊው ለክልሉ አሁንም ድረስ አጀንዳዎችን በመወርወር አካባቢውን ሠላም የራቀው ቀጣና ለማድረግ የሚሰሩ መኖራቸውን ጠቅሰው የተለያየ ፍላጎት ያላቸው እና በውስጥም በውጭም ያሉ ኃይሎች የክልሉን ሠላም ለማወክ ቀን ከለሊት እየሰሩ ነው ብለዋል።
https://rb.gy/7vdjh
የአማራ ክልል የገጠመው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር በድንገት የተከሰተ ሳይሆን ለዘመናት የተሰበከው የልዩነት ሃሳብ ውጤት በመሆኑ ችግሮችን ገምግሞ እና አርሞ መውጫ በሮችን ማዘጋጀት ተገቢ ነው ሲሉ የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኅላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ገለፁ፡፡
ኃላፊው ለክልሉ አሁንም ድረስ አጀንዳዎችን በመወርወር አካባቢውን ሠላም የራቀው ቀጣና ለማድረግ የሚሰሩ መኖራቸውን ጠቅሰው የተለያየ ፍላጎት ያላቸው እና በውስጥም በውጭም ያሉ ኃይሎች የክልሉን ሠላም ለማወክ ቀን ከለሊት እየሰሩ ነው ብለዋል።
https://rb.gy/7vdjh
ዜና ትንታኔ፡ በኮንደሚኒየም ቤቶች ላይ የወጣው አዲስ የግብር ተመን የህዝቡን አቅም ያላገናዘበ፣ የህግ ክፍተት ያለበት እና ማህበራዊ ቀውስ ሊያስከትል እንደሚችል የህግ ሙሁራንና የቤት ባለንብረቶች ገለጹ
በሞላ ምትኩ
በአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎቸ ቢሮ የተላለፈውና በትግበራ ላይ ያልው የቤት ጣራና ግድግዳ ግብር አዲስ የክፊያ ተመን በአሁኑ ወቅት ያለውን ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ እና አሁን ያለውን የኑሮ ውድነት በህዝቡ ላይ የፈጠረውን አሉታዊ ጫና በከፋ ደረጃ የሚያባብስ ከመሆኑም በላይ የህግ ክፍተት እንዳለበት በጋራ መኖሪያ ህንጻዎች የቤቶች ባለንብረቶች እና የህግ ሙሁራን ተናገሩ።
በአቃቂ ቃሊቲ ከፍለ ከተማ በቂሊንጦ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባለንብረቶች ለአዲስ ስታንዳርድ አንደገለጹት የከተማ አስተዳደሩ ህዝቡ በአስጭናቂ የኑሮ ሁኔታ ላይ እንዳለ እያወቀ አንዳንድ ማስተካከያዎች ቀድመን አንዳናደርግ አስቀድሞ ሳያሳውቀን ድንገተኛ የግብር ክፍያ አስገዳጅ ማምጣቱ አግባብነት የለውም ይላሉ።
https://rb.gy/e4wm0
በሞላ ምትኩ
በአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎቸ ቢሮ የተላለፈውና በትግበራ ላይ ያልው የቤት ጣራና ግድግዳ ግብር አዲስ የክፊያ ተመን በአሁኑ ወቅት ያለውን ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ እና አሁን ያለውን የኑሮ ውድነት በህዝቡ ላይ የፈጠረውን አሉታዊ ጫና በከፋ ደረጃ የሚያባብስ ከመሆኑም በላይ የህግ ክፍተት እንዳለበት በጋራ መኖሪያ ህንጻዎች የቤቶች ባለንብረቶች እና የህግ ሙሁራን ተናገሩ።
በአቃቂ ቃሊቲ ከፍለ ከተማ በቂሊንጦ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባለንብረቶች ለአዲስ ስታንዳርድ አንደገለጹት የከተማ አስተዳደሩ ህዝቡ በአስጭናቂ የኑሮ ሁኔታ ላይ እንዳለ እያወቀ አንዳንድ ማስተካከያዎች ቀድመን አንዳናደርግ አስቀድሞ ሳያሳውቀን ድንገተኛ የግብር ክፍያ አስገዳጅ ማምጣቱ አግባብነት የለውም ይላሉ።
https://rb.gy/e4wm0
ዜና፡ በምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ ሁለት የፖሊስ አዛዦች በጥይት ተገደሉ
በአማራ ክልል፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን የደጀን ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና የወንጀል መከላከል ክፍል ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ወርቁ ሽመልስ ትላንት ሰኔ 26፣ 2015 ለስራ በወጡበት ለጊዜው ማንነቱ ባልታወቀ አካል በተከፈተባቸው ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አስታወቀ፡፡
የፖሊስ አዛዦቹ ላይ ጥቃቱ የተከፈተባቸው ትላንት ከቀኑ 8፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ በደጀን ወረዳ ኩራር ቀበሌ ደምበዛ ጎጥ የሚሰጠውን የ8ኛ ክልላዊ ፈተና የጸጥታ ስራ ለመከታተል በወጡበት መሆኑን የወረዳው አስተዳደር ገልጧል፡፡ አብሯቸው መኪና በማሽከርከር ላይ የነበረ አንድ የፖሊስ አባል ቆስሎ ህክምና እየተደርገለት እነደሚገኝ ገልጧል፡፡
https://rb.gy/v8em2
በአማራ ክልል፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን የደጀን ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና የወንጀል መከላከል ክፍል ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ወርቁ ሽመልስ ትላንት ሰኔ 26፣ 2015 ለስራ በወጡበት ለጊዜው ማንነቱ ባልታወቀ አካል በተከፈተባቸው ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አስታወቀ፡፡
የፖሊስ አዛዦቹ ላይ ጥቃቱ የተከፈተባቸው ትላንት ከቀኑ 8፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ በደጀን ወረዳ ኩራር ቀበሌ ደምበዛ ጎጥ የሚሰጠውን የ8ኛ ክልላዊ ፈተና የጸጥታ ስራ ለመከታተል በወጡበት መሆኑን የወረዳው አስተዳደር ገልጧል፡፡ አብሯቸው መኪና በማሽከርከር ላይ የነበረ አንድ የፖሊስ አባል ቆስሎ ህክምና እየተደርገለት እነደሚገኝ ገልጧል፡፡
https://rb.gy/v8em2
የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ ሰዎች ታግቼ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ንብረት ተዘርፍኩ ያለው አሽከርካሪ ንብረቱን ሸጦ የሀሰት ክስ መመስረቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
አሽከርካሪው ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ/ም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-35747 ኢ/ት በሆነ ተሽከርካሪ አዳማ ከሚገኝ ድርጅት ግምቱ 2 ሚሊዬን 7መቶ ሰላሳ ሺ 240 ብር የሚያወጣ የፌሮ ብረት መርካቶ ከሚገኝ የግል ተበዳይ ሱቅ ለማራገፍ ይጭናል።
የፀጥታ ኃይል ልብስ የለበሱ አካላት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አግተው ንበረቱን እንደዘረፉት በአቃቂ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለቃሊቲ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታል፡፡
ፖሊስ ጣቢያው ለጉዳዩ ልዮ ትኩረት በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ንብረቱን ለማስመለስ ባደረገው በርቱ ክትትልና ባሰባሰበው መረጃ አሽከርካሪው ብረቱን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 አካባቢ ሸጦ ተሽከርካሪውን ጀሞ አካባቢ ማቆሙን ይደርስበታል፡፡
በግለሰቡ ላይ ምርመራው ቀጥሎ ከተሰረቀው ንብረት መካከል ግምቱ 648ሺ 432 ብር የሚያወጣ ብረት ማስመለሱን ፖሊስ ጣቢያው አስታውቋል። የተጣለበትን እምነት ወደኋላ በማለት ንብረቱን ሸጦ ሳይታገት ታግቻለሁ በማለት ፖሊስን ለማሳሳት ሀሰተኛ ክስ የመሰረተው አሽከርካሪ እና የተሰረቀውን ንብረት የገዛውን ጨምሮ በአጠቃላይ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን ፖሊስ አስታውቋል።
አንዳንድ ግለሰቦች ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማቀድ ሳይታገቱ ታግተናል በማለት ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጬ እና ሳይዘረፋ ተዘርፈናል በማለት የግል ጥቅማቸውን በህገወጥ መንገድ ለሟሟላት የሚሯሯጡ መኖራቸውን ያስታወቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ የተለያዩ ሚዲያዎች የእነዚህ ህገወጦች መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ መልእክቱን አስተላልፏል ።
አሽከርካሪው ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ/ም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-35747 ኢ/ት በሆነ ተሽከርካሪ አዳማ ከሚገኝ ድርጅት ግምቱ 2 ሚሊዬን 7መቶ ሰላሳ ሺ 240 ብር የሚያወጣ የፌሮ ብረት መርካቶ ከሚገኝ የግል ተበዳይ ሱቅ ለማራገፍ ይጭናል።
የፀጥታ ኃይል ልብስ የለበሱ አካላት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አግተው ንበረቱን እንደዘረፉት በአቃቂ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለቃሊቲ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታል፡፡
ፖሊስ ጣቢያው ለጉዳዩ ልዮ ትኩረት በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ንብረቱን ለማስመለስ ባደረገው በርቱ ክትትልና ባሰባሰበው መረጃ አሽከርካሪው ብረቱን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 አካባቢ ሸጦ ተሽከርካሪውን ጀሞ አካባቢ ማቆሙን ይደርስበታል፡፡
በግለሰቡ ላይ ምርመራው ቀጥሎ ከተሰረቀው ንብረት መካከል ግምቱ 648ሺ 432 ብር የሚያወጣ ብረት ማስመለሱን ፖሊስ ጣቢያው አስታውቋል። የተጣለበትን እምነት ወደኋላ በማለት ንብረቱን ሸጦ ሳይታገት ታግቻለሁ በማለት ፖሊስን ለማሳሳት ሀሰተኛ ክስ የመሰረተው አሽከርካሪ እና የተሰረቀውን ንብረት የገዛውን ጨምሮ በአጠቃላይ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን ፖሊስ አስታውቋል።
አንዳንድ ግለሰቦች ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማቀድ ሳይታገቱ ታግተናል በማለት ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጬ እና ሳይዘረፋ ተዘርፈናል በማለት የግል ጥቅማቸውን በህገወጥ መንገድ ለሟሟላት የሚሯሯጡ መኖራቸውን ያስታወቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ የተለያዩ ሚዲያዎች የእነዚህ ህገወጦች መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ መልእክቱን አስተላልፏል ።
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች ተገደሉ
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር በማህበራዊ ትስስር ገፁ፣ አቶ አብዱ የመንግስት ኃላፊነታቸው ለመወጣት ሲሰሩ መገደላቸውን ጠቅሶ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በትላንትናው እለት በምስራቅ ጎጃም ዞን የደጀን ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና የወንጀል መከላከል ክፍል ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ወርቁ ሽመልስ ለስራ በወጡበት ለጊዜው ማንነቱ ባልታወቀ አካል በተከፈተባቸው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር በማህበራዊ ትስስር ገፁ፣ አቶ አብዱ የመንግስት ኃላፊነታቸው ለመወጣት ሲሰሩ መገደላቸውን ጠቅሶ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በትላንትናው እለት በምስራቅ ጎጃም ዞን የደጀን ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና የወንጀል መከላከል ክፍል ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ወርቁ ሽመልስ ለስራ በወጡበት ለጊዜው ማንነቱ ባልታወቀ አካል በተከፈተባቸው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።
የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች መገደላቸውን ተከትሎ በከተማዋ ገደቦች ተቀመጡ
የጊዜያዊ የጸጥታ ኮማንድ ፓስት በከተማዋና በአካባቢዉ የሰላምና የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ እንዲሆን እና ዜጎች ያለ ስጋት ወጥተው የሚገቡበት ለማድረግ ብዙ ጥረት የተደረገ ቢሆንም አሁንም ከተማዋን ሰው አልባ እንድትሆንና ከፍተኛ የጸጥታ ችግር እንዲከሰት ጥረቶች እየተደረጉ በመሆኑ ክልከላዎች አድርጊያለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት ከነገ ማለትም ከሰኔ 28/2015 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ከምሽቱ 12 ስዓት ጀምሮ
ማንኛውም ተሽከርካሪ ይሁን የሰው እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ተገድቧል።
በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የምሽት ክለቦችን ጨምሮ ከምሽቱ 12 ስዓት በኃላ ምንም አይነት አገልግሎት አንዳይሰጡ ክልከላ አድርጓል።
እንዲሁም የከተማው ነዋሪ ለጸጥታ መዋቅሩ እገዛውንና ድጋፍ በማድረግ ከተማዋን ካለባት ከፍተኛ የጸጥታ ችግር ልንታደጋት ይገባል ሲል ዛሬ ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል።
የጊዜያዊ የጸጥታ ኮማንድ ፓስት በከተማዋና በአካባቢዉ የሰላምና የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ እንዲሆን እና ዜጎች ያለ ስጋት ወጥተው የሚገቡበት ለማድረግ ብዙ ጥረት የተደረገ ቢሆንም አሁንም ከተማዋን ሰው አልባ እንድትሆንና ከፍተኛ የጸጥታ ችግር እንዲከሰት ጥረቶች እየተደረጉ በመሆኑ ክልከላዎች አድርጊያለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት ከነገ ማለትም ከሰኔ 28/2015 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ከምሽቱ 12 ስዓት ጀምሮ
ማንኛውም ተሽከርካሪ ይሁን የሰው እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ተገድቧል።
በተጨማሪም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የምሽት ክለቦችን ጨምሮ ከምሽቱ 12 ስዓት በኃላ ምንም አይነት አገልግሎት አንዳይሰጡ ክልከላ አድርጓል።
እንዲሁም የከተማው ነዋሪ ለጸጥታ መዋቅሩ እገዛውንና ድጋፍ በማድረግ ከተማዋን ካለባት ከፍተኛ የጸጥታ ችግር ልንታደጋት ይገባል ሲል ዛሬ ኮማንድ ፖስቱ አሳስቧል።
ዜና፡ ምክር ቤቱ “የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል” በሚል ስያሜ 12ኛ ክልል እንዲደራጅ ውሳኔ አሳለፈ
የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የስድስት ዞኖችና የአምስት ልዩ ወረዳዎች ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የተካተቱበት “የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል” በሚል ስያሜ አዲስ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬው እለት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ጌዲዮ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ኮንሶ ዞኖችና ደራሼ፣ ቡርጂ፣ አማሮ፣ ኧሌና ባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች “የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል” በሚል አዲስ ክልል ስር እንዲደራጉ ውስኗል፡፡
https://rb.gy/kdsy1
የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የስድስት ዞኖችና የአምስት ልዩ ወረዳዎች ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የተካተቱበት “የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል” በሚል ስያሜ አዲስ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬው እለት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ጌዲዮ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ኮንሶ ዞኖችና ደራሼ፣ ቡርጂ፣ አማሮ፣ ኧሌና ባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች “የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል” በሚል አዲስ ክልል ስር እንዲደራጉ ውስኗል፡፡
https://rb.gy/kdsy1
ዜና፡ በፋኖ ታጣቂ ሀይሎች ከቀያቸው የተፈናቀሉ የምስራቅ ወላጋና የሆሮ ጉዱሩ ነዋሪዎች ለረሃብ፣ ለበሽታና ለተጨማሪ ሰብዓዊ ቀውስ መጋለጣቸውን ገለፁ
በጌታሁን ለገሰ
በኦሮሚያ ክልል የሆሮ ጉዱሩና የምስራቅ ወለጋ ዞን ነዋሪዎች በፋኖ ታጣቂ ሀይሎች ከቀያቸው ተፈናቅለው ለሰብዓዊ ቀውስ መዳረጋቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ አፋን ኦሮሞ ተናገሩ፡፡ ተፈናቃዮቹ ምንም አይነት ሰብዓዊ እርዳታ እያገኙ እንዳልሆነ ገልፀው ለደህንነት ስጋት፣ ለረሃብ፣ ለመኖሪያ ቤትና ህክምና እጦት መጋለጣቸውን ገልፀዋል፡፡
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ከሆሮ ጉዱሩ ዞን አሙሩ ወረዳ ከሲደን ባርክሌቲ ቀበሌ ተፈናቅሎ ወደ ጊዳ አያና ወረዳ መሸሻቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ የገለፁ አንድ አርሶ አደር፣ ሲኖሩበት በነበረው ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት ባለቤታቸው እና አንድ ልጃቸው እንደተገሉባቸው ተናግረዋል፡፡
አቶ ዳባ 11 የቤተሰባቸውን አባላት ይዘው በጊዳ አያና ከተማ እየኖሩ መሆኑን ገልፀው መንግስት ለአንድ ቤተሰብ እያደረገ ያለው እርዳታ ለአንድ ሰውም የሚበቃ አይደለም ብለዋል፡፡ በርካታ ሰዎች ከአንድ ቤት እየሞቱ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል፡፡
https://rb.gy/2knvx
በጌታሁን ለገሰ
በኦሮሚያ ክልል የሆሮ ጉዱሩና የምስራቅ ወለጋ ዞን ነዋሪዎች በፋኖ ታጣቂ ሀይሎች ከቀያቸው ተፈናቅለው ለሰብዓዊ ቀውስ መዳረጋቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ አፋን ኦሮሞ ተናገሩ፡፡ ተፈናቃዮቹ ምንም አይነት ሰብዓዊ እርዳታ እያገኙ እንዳልሆነ ገልፀው ለደህንነት ስጋት፣ ለረሃብ፣ ለመኖሪያ ቤትና ህክምና እጦት መጋለጣቸውን ገልፀዋል፡፡
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ከሆሮ ጉዱሩ ዞን አሙሩ ወረዳ ከሲደን ባርክሌቲ ቀበሌ ተፈናቅሎ ወደ ጊዳ አያና ወረዳ መሸሻቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ የገለፁ አንድ አርሶ አደር፣ ሲኖሩበት በነበረው ቀበሌ በተፈፀመ ጥቃት ባለቤታቸው እና አንድ ልጃቸው እንደተገሉባቸው ተናግረዋል፡፡
አቶ ዳባ 11 የቤተሰባቸውን አባላት ይዘው በጊዳ አያና ከተማ እየኖሩ መሆኑን ገልፀው መንግስት ለአንድ ቤተሰብ እያደረገ ያለው እርዳታ ለአንድ ሰውም የሚበቃ አይደለም ብለዋል፡፡ በርካታ ሰዎች ከአንድ ቤት እየሞቱ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል፡፡
https://rb.gy/2knvx
ዜና፡ "ብልፅግና መራሹ መንግስትም ሆነ ፓርላማው አገራችን ከገባችነት የፖለቲካ ቅርቃብ ማውጣት ስለማይችሉ ጠ/ሚ አብይ ስልጣንዎን ለጊዚያዊ ሲቪል አስተዳደር ያስረክቡ" - ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ
“ከለውጡ በኋላ ፈተና በዝቷል ለተባለው እውነት ነው ፈተና በስቷል ግን ደግሞ ተፈናው እያዳከመን ሳይሆን እንደ ወርቅ አጠንክሮ እያወጣን ነው”- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ጀምሮ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገሩን ገልፀው ብልፅግና መራሹ መንግስትም ሆነ ፓርላማው አገራችን ከገባችነት የፖለቲካ ቅርቃብ ማውጣት ስለማይችሉ ስልጣንዎን ለጊዚያዊ ሲቪል አስተዳደር ያስረክቡ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አክለውም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በምክር ቤቱ ፍቃድ ምክር ቤቱን እንዲበትኑና ለአዲስ ምርጫ መንገዱን እንዲጠርጉ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ይህን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ፣ “ከለውጡ በኋላ ፈተና በዝቷል ለተባለው እውነት ነው ፈተና በስቷል ግን ደግሞ ተፈናው እያዳከመን ሳይሆን እንደ ወርቅ አጠንክሮ እያወጣን ነው” ብለዋል፡፡ የችግሩ መንስዔ ፖለቲካዊም ኢኮኖሚያዊም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ፖለቲካዊው ፅንፍ የያዘ ፖለቲካ ነው “ እኔ ብቻ ነኝ የምመራው፣ እኔ ካልመራው ምርጫ ይፍረስ፣ እኔ ካልመራው ፓርላማው ይበተን” የሚል ፅንፍ የወጣ አስተሳሰብ ነው ብለዋል፡፡
https://rb.gy/36irx
“ከለውጡ በኋላ ፈተና በዝቷል ለተባለው እውነት ነው ፈተና በስቷል ግን ደግሞ ተፈናው እያዳከመን ሳይሆን እንደ ወርቅ አጠንክሮ እያወጣን ነው”- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ጀምሮ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገሩን ገልፀው ብልፅግና መራሹ መንግስትም ሆነ ፓርላማው አገራችን ከገባችነት የፖለቲካ ቅርቃብ ማውጣት ስለማይችሉ ስልጣንዎን ለጊዚያዊ ሲቪል አስተዳደር ያስረክቡ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አክለውም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በምክር ቤቱ ፍቃድ ምክር ቤቱን እንዲበትኑና ለአዲስ ምርጫ መንገዱን እንዲጠርጉ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ይህን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ፣ “ከለውጡ በኋላ ፈተና በዝቷል ለተባለው እውነት ነው ፈተና በስቷል ግን ደግሞ ተፈናው እያዳከመን ሳይሆን እንደ ወርቅ አጠንክሮ እያወጣን ነው” ብለዋል፡፡ የችግሩ መንስዔ ፖለቲካዊም ኢኮኖሚያዊም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ፖለቲካዊው ፅንፍ የያዘ ፖለቲካ ነው “ እኔ ብቻ ነኝ የምመራው፣ እኔ ካልመራው ምርጫ ይፍረስ፣ እኔ ካልመራው ፓርላማው ይበተን” የሚል ፅንፍ የወጣ አስተሳሰብ ነው ብለዋል፡፡
https://rb.gy/36irx
ዜና: የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በትግራይ ክልል የነበርው ጦርነት እንዲቆም ጥረት ባለማድረጉ ይቅርታ ጠየቀ፡፡
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ በትግራይ ክልል በነበርው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተክርስቲያን ጦርነቱ እንዲቆም መግለጫ ባለመስጠቷ ፣ በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው ሕዝበ ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እያለ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ እንደሚጓዝ የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል፡፡
https://rb.gy/9wwz8
የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ በትግራይ ክልል በነበርው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተክርስቲያን ጦርነቱ እንዲቆም መግለጫ ባለመስጠቷ ፣ በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው ሕዝበ ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እያለ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ እንደሚጓዝ የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል፡፡
https://rb.gy/9wwz8
ሹፌርና ረዳቱን በመግደል 100 ኩንታል ሰሊጥ የጫነን FSR መኪና ይዘው የተሰወሩ ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር አባጀምበር ቀበሌ የጨረቃን ጎጥ ከተባለው ቦታ ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ/ም ፣ ከምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውሃ ከተማ መቶ ኩንታል ሰሊጥ ጭኖ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረን FSR መኪና ፣ ሌሊት ባልታወቀ ሰዓት ማንነታቸው ያልታወቁ ሰወች መኪናውን አስቁመው ሾፌርና ረዳቱን በመግደል መኪናውን ይዘው ይሰወራሉ::
የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በሰራው እጅግ ፈጣንና ጥብቅ የሆነ ክትትል ፣ ወንጀለኞቹ መኪናውን ወደኋላ በመመለስ በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዲቦ ከተማ ወስደው ማሳደራቸውን መረጃ ይደርሰዋል፡፡
ፖሊስ የወንጀለኞችን ዱካ ይዞ ጠንካራ ክትትል በማድረግና እግር በእግር በመከታተል ላይ እያለ ፣ ወንጀለኞቹ ሰኔ 29/2015 ዓም መኪናውን ይዘው ወደ ግንደወይን ከተማ በመመለስ ላይ ሳሉ ፣ ግንደወይን ከተማ አካባቢ ሲደርሱ በጎንቻ ሲሶ እነሴና በግንደወይን ከተማ ህዝብና የጸጥታ አካላት ብርቱ ጥረት አንዱ ወንጀለኛ ከመኪናው ጋር በቁጥጥር ስር ሲውል ፣ ሌሎች ወንጀለኞችን ለመያዝ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቋል፡፡
ወንጀለኞችን ለመያዝ በተደረገው ጥረትም የጎንቻ ሲሶ እነሴና የግንዶይን ከተማ አስተዳደር ህዝብና የፀጥታ አካላትን ፣ እንዲሁም መረጃ በመስጠት ለተባበሩት ሁሉ የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል ።
ምንጭ- ምስራቅ ጎጃም ፖሊስ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር አባጀምበር ቀበሌ የጨረቃን ጎጥ ከተባለው ቦታ ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ/ም ፣ ከምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳ ውሃ ከተማ መቶ ኩንታል ሰሊጥ ጭኖ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረን FSR መኪና ፣ ሌሊት ባልታወቀ ሰዓት ማንነታቸው ያልታወቁ ሰወች መኪናውን አስቁመው ሾፌርና ረዳቱን በመግደል መኪናውን ይዘው ይሰወራሉ::
የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በሰራው እጅግ ፈጣንና ጥብቅ የሆነ ክትትል ፣ ወንጀለኞቹ መኪናውን ወደኋላ በመመለስ በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዲቦ ከተማ ወስደው ማሳደራቸውን መረጃ ይደርሰዋል፡፡
ፖሊስ የወንጀለኞችን ዱካ ይዞ ጠንካራ ክትትል በማድረግና እግር በእግር በመከታተል ላይ እያለ ፣ ወንጀለኞቹ ሰኔ 29/2015 ዓም መኪናውን ይዘው ወደ ግንደወይን ከተማ በመመለስ ላይ ሳሉ ፣ ግንደወይን ከተማ አካባቢ ሲደርሱ በጎንቻ ሲሶ እነሴና በግንደወይን ከተማ ህዝብና የጸጥታ አካላት ብርቱ ጥረት አንዱ ወንጀለኛ ከመኪናው ጋር በቁጥጥር ስር ሲውል ፣ ሌሎች ወንጀለኞችን ለመያዝ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቋል፡፡
ወንጀለኞችን ለመያዝ በተደረገው ጥረትም የጎንቻ ሲሶ እነሴና የግንዶይን ከተማ አስተዳደር ህዝብና የፀጥታ አካላትን ፣ እንዲሁም መረጃ በመስጠት ለተባበሩት ሁሉ የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል ።
ምንጭ- ምስራቅ ጎጃም ፖሊስ
ዜና፡ በ #ሸዋሮቢት ከተማ እንድ የፖሊስ አባል ተደገለ፤ ግድያው በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ የተገደሉ የአካባቢ ባላስልጣንና የፀጥታ አካልን ብዛት ወደ አራት ከፍ አድርጎታል
ምክትል ሳጅን ያለለት ደጉ ትላንት ሰኔ 29 ቀን ማታ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 08 ቀበሌ ከምሽቱ 4 ስዓት በስራ ላይ እያሉ ባልታወቁ ግለሰቦች በጥይት መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡
የአሁኑ ግድያ በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ የተገደሉ የአካባቢ ባላስልጣንና የፀጥታ አካልን ብዛት ወደ አራት ከፍ አድርጎታል፡፡
https://rb.gy/5uzd6
ምክትል ሳጅን ያለለት ደጉ ትላንት ሰኔ 29 ቀን ማታ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 08 ቀበሌ ከምሽቱ 4 ስዓት በስራ ላይ እያሉ ባልታወቁ ግለሰቦች በጥይት መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡
የአሁኑ ግድያ በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ የተገደሉ የአካባቢ ባላስልጣንና የፀጥታ አካልን ብዛት ወደ አራት ከፍ አድርጎታል፡፡
https://rb.gy/5uzd6
በ #ትግራይ ክልል የግብር መክፈያ ጊዜ ለሶስት ወር ተራዘመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015- የትግራይ ክልል ግዚያዊ መስተዳድር ካቢኔ ትናንት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል የ2015 በጀት ዓመት ግብር መክፈያ ጊዜ ማራዘም አንዱ ሲሆን በውሳኔው መሰረት በክልሉ ግብር የሚከፈልበት ጊዜ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል።
የንግድ ፈቃድ የሚታደስበት ወቅትም በተመሳሳይ እስከ መስከረም 30 2016 ዓ.ም ተራዝሟል።
በትግራይ በነበረው ጦርነት ምክንያት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ውል ገብተው ግዴታቸውን ያልተወጡ ኮንትራክተሮች ውላቸው እንዲያሳድሱም ውሳኔ መሰጠቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015- የትግራይ ክልል ግዚያዊ መስተዳድር ካቢኔ ትናንት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል የ2015 በጀት ዓመት ግብር መክፈያ ጊዜ ማራዘም አንዱ ሲሆን በውሳኔው መሰረት በክልሉ ግብር የሚከፈልበት ጊዜ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል።
የንግድ ፈቃድ የሚታደስበት ወቅትም በተመሳሳይ እስከ መስከረም 30 2016 ዓ.ም ተራዝሟል።
በትግራይ በነበረው ጦርነት ምክንያት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ውል ገብተው ግዴታቸውን ያልተወጡ ኮንትራክተሮች ውላቸው እንዲያሳድሱም ውሳኔ መሰጠቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።