የ #ኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ደንበኞቹ የባንክ ሒሳባቸውን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር እንዲያስተሳስሩ አሳሰበ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞቹ የባንክ ሒሳባቸውን ከፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ቁጥር ጋር እንዲያስተሳስሩ፣ ካልሆነ ግን ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ በኋላ ምንም ዓይነት የባንክ አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ አስታወቀ።
ባንኩ ታኅሣሥ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ደንበኞች ወደ የትኛውም የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ ባለ 16 አሃዝ የፋይዳ አካውንት ቁጥራቸውን በማቅረብ ከሒሳባቸው ጋር ማገናኘት እንዳለባቸው ገልጾ ይህንን ያላደረጉ ደንበኞች ገንዘብ ማስገባት፣ ማውጣት እና ሌሎች የባንክ አገልግሎቶችን ማግኘት እንደማይችሉ ባንኩ አስጠንቅቋል።
ባንኩ በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና ድሬዳዋ ደንበኞች እስከ ጥር 1 ቀን 2018 ማስተሳሰር እንደሚችሉ ገልጾ ከጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግን ግዴታ እንደሚሆን አስታውቋል።
በትልልቅ የክልል ከተሞችና በወረዳ ዋና ከተሞች ደንበኞች እስከ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የጊዜ ገደብ የተሰጣቸው ሲሆን፣ የግዴታ አፈጻጸሙ ከየካቲት 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ይተገበራል።
በገጠር ወረዳዎችና ቀበሌዎች ደግሞ....
https://www.facebook.com/share/p/19VgLAQgXB/
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞቹ የባንክ ሒሳባቸውን ከፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ቁጥር ጋር እንዲያስተሳስሩ፣ ካልሆነ ግን ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ በኋላ ምንም ዓይነት የባንክ አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ አስታወቀ።
ባንኩ ታኅሣሥ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ደንበኞች ወደ የትኛውም የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ ባለ 16 አሃዝ የፋይዳ አካውንት ቁጥራቸውን በማቅረብ ከሒሳባቸው ጋር ማገናኘት እንዳለባቸው ገልጾ ይህንን ያላደረጉ ደንበኞች ገንዘብ ማስገባት፣ ማውጣት እና ሌሎች የባንክ አገልግሎቶችን ማግኘት እንደማይችሉ ባንኩ አስጠንቅቋል።
ባንኩ በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና ድሬዳዋ ደንበኞች እስከ ጥር 1 ቀን 2018 ማስተሳሰር እንደሚችሉ ገልጾ ከጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግን ግዴታ እንደሚሆን አስታውቋል።
በትልልቅ የክልል ከተሞችና በወረዳ ዋና ከተሞች ደንበኞች እስከ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የጊዜ ገደብ የተሰጣቸው ሲሆን፣ የግዴታ አፈጻጸሙ ከየካቲት 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ይተገበራል።
በገጠር ወረዳዎችና ቀበሌዎች ደግሞ....
https://www.facebook.com/share/p/19VgLAQgXB/
የ #ሶማሊያ እና የ #ኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር በሞቃዲሾ ተገናኝተው ተወያዩ
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዲሰላም አብዲ አሊ፣ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ጋር በሞቃዲሹ ተገናኝተው ተወያዩ።
ውይይቱ ያተኮረው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት እና ቀጠናዊ ትብብር ይበልጥ በማጠናከር ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በከፍተኛ ደረጃ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ የሁለቱ ሀገራት ባለሥልጣናት እንደ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ባሉ ዘርፎች ያላቸውን ስትራቴጂያዊ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ተወያይተዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚደረገውን የጋራ ጥረት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረጋቸው ተጠቁሟል። እንደ ሽብርተኝነት፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ላሉ ቀጠናዊ ተግዳሮቶች የተቀናጀ ምላሽ መስጠት አስፈላጊ መሆኑንም አፅንዖት ሰጥተውበታል ተብሏል።
ውይይቱ በሁለቱ ጎረቤት አገራት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ያጎላ ሲሆን፤ የኢኮኖሚ አጋርነትን እና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ላይም መክሯል።
ሁለቱም ወገኖች ለሕዝቦቻቸው ጥቅም ሲባል መረጋጋትን፣ ብልጽግናን እና ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማምጣት በቅርበት ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ ማረጋገጣቸውን ሸበሌ ሚዲያ ዘግቧል።
ረጅም ድንበር የሚጋሩትና ታሪካዊ ትስስር ያላቸው ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ዲፕሎማሲያዊ እና የደህንነት ትብብራቸውን አጠናክረዋል። በተለይም የሽብር ቡድኖችን ለመዋጋት እና ቀጠናዊ የልማት ውጥኖችን ለመደገፍ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ ዘገባው አመልክቷል።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዲሰላም አብዲ አሊ፣ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ጋር በሞቃዲሹ ተገናኝተው ተወያዩ።
ውይይቱ ያተኮረው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት እና ቀጠናዊ ትብብር ይበልጥ በማጠናከር ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በከፍተኛ ደረጃ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ የሁለቱ ሀገራት ባለሥልጣናት እንደ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ባሉ ዘርፎች ያላቸውን ስትራቴጂያዊ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ተወያይተዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚደረገውን የጋራ ጥረት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረጋቸው ተጠቁሟል። እንደ ሽብርተኝነት፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ላሉ ቀጠናዊ ተግዳሮቶች የተቀናጀ ምላሽ መስጠት አስፈላጊ መሆኑንም አፅንዖት ሰጥተውበታል ተብሏል።
ውይይቱ በሁለቱ ጎረቤት አገራት መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ያጎላ ሲሆን፤ የኢኮኖሚ አጋርነትን እና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ላይም መክሯል።
ሁለቱም ወገኖች ለሕዝቦቻቸው ጥቅም ሲባል መረጋጋትን፣ ብልጽግናን እና ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማምጣት በቅርበት ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ ማረጋገጣቸውን ሸበሌ ሚዲያ ዘግቧል።
ረጅም ድንበር የሚጋሩትና ታሪካዊ ትስስር ያላቸው ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ዲፕሎማሲያዊ እና የደህንነት ትብብራቸውን አጠናክረዋል። በተለይም የሽብር ቡድኖችን ለመዋጋት እና ቀጠናዊ የልማት ውጥኖችን ለመደገፍ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ ዘገባው አመልክቷል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ የሶማሊያ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ተቀብለው አነጋገሩ
የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብለው ማነጋገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሑፍ "ባለፈው አንድ አመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል" ሲሉ ገልፀዋል።
በተጨማሪም ውይይቱ "የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህን የገለፁት የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዲሰላም አብዲ አሊ፣ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ጋር በሞቃዲሹ ተገናኝተው መወያየታቸውን ተከትሎ ነው።
ውይይቱ ያተኮረው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት እና ቀጠናዊ ትብብር ይበልጥ በማጠናከር ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በከፍተኛ ደረጃ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ የሁለቱ ሀገራት ባለሥልጣናት እንደ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ባሉ ዘርፎች ያላቸውን ስትራቴጂያዊ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ተወያይተዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚደረገውን የጋራ ጥረት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረጋቸው ተጠቁሟል። እንደ ሽብርተኝነት፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ላሉ ቀጠናዊ ተግዳሮቶች የተቀናጀ ምላሽ መስጠት አስፈላጊ መሆኑንም አፅንዖት ሰጥተውበታል ተብሏል።
የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብለው ማነጋገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሑፍ "ባለፈው አንድ አመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል" ሲሉ ገልፀዋል።
በተጨማሪም ውይይቱ "የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህን የገለፁት የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዲሰላም አብዲ አሊ፣ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ጋር በሞቃዲሹ ተገናኝተው መወያየታቸውን ተከትሎ ነው።
ውይይቱ ያተኮረው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት እና ቀጠናዊ ትብብር ይበልጥ በማጠናከር ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በከፍተኛ ደረጃ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ የሁለቱ ሀገራት ባለሥልጣናት እንደ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ባሉ ዘርፎች ያላቸውን ስትራቴጂያዊ ትብብር ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ተወያይተዋል።
በተጨማሪም በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚደረገውን የጋራ ጥረት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረጋቸው ተጠቁሟል። እንደ ሽብርተኝነት፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ላሉ ቀጠናዊ ተግዳሮቶች የተቀናጀ ምላሽ መስጠት አስፈላጊ መሆኑንም አፅንዖት ሰጥተውበታል ተብሏል።
ዜና: በ #ምስራቅ_ወለጋ #ኪረሙ ወረዳ እየተባባሰ በመጣው የፀጥታ ችግር ነዋሪዎች እየተፈናቀሉ መሆኑ ተገለጸ
በ #ኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ላለፉት አምስት ወራት እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ችግር ነዋሪዎችን ለከፋ መፈናቀልና ሰብዓዊ ቀውስ መዳረጉን አዲስ ስታንዳርድ ያነጋገረቻቸው ነዋሪዎች ገለጹፁ።
ነዋሪዎቹ "የፋኖ ታጣቂዎች በአካባቢው መንቀሳቀሳቸው" ለፀጥታው ችግር መባባስ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
የኪረሙ ወረዳ ባለስልጣን የሆኑት አቶ አለባቸው ወዬሳ፣ ሰሞኑን በታጣቂዎች በደረሰ የጸጥታ ችግር ከ1,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን አረጋግጠው፣ ከተፈናቃዮቹ መካከል አብዛኞቹ የኪረሙ ወረዳ የአሹ ኩታዬ፣ የጉዲና ጅሬኛ እና የባቡ መንደሮች ነዋሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከጉዲና ጅሬኛ መንደር የተፈናቀሉ አንድ ነዋሪ፣ "ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊቱን ሙሉ የዘለቀ ተከታታይ ተኩስና ግጭት ነበር" ያሉ ሲሆን "ለሕይወታቸን በመስጋት ሰብላችንንና ቤታችንን ጥለን ወደ ኪረሙ ከተማ በዘመድ ቤት ተጠልለን ነው የምንገኘው" ብለዋል።
ነዋሪው አክለውም ብዙዎቹ ተፈናቃዮች ወደ ጫካ፣ ወደ አጎራባች መንደሮች እንዲሁም ወደ ኪረሙ ከተማ በመሰደድ ለከፍተኛ ችግር እየተጋለጡ መሆኑን ጠቁመዋል።
ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የ12ኛ ክፍል ተማሪ፣ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ትምህርቱን አቋርጦ መፈናቀሉን ተናግሯል።
ሙሉ ዘገባ: https://addisstandard.com/Amharic/?p=10164&=1
በ #ኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ላለፉት አምስት ወራት እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ችግር ነዋሪዎችን ለከፋ መፈናቀልና ሰብዓዊ ቀውስ መዳረጉን አዲስ ስታንዳርድ ያነጋገረቻቸው ነዋሪዎች ገለጹፁ።
ነዋሪዎቹ "የፋኖ ታጣቂዎች በአካባቢው መንቀሳቀሳቸው" ለፀጥታው ችግር መባባስ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
የኪረሙ ወረዳ ባለስልጣን የሆኑት አቶ አለባቸው ወዬሳ፣ ሰሞኑን በታጣቂዎች በደረሰ የጸጥታ ችግር ከ1,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን አረጋግጠው፣ ከተፈናቃዮቹ መካከል አብዛኞቹ የኪረሙ ወረዳ የአሹ ኩታዬ፣ የጉዲና ጅሬኛ እና የባቡ መንደሮች ነዋሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከጉዲና ጅሬኛ መንደር የተፈናቀሉ አንድ ነዋሪ፣ "ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊቱን ሙሉ የዘለቀ ተከታታይ ተኩስና ግጭት ነበር" ያሉ ሲሆን "ለሕይወታቸን በመስጋት ሰብላችንንና ቤታችንን ጥለን ወደ ኪረሙ ከተማ በዘመድ ቤት ተጠልለን ነው የምንገኘው" ብለዋል።
ነዋሪው አክለውም ብዙዎቹ ተፈናቃዮች ወደ ጫካ፣ ወደ አጎራባች መንደሮች እንዲሁም ወደ ኪረሙ ከተማ በመሰደድ ለከፍተኛ ችግር እየተጋለጡ መሆኑን ጠቁመዋል።
ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የ12ኛ ክፍል ተማሪ፣ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ትምህርቱን አቋርጦ መፈናቀሉን ተናግሯል።
ሙሉ ዘገባ: https://addisstandard.com/Amharic/?p=10164&=1
Addis standard
በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ እየተባባሰ በመጣው የፀጥታ ችግር ነዋሪዎች እየተፈናቀሉ መሆኑ ተገለጸ - Addis standard
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10/ 2018 ዓ/ም:- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ላለፉት አምስት ወራት እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ችግር ነዋሪዎችን ለከፋ መፈናቀልና ሰብዓዊ ቀውስ መዳረጉን አዲስ ስታንዳርድ ያነጋገረቻቸው ነዋሪዎች ገለጹፁ። ነዋሪዎቹ “የፋኖ ታጣቂዎች በአካባቢው መንቀሳቀሳቸው” ለፀጥታው ችግር መባባስ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል። የኪረሙ ወረዳ ባለስልጣን የሆኑት አቶ አለባቸው…
#ኢትዮጵያ እና #ኬንያ የድንበር ንግድ ስምምነት ተፈራረሙ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እና የኬንያ የኢንቨስትመንት፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ካቢኔ ሲክሬተሪ ሊ ኪንያንጂዩን በትናንትናው ዕለት የድንበር ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ እ.ኤ.አ ሚያዚያ 17 ቀን 2025 በኬንያ ሞምባሳ የተደረሰበት ስምምነት አካል መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ አክለውም በሁለቱ ጎረቤት አገሮች መካከል ለረጅም ጊዜ የወዳጅነት እና የሁለትዮሽ ትብብር ታሪክ ውስጥ ጉልህ ምዕራፍ የሚኖረው ነው ብለዋል።
አክለውም የንግድ እንቅፋቶችን በመቀነስ አነስተኛ መጠን ያለው ድንበር ተሻጋሪ ንግድን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በአሁኑ ጊዜ አብዛኛዎቹን መደበኛ ያልሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎች በተለይም ለሴቶች እና ወጣቶች ግልጽና ሊገመት የሚችል ማዕቀፍ የሚፈጥር መሆኑንም ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ወደ ሙሉ ትግበራ ሲገባ የንግድ ዕድሎችን የሚያሰፋ ሲሆን የሁለቱ ሃገራት መንግስታትና የግሉ ዘርፍ በጠንካራ ቅንጅት መስራት ይኖርብናል ሲሉ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ስምምነቱ የጉምሩክ አሠራሮችን ቀላል በማድረግ እና ሰነዶችን በማስማማት ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ህጋዊ እና ዘላቂ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲፈጠር እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
የኬንያ ልኡካን ቡድን በቆይታቸው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የወጪ ንግድ ማዕከል መጎብኘታቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እና የኬንያ የኢንቨስትመንት፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ካቢኔ ሲክሬተሪ ሊ ኪንያንጂዩን በትናንትናው ዕለት የድንበር ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ እ.ኤ.አ ሚያዚያ 17 ቀን 2025 በኬንያ ሞምባሳ የተደረሰበት ስምምነት አካል መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ አክለውም በሁለቱ ጎረቤት አገሮች መካከል ለረጅም ጊዜ የወዳጅነት እና የሁለትዮሽ ትብብር ታሪክ ውስጥ ጉልህ ምዕራፍ የሚኖረው ነው ብለዋል።
አክለውም የንግድ እንቅፋቶችን በመቀነስ አነስተኛ መጠን ያለው ድንበር ተሻጋሪ ንግድን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በአሁኑ ጊዜ አብዛኛዎቹን መደበኛ ያልሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎች በተለይም ለሴቶች እና ወጣቶች ግልጽና ሊገመት የሚችል ማዕቀፍ የሚፈጥር መሆኑንም ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ወደ ሙሉ ትግበራ ሲገባ የንግድ ዕድሎችን የሚያሰፋ ሲሆን የሁለቱ ሃገራት መንግስታትና የግሉ ዘርፍ በጠንካራ ቅንጅት መስራት ይኖርብናል ሲሉ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ስምምነቱ የጉምሩክ አሠራሮችን ቀላል በማድረግ እና ሰነዶችን በማስማማት ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ህጋዊ እና ዘላቂ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲፈጠር እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
የኬንያ ልኡካን ቡድን በቆይታቸው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የወጪ ንግድ ማዕከል መጎብኘታቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#ኢትዮ_ቴሌኮምና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኤክስፖርት የጥራት ደረጃ የተዘጋጁ ምርቶችን በ #ዘመን_ገበያ በኩል ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ለማቅረብ የሚያሰችል ስምምነት ተፈራረሙ
ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚመረቱ የኤክስፖርት ጥራት ያላቸውን ምርቶች በቴሌብር "ዘመን ገበያ" አማካኝነት ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ አምራቾች ለዓለም አቀፍ ገበያ የሚያቀርቧቸውን ምርቶች ለመጀመሪያ ጊዜ ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።
በ"ዘመን ገበያ" ላይ ለግብይት የሚቀርቡት ምርቶች፣ ከፍተኛ የጥራት ደረጃ ያላቸው ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች ፤ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ምርቶች ፤ የኤሌክትሮኒክስና ቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲሁም መድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶች ይገኙበታል።
https://www.facebook.com/share/p/1APAyCV53y/
ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚመረቱ የኤክስፖርት ጥራት ያላቸውን ምርቶች በቴሌብር "ዘመን ገበያ" አማካኝነት ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ አምራቾች ለዓለም አቀፍ ገበያ የሚያቀርቧቸውን ምርቶች ለመጀመሪያ ጊዜ ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።
በ"ዘመን ገበያ" ላይ ለግብይት የሚቀርቡት ምርቶች፣ ከፍተኛ የጥራት ደረጃ ያላቸው ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች ፤ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ምርቶች ፤ የኤሌክትሮኒክስና ቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲሁም መድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶች ይገኙበታል።
https://www.facebook.com/share/p/1APAyCV53y/
የ #ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልገሎት ለመስጠት ከ #ቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሰጠውን አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግና ይበልጥ ለማዘመን የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ ጋር መፈራረሙን አስታወቀ፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙቱ የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመውና የሁዋዌ ኩባንያ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሲሆኑ፤ ስምምነቱንም በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት ተካሂዷል፡፡
የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በሃገራችን ስማርት ግሪድ ለማስፋፋት፣ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ለማዘመንና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ከህዋዌ ጋር በትብብር ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው በፊርማ ስነ ስርዓቱ ወቅት ተናግረዋል፡፡
እንደ አገልግሎቱ መረጃ ኢንጅነር ጌቱ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ቻርጅ መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ሁሉቱም ተቋማት በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን ገልፀዋል፡፡
ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መስመር ስርጭት መቆጣጠሪያ ለመገንባት፣ ለረጅም ጊዜ ኢነርጂ የሚያቆዩ ባትሪዎችን ለመትከልና የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችን በኢትዮጵያ ለመተግበር ስምምነት ላይ መደረሱንም ጨመረው ጠቁመዋል፡፡
የሁዋዌ ኩባንያ ተወካዮች በበኩላቸው በፈጠራ ላይ የተመሰረቱና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የተላበሱ ዘላቂ የኢነርጂ መፍትሄ ቴክኖሎጂዎችን በኢትዮጵያ ለመተግበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
ቴክኖሎጂን አውቆ የሚተገበር ሠራተኛን ለመፍጠር ክህሎት ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን እንደሚያመቻቹም ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሰጠውን አገልግሎት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግና ይበልጥ ለማዘመን የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ ጋር መፈራረሙን አስታወቀ፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙቱ የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመውና የሁዋዌ ኩባንያ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሲሆኑ፤ ስምምነቱንም በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት ተካሂዷል፡፡
የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በሃገራችን ስማርት ግሪድ ለማስፋፋት፣ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ለማዘመንና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ከህዋዌ ጋር በትብብር ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው በፊርማ ስነ ስርዓቱ ወቅት ተናግረዋል፡፡
እንደ አገልግሎቱ መረጃ ኢንጅነር ጌቱ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ቻርጅ መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ሁሉቱም ተቋማት በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን ገልፀዋል፡፡
ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መስመር ስርጭት መቆጣጠሪያ ለመገንባት፣ ለረጅም ጊዜ ኢነርጂ የሚያቆዩ ባትሪዎችን ለመትከልና የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችን በኢትዮጵያ ለመተግበር ስምምነት ላይ መደረሱንም ጨመረው ጠቁመዋል፡፡
የሁዋዌ ኩባንያ ተወካዮች በበኩላቸው በፈጠራ ላይ የተመሰረቱና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የተላበሱ ዘላቂ የኢነርጂ መፍትሄ ቴክኖሎጂዎችን በኢትዮጵያ ለመተግበር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
ቴክኖሎጂን አውቆ የሚተገበር ሠራተኛን ለመፍጠር ክህሎት ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን እንደሚያመቻቹም ተናግረዋል፡፡
#አሜሪካ ወታደሮችን ለማሰባሰብ ተግዳሮት በገጠማት ወቅት፤ ማርኮ ሩቢዮ #ኢትዮጵያ በጋዛ ለታቀደው ሰላም አስከባሪ ኃይል ወታደሮችን እንድታዋጣ ጥያቄ ማቅረባቸው ተዘገበ
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በጋዛ ለታቀደው ዓለም አቀፍ የጸጥታ ኃይል ወታደሮቿን እንድታዋጣ እንዲያስቡበት መጠየቃቸውን ‘ዘ ታይምስ ኦፍ ኢስራኤል’ የምዕራባውያን ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ዋሽንግተን በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የ20 ነጥብ የጋዛ እቅድ ስር የተመለከተውን ዓለም አቀፍ ኃይል ለማዋቀር በሚደረገው ጥረት፣ ጥያቄው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የቀረበ መሆኑ ተገልጿል።
እቅዱ በጦርነት ምክንያት ክፉኛ በፈራረሰው የፍልስጤም ግዛት ውስጥ፣ መልሶ ግንባታ እና ኢኮኖሚያዊ ማገገም ላይ ትኩረት ለሚያደርገው የሽግግር ወቅት ክትትል የሚሰጥ ዓለም አቀፍ የጸጥታ ኃይል እንዲኖር ይጠይቃል። ግዛቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ በዘለቀው ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ውድመት ደርሶበታል።
ብዙ አገራት በዓለምአቀፍ ኃይሉ ውስጥ ተሳትፎ ማድረግን በጥንቃቄ እየተመለከቱት መሆኑ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለጸጥታ ኃይሉ ድጋፍ ለማግኘት ተግዳሮት እንዲገጥማት ማድረጉን ዘገባው አመልክቷል።
በተለይም የተልዕኮው ዓላማ በጋዛ የሚንቀሳቀሰውን ሐማስን ትጥቅ ማስፈታት መሆኑ፣ አገራቱ ለመሳተፍ እንዲሰጉ አድርጓቸዋል ተብሏል። ይህ ስጋት በዕቅድ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የጸጥታ ኃይል አባላት የማሟላት ጥረትን እንዳወሳሰበው ተመላክቷል።
የቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥትም በኩል ሆነ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እስካሁን የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።
https://www.facebook.com/share/1C7X3PrwXb/
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በጋዛ ለታቀደው ዓለም አቀፍ የጸጥታ ኃይል ወታደሮቿን እንድታዋጣ እንዲያስቡበት መጠየቃቸውን ‘ዘ ታይምስ ኦፍ ኢስራኤል’ የምዕራባውያን ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ዋሽንግተን በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የ20 ነጥብ የጋዛ እቅድ ስር የተመለከተውን ዓለም አቀፍ ኃይል ለማዋቀር በሚደረገው ጥረት፣ ጥያቄው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የቀረበ መሆኑ ተገልጿል።
እቅዱ በጦርነት ምክንያት ክፉኛ በፈራረሰው የፍልስጤም ግዛት ውስጥ፣ መልሶ ግንባታ እና ኢኮኖሚያዊ ማገገም ላይ ትኩረት ለሚያደርገው የሽግግር ወቅት ክትትል የሚሰጥ ዓለም አቀፍ የጸጥታ ኃይል እንዲኖር ይጠይቃል። ግዛቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ በዘለቀው ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ውድመት ደርሶበታል።
ብዙ አገራት በዓለምአቀፍ ኃይሉ ውስጥ ተሳትፎ ማድረግን በጥንቃቄ እየተመለከቱት መሆኑ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለጸጥታ ኃይሉ ድጋፍ ለማግኘት ተግዳሮት እንዲገጥማት ማድረጉን ዘገባው አመልክቷል።
በተለይም የተልዕኮው ዓላማ በጋዛ የሚንቀሳቀሰውን ሐማስን ትጥቅ ማስፈታት መሆኑ፣ አገራቱ ለመሳተፍ እንዲሰጉ አድርጓቸዋል ተብሏል። ይህ ስጋት በዕቅድ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የጸጥታ ኃይል አባላት የማሟላት ጥረትን እንዳወሳሰበው ተመላክቷል።
የቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥትም በኩል ሆነ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እስካሁን የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።
https://www.facebook.com/share/1C7X3PrwXb/
ዜና: የገንዘብ ድጋፍ እጥረት በ1.1 ሚሊዮን ሰዎች ላይ አደጋ መደቀኑን ተከትሎ ኢትዮጵያ ወደ ሀገሯ ለሚገቡ ስደተኞች የምታደርገው የዕርዳታ መርሃ ግብር ሊቀለበስ እንደሚችል የረድኤት ድርጅቶች አስጠነቀቁ
አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ካልተገኘ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ስደተኞች የሚቀርቡ መሠረታዊ አገልግሎቶች ሊቋረጡ እንደሚችሉና የኢትዮጵያ የስደተኞች ዕርዳታ መርሃ ግብር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት እንደሚገኝ መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የረድኤት ተቋማት አስጠነቀቁ።
የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እና የዓለም የምግብ ፕሮግራም ትናንት ታኅሣሥ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለአዲስ ስታንዳርድ በላኩት የጋራ መግለጫ፤ የገንዘብ እጥረቱ በስደተኞች ላይ የሚደረገውን ድጋፍ “ሊቋቋሙት ወደማይችሉበት ደረጃ” አድርሶታል ብለዋል።
ተቋማቱ በመግለጫቸው በአፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ስደተኞች በመቀበል ሁለተኛ የሆነችው ኢትዮጵያ በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን ግጭት፣ እንዲሁም በሶማሊያ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ወደ ሀገሯ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር ቢጨምርም፤ የሚገኘው የገንዘብ ድጋፍ ግን በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል ሲሉ ገልጸዋል። በዚህ የገንዘብ እጥረት ምክንያትም በ2025 (እ.ኤ.አ) የሚቀርቡ የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ቁሳቁሶች በ70 በመቶ መቀነሳቸውን ገልጸዋል።
የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ጫና ባይቀንስም ስደተኞችን የመጠበቅ ግዴታዋን እየተወጣች ትገኛለች ሲሉ ተናግረዋል።
ሆኖም ይህንን ከባድ ኃላፊነት መንግሥት ብቻውን ሊወጣው አይችልም ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ያሉ ሀብቶች ከአቅም በላይ መለጠጣቸውንና በአስተናጋጅ ማኅበረሰቦች ላይ የሚፈጠረው ጫናም እየጨመረ መምጣቱን አክለው ገልጸዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ይመልከቱ:-
https://addisstandard.com/Amharic/?p=10166&=1
አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ካልተገኘ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ስደተኞች የሚቀርቡ መሠረታዊ አገልግሎቶች ሊቋረጡ እንደሚችሉና የኢትዮጵያ የስደተኞች ዕርዳታ መርሃ ግብር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት እንደሚገኝ መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የረድኤት ተቋማት አስጠነቀቁ።
የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እና የዓለም የምግብ ፕሮግራም ትናንት ታኅሣሥ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለአዲስ ስታንዳርድ በላኩት የጋራ መግለጫ፤ የገንዘብ እጥረቱ በስደተኞች ላይ የሚደረገውን ድጋፍ “ሊቋቋሙት ወደማይችሉበት ደረጃ” አድርሶታል ብለዋል።
ተቋማቱ በመግለጫቸው በአፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ስደተኞች በመቀበል ሁለተኛ የሆነችው ኢትዮጵያ በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን ግጭት፣ እንዲሁም በሶማሊያ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ወደ ሀገሯ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር ቢጨምርም፤ የሚገኘው የገንዘብ ድጋፍ ግን በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል ሲሉ ገልጸዋል። በዚህ የገንዘብ እጥረት ምክንያትም በ2025 (እ.ኤ.አ) የሚቀርቡ የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ቁሳቁሶች በ70 በመቶ መቀነሳቸውን ገልጸዋል።
የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ጫና ባይቀንስም ስደተኞችን የመጠበቅ ግዴታዋን እየተወጣች ትገኛለች ሲሉ ተናግረዋል።
ሆኖም ይህንን ከባድ ኃላፊነት መንግሥት ብቻውን ሊወጣው አይችልም ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ያሉ ሀብቶች ከአቅም በላይ መለጠጣቸውንና በአስተናጋጅ ማኅበረሰቦች ላይ የሚፈጠረው ጫናም እየጨመረ መምጣቱን አክለው ገልጸዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ይመልከቱ:-
https://addisstandard.com/Amharic/?p=10166&=1
Addis standard
የገንዘብ ድጋፍ እጥረት በ1.1 ሚሊዮን ሰዎች ላይ አደጋ መደቀኑን ተከትሎ ኢትዮጵያ ወደ ሀገሯ ለሚገቡ ስደተኞች የምታደርገው የዕርዳታ መርሃ ግብር ሊቀለበስ እንደሚችል የረድኤት ድርጅቶች አስጠነቀቁ -…
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11/ 2018 ዓ/ም:- ስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ካልተገኘ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ስደተኞች የሚቀርቡ መሠረታዊ አገልግሎቶች ሊቋረጡ እንደሚችሉና የኢትዮጵያ የስደተኞች ዕርዳታ መርሃ ግብር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት እንደሚገኝ መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የረድኤት ተቋማት አስጠነቀቁ። የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት፣…
#የመን 180 #ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በህገወጥ መንገድ በሻብዋ የባህር ዳርቻ መድረሳቸውን አስታወቀች
የመን የሚገቡ መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ባለበት በዚህ ወቅት 180 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በሚገኘው የሻብዋ የባህር ዳርቻ መድረሳቸውን የየመን የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ትናንት እሁድ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ የሽብዋ አካባቢ ፖሊስ 180 ስደተኞች በአራት ሶማሊያውያን በሚመራ የኮንትሮባንድ ጀልባ ከአፍሪካ ቀንድ የተነሱ ኢትዮጵያውያን ዜጎች መሆናቸውን ገልጿል ብሏል።
መግለጫው እንዳስታወቀው፣ የሻብዋ አካባቢ የፀጥታ ባለስልጣናት የስደተኞችን ፍልሰት ለመግታት እና ህገ-ወጥ ሰርጎ ገብነትን ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰዱ ነው።
በተመሳሳይ፣ ዓለምአቀፉ የስደተኞች ድርጅት ያወጣው የቅርብ ጊዜ መረጃ እንደሚያሳየው በህዳር ወር 17,659 ስደተኞች ወደ የመን ገብተዋል። በጥቅምት ወር ደግሞ የገቡት ስደተኞች ቁጥር 17,685 ነበር።
እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት የተፈናቃዮች መከታተያ መረጃ ከሆነ፥ ጅቡቲ በ67 በመቶ ቀዳሚዋ የስደተኞች መነሻ አገር ሆና ቀጥላለች። በመቀጠል ሶማሊያ 31 በመቶ እንዲሁም ኦማን 2 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ ይዘዋል።
ምንም እንኳን የመን የፀጥታ ሁኔታዋ እና በአገሪቱ ያለው የሰብአዊ ቀውስ እየተባባሰ ቢመጣም፣ ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለመሻገር ለሚሞክሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞች እንደ ዋና መሸጋገሪያ መስመር ሆና ማገልገሏን ቀጥላለች። ከእነዚህም መካከል አብዛኛዎቹ በኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እጅ ለከፋ መከራ እና ብዝበዛ እንደሚጋለጡ ዥንዋ ዘግቧል።
የመን የሚገቡ መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ባለበት በዚህ ወቅት 180 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በሚገኘው የሻብዋ የባህር ዳርቻ መድረሳቸውን የየመን የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ትናንት እሁድ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ የሽብዋ አካባቢ ፖሊስ 180 ስደተኞች በአራት ሶማሊያውያን በሚመራ የኮንትሮባንድ ጀልባ ከአፍሪካ ቀንድ የተነሱ ኢትዮጵያውያን ዜጎች መሆናቸውን ገልጿል ብሏል።
መግለጫው እንዳስታወቀው፣ የሻብዋ አካባቢ የፀጥታ ባለስልጣናት የስደተኞችን ፍልሰት ለመግታት እና ህገ-ወጥ ሰርጎ ገብነትን ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰዱ ነው።
በተመሳሳይ፣ ዓለምአቀፉ የስደተኞች ድርጅት ያወጣው የቅርብ ጊዜ መረጃ እንደሚያሳየው በህዳር ወር 17,659 ስደተኞች ወደ የመን ገብተዋል። በጥቅምት ወር ደግሞ የገቡት ስደተኞች ቁጥር 17,685 ነበር።
እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት የተፈናቃዮች መከታተያ መረጃ ከሆነ፥ ጅቡቲ በ67 በመቶ ቀዳሚዋ የስደተኞች መነሻ አገር ሆና ቀጥላለች። በመቀጠል ሶማሊያ 31 በመቶ እንዲሁም ኦማን 2 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ ይዘዋል።
ምንም እንኳን የመን የፀጥታ ሁኔታዋ እና በአገሪቱ ያለው የሰብአዊ ቀውስ እየተባባሰ ቢመጣም፣ ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለመሻገር ለሚሞክሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞች እንደ ዋና መሸጋገሪያ መስመር ሆና ማገልገሏን ቀጥላለች። ከእነዚህም መካከል አብዛኛዎቹ በኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እጅ ለከፋ መከራ እና ብዝበዛ እንደሚጋለጡ ዥንዋ ዘግቧል።
የ #ኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ያቋረጠበት የአየር ፀባይ ለዉጥ በ #ደሴ እና አካባቢው የደረሱ ሰብሎችን አወደመ
በ #አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማና አካባቢዋ በድንገት በተቀየረ የአየር ሁኔታ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎቹን ለማቋረጥ መገደዱን አስታወቋል።
አየር መንገዱ ለበረራ አመቺ ያልሆነ የአየር ፀባይ በመከሰቱ የታህሳስ 12 አና 13 ቀን በረራዎቹን መሰረዙን ትናንት ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
አየር መንገዱ ከሚቲዎሮሎጂ በሚያገኘው መረጃ መሠረት ሁኔታውን እየተከታተለ የአየር ሁኔታው ሲስተካከል በረራዎቹ ወደ መደበኛ አገልግሎታቸው እንደሚመለሱ አመልክቶ በአገልግሎቱ መቋረጥ ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።
በተመሳሳይ በደሴ ዙሪያ ወረዳ በተለይም በደረባ እና በአደይ ቀበሌዎች ታህሳስ 11 ቀን ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ በደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱን የወረዳው ግብርና ልማት ጽህፈት በት አስታዉቋል።
የወረዳው ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ሁሴን የሱፍ በረዶው ለመሰብሰብ ደርሰው በነበሩ ሰብሎች ላይ በድንገት በመጣሉ ከፍተኛ ብክነት ማስከተሉን ጠቅሰዋል።
ምክትል ኃላፊው አክለውም ሰሞኑን የሚታየው ዝናብ በደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ፣ አርሶ አደሩ ከሰላም ስራዎች በተጨማሪ የደረሱ ሰብሎችን በተደራጀ ሁኔታ በመሰብሰብ የሚደርሰውን ተጨማሪ ውድመት እንዲከላከል ጥሪ አቅርበዋል።
በ #አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማና አካባቢዋ በድንገት በተቀየረ የአየር ሁኔታ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎቹን ለማቋረጥ መገደዱን አስታወቋል።
አየር መንገዱ ለበረራ አመቺ ያልሆነ የአየር ፀባይ በመከሰቱ የታህሳስ 12 አና 13 ቀን በረራዎቹን መሰረዙን ትናንት ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
አየር መንገዱ ከሚቲዎሮሎጂ በሚያገኘው መረጃ መሠረት ሁኔታውን እየተከታተለ የአየር ሁኔታው ሲስተካከል በረራዎቹ ወደ መደበኛ አገልግሎታቸው እንደሚመለሱ አመልክቶ በአገልግሎቱ መቋረጥ ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።
በተመሳሳይ በደሴ ዙሪያ ወረዳ በተለይም በደረባ እና በአደይ ቀበሌዎች ታህሳስ 11 ቀን ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ በደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱን የወረዳው ግብርና ልማት ጽህፈት በት አስታዉቋል።
የወረዳው ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ሁሴን የሱፍ በረዶው ለመሰብሰብ ደርሰው በነበሩ ሰብሎች ላይ በድንገት በመጣሉ ከፍተኛ ብክነት ማስከተሉን ጠቅሰዋል።
ምክትል ኃላፊው አክለውም ሰሞኑን የሚታየው ዝናብ በደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ፣ አርሶ አደሩ ከሰላም ስራዎች በተጨማሪ የደረሱ ሰብሎችን በተደራጀ ሁኔታ በመሰብሰብ የሚደርሰውን ተጨማሪ ውድመት እንዲከላከል ጥሪ አቅርበዋል።
የ #አዲስ_አበባ ገቢዎች ቢሮ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገለፀ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበጀት ዓመቱ ባለፉት አምስት ወራት ለግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት ባልሰጡ እና ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መውሰዱን ገለጸ።
በቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አብዱራህማን እንደገለጹት፤ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሳይወጡ በተገኙ 20 አመራሮች እና 159 ፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊ የዲስፕሊን እርምጃ ተወስዷል።
ኃላፊው ይህንን የገለጹት ከዋና መሥሪያ ቤት ጀምሮ በሁሉም ቅርንጫፎችና ወረዳ ጽሕፈት ቤቶች የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ አፈጻጸም ለመገምገም በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነው።
አቶ መሐመድ አብዱራህማን የክትትልና ድጋፍ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመው፤ በተለይም በታክስ ሀርሞናይዜሽን፣ በቲን ቁጥር አሰጣጥ፣ በኢ-ፋይሊንግ (e-filing) እና ኢ-ፔይመንት (e-payment)፣ በመዝጊያ ክሊራንስ እንዲሁም በቅሬታ ሰሚ መማክርት ጉባኤ ውይይቶች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቢሮው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በበኩላቸው፤ የሚሰጡ አገልግሎቶችን የጥራት ደረጃ በማሳደግ ገቢን በፍትሐዊነት መሰብሰብ እንደሚገባ ገልጸዋል። የከተማዋን የልማት ትኩረት ነጥቦች ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ ተገልጋዩ ካለምንም እንግልት አገልግሎት የሚያገኝበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር በየደረጃው ያለ አመራር ዋነኛ ኃላፊነት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበጀት ዓመቱ ባለፉት አምስት ወራት ለግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት ባልሰጡ እና ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ 179 አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ የዲስፕሊን እርምጃ መውሰዱን ገለጸ።
በቢሮው የሞደርናይዜሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አብዱራህማን እንደገለጹት፤ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሳይወጡ በተገኙ 20 አመራሮች እና 159 ፈጻሚዎች ላይ አስተዳደራዊ የዲስፕሊን እርምጃ ተወስዷል።
ኃላፊው ይህንን የገለጹት ከዋና መሥሪያ ቤት ጀምሮ በሁሉም ቅርንጫፎችና ወረዳ ጽሕፈት ቤቶች የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ አፈጻጸም ለመገምገም በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነው።
አቶ መሐመድ አብዱራህማን የክትትልና ድጋፍ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመው፤ በተለይም በታክስ ሀርሞናይዜሽን፣ በቲን ቁጥር አሰጣጥ፣ በኢ-ፋይሊንግ (e-filing) እና ኢ-ፔይመንት (e-payment)፣ በመዝጊያ ክሊራንስ እንዲሁም በቅሬታ ሰሚ መማክርት ጉባኤ ውይይቶች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቢሮው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ሱሌ በበኩላቸው፤ የሚሰጡ አገልግሎቶችን የጥራት ደረጃ በማሳደግ ገቢን በፍትሐዊነት መሰብሰብ እንደሚገባ ገልጸዋል። የከተማዋን የልማት ትኩረት ነጥቦች ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ ተገልጋዩ ካለምንም እንግልት አገልግሎት የሚያገኝበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር በየደረጃው ያለ አመራር ዋነኛ ኃላፊነት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ዜና፡ በ #ጋምቤላ ተጨማሪ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመከላከል በቂ የጸጥታ ኃይል በአስቸኳይ እንዲሰማራ እና ተጎጂዎች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ #ኢሰመኮ አሳሰበ
የ #ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ክልል እየታየ ያለውን የጸጥታ መደፍረስና የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በአስቸኳይ ለመግታት በቂ የጸጥታ ኃይል እንዲሰማራና ተጎጂዎች ተገቢውን ካሳ እና ህክምና እንዲያገኙ አሳሰበ።
ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የጋምቤላ ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አዛዥ የነበሩት ዋና ኢንስፔክተር ኡመድ ኡጁሉ መገደላቸውን ተከትሎ፣ በከተማዋና በአካባቢው ወረዳዎች የተቀሰቀሰውን ግጭትና የተኩስ ልውውጥ መከሰቱን አስታውቋል።
በተከሰተው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ የሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና የአካል ጉዳት መድረሱን፣ የሰዎችን እና የመጓጓዣ አማራጮችን እንቅስቃሴ የሚገድብ የሰዓት እላፊ በክልሉ መንግሥት መጣሉን፤ ባንኮችንና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ በርካታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አገልግሎት ማቋረጣቸውን መገንዘቡን አስታውቋል።
#አዲስ_ስታንዳርድ ታህሳስ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ያነጋገራቸው የጥቃቱ ሰለባና አንድ የሕክምና ባለሙያ በጋምቤላ ከተማ እንዳዲስ የተቀሰቀሰው ጥቃት “በጎሳ ክፍፍል" እንዲሁም "በስልጣን ሽርኩቻ” ላይ ያተኮረ መሆኑን በመጥቀስ፣ የበርካታ ንጹሐን ዜጎች ሕይወት ማለፉና የአካል ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።
አንድ የጥቃቱ ስለባ፤ “በፖሊስ የጸጥታ አካላት በጥይት ጥታቅ እንደተፈጸመበት" ለአዲስ ስታንዳርድ አስረድተዋል። ጥቃቱ “በጎሳ ልዩነቶች” ላይ ያነጣጠረ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጤና ባለሞያ አንዳንድ ታካሚዎች በሆስፒታሉ አካባቢ በሚሰማው የተኩስ ድምፅ በመሸበር፣ ሕክምናቸውን ሳይጨርሱ ወደ ቤታቸው መሄዳቸውን አመልክተዋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10171
የ #ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ክልል እየታየ ያለውን የጸጥታ መደፍረስና የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በአስቸኳይ ለመግታት በቂ የጸጥታ ኃይል እንዲሰማራና ተጎጂዎች ተገቢውን ካሳ እና ህክምና እንዲያገኙ አሳሰበ።
ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የጋምቤላ ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አዛዥ የነበሩት ዋና ኢንስፔክተር ኡመድ ኡጁሉ መገደላቸውን ተከትሎ፣ በከተማዋና በአካባቢው ወረዳዎች የተቀሰቀሰውን ግጭትና የተኩስ ልውውጥ መከሰቱን አስታውቋል።
በተከሰተው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ የሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና የአካል ጉዳት መድረሱን፣ የሰዎችን እና የመጓጓዣ አማራጮችን እንቅስቃሴ የሚገድብ የሰዓት እላፊ በክልሉ መንግሥት መጣሉን፤ ባንኮችንና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ በርካታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አገልግሎት ማቋረጣቸውን መገንዘቡን አስታውቋል።
#አዲስ_ስታንዳርድ ታህሳስ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ያነጋገራቸው የጥቃቱ ሰለባና አንድ የሕክምና ባለሙያ በጋምቤላ ከተማ እንዳዲስ የተቀሰቀሰው ጥቃት “በጎሳ ክፍፍል" እንዲሁም "በስልጣን ሽርኩቻ” ላይ ያተኮረ መሆኑን በመጥቀስ፣ የበርካታ ንጹሐን ዜጎች ሕይወት ማለፉና የአካል ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።
አንድ የጥቃቱ ስለባ፤ “በፖሊስ የጸጥታ አካላት በጥይት ጥታቅ እንደተፈጸመበት" ለአዲስ ስታንዳርድ አስረድተዋል። ጥቃቱ “በጎሳ ልዩነቶች” ላይ ያነጣጠረ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጤና ባለሞያ አንዳንድ ታካሚዎች በሆስፒታሉ አካባቢ በሚሰማው የተኩስ ድምፅ በመሸበር፣ ሕክምናቸውን ሳይጨርሱ ወደ ቤታቸው መሄዳቸውን አመልክተዋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10171
Addis standard
በጋምቤላ ተጨማሪ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመከላከል በቂ የጸጥታ ኃይል በአስቸኳይ እንዲሰማራ እና ተጎጂዎች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ ኢሰመኮ አሳሰበ - Addis standard
አዲስአበባ፣ታኅሣሥ13 ቀን2018 ዓ.ም.፦ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ክልል እየታየ ያለውን የጸጥታ መደፍረስና የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በአስቸኳይ ለመግታት በቂ የጸጥታ ኃይል እንዲሰማራና ተጎጂዎች ተገቢውን ካሳ እና ህክምና እንዲያገኙ አሳሰበ። ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የጋምቤላ ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አዛዥ የነበሩት ዋና ኢንስፔክተር ኡመድ…
የ #ሰላም ሚኒስቴር ከፌዴራልና ክልል ምክር ቤቶች ጋር መከረ፤ በመድረኩ ተቋማት በዕቅዳቸው ውስጥ የሰላም ግንባታን ሊያካትቱ ይገባል ተባለ
የሰላም ሚኒስቴር ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር፣ የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች በሕግ ማውጣት፣ በክትትልና ቁጥጥር ሥራዎቻቸው ውስጥ የሰላም ግንባታን ማካተት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ማካሄዱን አስታወቀ።
የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ ኢድሪስ በመድረኩ ላይ "ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ተቋማት በስትራቴጂያዊ ዕቅዶቻቸው ውስጥ የሰላም ግንባታ ተግባራትን ማካተት ይኖርባቸዋል" ብለዋል።
ሰላም ከአንድ ተቋም ብቻ የሚጠበቅ ሳይሆን በግለሰቦች፣ በተቋማትና በድርጅቶች ሁሉ ውስጥ የጋራ አጀንዳ መሆን እንዳለበት ሚኒስትሩ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ሰላም የሚጀምረው እያንዳንዱ ተቋም የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ከመወጣት ጀምሮ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታና የማኅበረሰብ ግንኙነት እንዲሁም የሰላም ግንባታን ታሳቢ ያደረገ ዲዛይን ሊኖረው እንደሚገባ ጠቁመዋል።
አክለውም የተቋማት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የሰላም ሥራዎችን ሚዛን ውስጥ ያስገባ መሆን እንዳለበት መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ እና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ ቢቂላ ሁሪሳን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ተብሏል።
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
የሰላም ሚኒስቴር ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በመተባበር፣ የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች በሕግ ማውጣት፣ በክትትልና ቁጥጥር ሥራዎቻቸው ውስጥ የሰላም ግንባታን ማካተት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ማካሄዱን አስታወቀ።
የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ ኢድሪስ በመድረኩ ላይ "ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ተቋማት በስትራቴጂያዊ ዕቅዶቻቸው ውስጥ የሰላም ግንባታ ተግባራትን ማካተት ይኖርባቸዋል" ብለዋል።
ሰላም ከአንድ ተቋም ብቻ የሚጠበቅ ሳይሆን በግለሰቦች፣ በተቋማትና በድርጅቶች ሁሉ ውስጥ የጋራ አጀንዳ መሆን እንዳለበት ሚኒስትሩ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ሰላም የሚጀምረው እያንዳንዱ ተቋም የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ከመወጣት ጀምሮ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታና የማኅበረሰብ ግንኙነት እንዲሁም የሰላም ግንባታን ታሳቢ ያደረገ ዲዛይን ሊኖረው እንደሚገባ ጠቁመዋል።
አክለውም የተቋማት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የሰላም ሥራዎችን ሚዛን ውስጥ ያስገባ መሆን እንዳለበት መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ እና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ ቢቂላ ሁሪሳን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ተብሏል።
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ዜና፡ #ሳልሳይ_ወያነ_ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እስኪመለሱና የግዛት አንድነት እስኪረጋገጥ ድረስ ምርጫ እንዲራዘም ጠየቀ
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) በ #ትግራይ ክልል ተዓማኒ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልጉ አነስተኛ የፖለቲካ እና የፀጥታ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው ምርጫው እንዲራዘም ጥሪ አቀረበ።
የሳወት ሊቀመንበር አቶ ክንፈ ሃዱሽ ቅዳሜ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እስኪመለሱና የክልሉ የግዛት አንድነት እስኪረጋገጥ ድረስ የምርጫው ጊዜ መራዘም እንዳለበት ተናግረዋል።
ክልሉ እየተባባሰ በመጣው የፖለቲካ እና የፀጥታ ቀውስ ምክንያት “ከባድ የህልውና አደጋ” ተጋርጦበታል ያሉት አቶ ክንፈ፤ ስልጣንን ለመያዝ ወይም ለማቆየት በትጥቅ ኃይል ላይ የሚደገፉ የፖለቲካ ኃይሎች ክልሉን ወደ አለመረጋጋት እየገፉት መሆኑን አስጠንቅቀዋል።
“በአሁኑ ወቅት በስልጣን ላይ ያለው በመሳሪያ የሚመራ የፖለቲካ ኃይል ነው” ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ገዢው ኃይል ራሱ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት የመጣ መሆኑን እና ሌሎች የፖለቲካ ተዋናዮችም አለመግባባቶችን በወታደራዊ መንገድ ለመፍታት መሞከራቸው መፍትሄ እንደማያመጣ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በወታደራዊ አዛዦች የሚመራ የመንግስት መዋቅር ለክልሉ ደህንነትም ሆነ ተዓማኒነት ላለው ምርጫ ተስፋ ከፍተኛ ስጋት እንደሚፈጥር አስጠንቅቋል። “እንዲህ ዓይነቱ መዋቅር ለነጻ እና ፍትሃዊ የምርጫ ሂደት የሚያስፈልገውን ምህዳር ያዳክማል” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ፣ የትግራይ ክልልን ጨምሮ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች መጪውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10185
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) በ #ትግራይ ክልል ተዓማኒ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልጉ አነስተኛ የፖለቲካ እና የፀጥታ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው ምርጫው እንዲራዘም ጥሪ አቀረበ።
የሳወት ሊቀመንበር አቶ ክንፈ ሃዱሽ ቅዳሜ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እስኪመለሱና የክልሉ የግዛት አንድነት እስኪረጋገጥ ድረስ የምርጫው ጊዜ መራዘም እንዳለበት ተናግረዋል።
ክልሉ እየተባባሰ በመጣው የፖለቲካ እና የፀጥታ ቀውስ ምክንያት “ከባድ የህልውና አደጋ” ተጋርጦበታል ያሉት አቶ ክንፈ፤ ስልጣንን ለመያዝ ወይም ለማቆየት በትጥቅ ኃይል ላይ የሚደገፉ የፖለቲካ ኃይሎች ክልሉን ወደ አለመረጋጋት እየገፉት መሆኑን አስጠንቅቀዋል።
“በአሁኑ ወቅት በስልጣን ላይ ያለው በመሳሪያ የሚመራ የፖለቲካ ኃይል ነው” ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ገዢው ኃይል ራሱ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት የመጣ መሆኑን እና ሌሎች የፖለቲካ ተዋናዮችም አለመግባባቶችን በወታደራዊ መንገድ ለመፍታት መሞከራቸው መፍትሄ እንደማያመጣ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በወታደራዊ አዛዦች የሚመራ የመንግስት መዋቅር ለክልሉ ደህንነትም ሆነ ተዓማኒነት ላለው ምርጫ ተስፋ ከፍተኛ ስጋት እንደሚፈጥር አስጠንቅቋል። “እንዲህ ዓይነቱ መዋቅር ለነጻ እና ፍትሃዊ የምርጫ ሂደት የሚያስፈልገውን ምህዳር ያዳክማል” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ፣ የትግራይ ክልልን ጨምሮ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች መጪውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10185
Addis standard
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እስኪመለሱና የግዛት አንድነት እስኪረጋገጥ ድረስ ምርጫ እንዲራዘም ጠየቀ - Addis standard
መቀለ፣ ታህሳስ 13/ 2018 ዓ/ም፦ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) በትግራይ ክልል ተዓማኒ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልጉ አነስተኛ የፖለቲካ እና የፀጥታ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው ምርጫው እንዲራዘም ጥሪ አቀረበ። የሳወት ሊቀመንበር አቶ ክንፈ ሃዱሽ ቅዳሜ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እስኪመለሱና የክልሉ የግዛት አንድነት እስኪረጋገጥ ድረስ የምርጫው ጊዜ መራዘም እንዳለበት ተናግረዋል።…
የ #ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የንግድ ትስስርን ለማጠናከር የ #ሶማሊላንድን #በርበራ ወደብ ጎበኙ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ልዑክ፣ በሶማሊላንድ የሚገኘውን የበርበራ ወደብ እና የበርበራ ነፃ የንግድ ቀጠናን መጎብኘቱን ባለሥልጣናት አስታወቁ።
ጉብኝቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።
ልዑኩ በኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ የተመራ ሲሆን የሶማሌ ክልል የኢንቨስትመንት፣ የትራንስፖርትና የንግድ ዘርፍ ምክትል ሚኒስትሮች እና የሶማሌ፣ የትግራይ፣ የኦሮሚያ፣ የአማራ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የንግድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንቶችን ያካተተ ነው ተብሏል።
ልዑኩ ዛሬ ሰኞ ዕለት በበርበራ ወደብ ባደረገው ጉብኝት፣ የወደብ አገልግሎቶችን፣ የጉምሩክ አሰራርን እንዲሁም ቁልፍ የትራንስፖርትና የሎጂስቲክስ መሠረተ ልማቶችን ተመልክቷል።
የሶማሊላንድ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ሞሐመድ ሀሰን ሳሌባን፣ የወደብ አገልግሎትንና የንግድ እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍ የተደረጉ ማሻሻያዎችን ለልዑኩ አስረድተዋል። ሚኒስትሩ አክለውም የበርበራ ወደብና ነፃ የንግድ ቀጠናው ቀጣናዊ የንግድ ትስስርን ለማሳደግ ያላቸውን ሚናም አብራርተዋል።
ወደቡን የሚያስተዳድረው የ #ዲ.ፒ_ወርልድ ኃላፊዎች በበኩላቸው ፣ የወደቡን የሥራ አቅም ለማሳደግና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን ለልዑኩ አስረድተዋል። በተጨማሪም በርበራን በአፍሪካ ቀንድ ተወዳዳሪ የሎጂስቲክስ ማዕከል ለማድረግ የታለሙ ሥራዎችን አፅንዖት ሰጥተው አብራርተዋል።
https://www.facebook.com/share/1FK8zgddLq/
የኢትዮጵያ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ልዑክ፣ በሶማሊላንድ የሚገኘውን የበርበራ ወደብ እና የበርበራ ነፃ የንግድ ቀጠናን መጎብኘቱን ባለሥልጣናት አስታወቁ።
ጉብኝቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።
ልዑኩ በኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ የተመራ ሲሆን የሶማሌ ክልል የኢንቨስትመንት፣ የትራንስፖርትና የንግድ ዘርፍ ምክትል ሚኒስትሮች እና የሶማሌ፣ የትግራይ፣ የኦሮሚያ፣ የአማራ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የንግድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንቶችን ያካተተ ነው ተብሏል።
ልዑኩ ዛሬ ሰኞ ዕለት በበርበራ ወደብ ባደረገው ጉብኝት፣ የወደብ አገልግሎቶችን፣ የጉምሩክ አሰራርን እንዲሁም ቁልፍ የትራንስፖርትና የሎጂስቲክስ መሠረተ ልማቶችን ተመልክቷል።
የሶማሊላንድ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ሞሐመድ ሀሰን ሳሌባን፣ የወደብ አገልግሎትንና የንግድ እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍ የተደረጉ ማሻሻያዎችን ለልዑኩ አስረድተዋል። ሚኒስትሩ አክለውም የበርበራ ወደብና ነፃ የንግድ ቀጠናው ቀጣናዊ የንግድ ትስስርን ለማሳደግ ያላቸውን ሚናም አብራርተዋል።
ወደቡን የሚያስተዳድረው የ #ዲ.ፒ_ወርልድ ኃላፊዎች በበኩላቸው ፣ የወደቡን የሥራ አቅም ለማሳደግና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን ለልዑኩ አስረድተዋል። በተጨማሪም በርበራን በአፍሪካ ቀንድ ተወዳዳሪ የሎጂስቲክስ ማዕከል ለማድረግ የታለሙ ሥራዎችን አፅንዖት ሰጥተው አብራርተዋል።
https://www.facebook.com/share/1FK8zgddLq/
ትራምፕ #ግብፅ እና #ሶማሊያን ጨምሮ በ15 የአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ አምባሳደሮቻቸውን ወደ ዋሽንግተን ጠሩ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግብፅ እና ሶማሊያን ጨምሮ በ15 የአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ አምባሳደሮቻቸውን ወደ ሀገራቸው ጠርተዋል።
እርምጃው ያልተለመደ ነው የተባለ ሲሆን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በውጭ ሀገራት ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ውክልና መልሳ ለማዋቀር የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ተብሏል።
በዲፕሎማሲያዊ ማኅበረሰብ ምንጮች እየተዘዋወረ ባለው መረጃ መሠረት፣ አሜሪካ አምባሳደሮቿን ወደ ሀገሯ የጠራችባቸው የአፍሪካ ሀገራት ዝርዝር የተለያዩ የአህጉሪቱን ቀጠናዎች ያካተተ ነው።
ዝርዝሩ በሰሜን አፍሪካ የሚገኙትን #ግብፅ እና #አልጄሪያን ጨምሮ በ #አፍሪካ_ቀንድ፣ በ #ምስራቅ፣ በ #ምዕራብ፣ በ #መካከለኛውና በ #ደቡባዊ_አፍሪካ የሚገኙ ሀገራትን ያጠቃልላል።
አምባሳደሮቹ እንዲመለሱ ስለተደረገበት ምክንያት እስካሁን የተሰጠ ይፋዊ ማብራሪያ የለም የተባለ ሲሆን፤ ክፍት የሆኑትን የሥራ መደቦች ለመተካት ግልጽ የሆነ የጊዜ ሰሌዳ አለመቀመጡም ተመላክቷል።
ውሳኔው በአፍሪካ ቀንድ በሶማሊያ የሚገኙ የአሜሪካ አምባሳደርን እንደሚመለከት የተነገረ ሲሆን ቀጠናው በዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች መተላለፊያነቱ፣ በአሜሪካ የጦር ሰፈር መገኘት እና በፀረ-ሽብር ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ ለዋሽንግተን ስልታዊ ፋይዳ ያለው አካባቢ መሆኑ ተጠቁሟል።
ተጨማሪ:-
https://www.facebook.com/share/1EaochTddW/
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግብፅ እና ሶማሊያን ጨምሮ በ15 የአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ አምባሳደሮቻቸውን ወደ ሀገራቸው ጠርተዋል።
እርምጃው ያልተለመደ ነው የተባለ ሲሆን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በውጭ ሀገራት ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ውክልና መልሳ ለማዋቀር የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ተብሏል።
በዲፕሎማሲያዊ ማኅበረሰብ ምንጮች እየተዘዋወረ ባለው መረጃ መሠረት፣ አሜሪካ አምባሳደሮቿን ወደ ሀገሯ የጠራችባቸው የአፍሪካ ሀገራት ዝርዝር የተለያዩ የአህጉሪቱን ቀጠናዎች ያካተተ ነው።
ዝርዝሩ በሰሜን አፍሪካ የሚገኙትን #ግብፅ እና #አልጄሪያን ጨምሮ በ #አፍሪካ_ቀንድ፣ በ #ምስራቅ፣ በ #ምዕራብ፣ በ #መካከለኛውና በ #ደቡባዊ_አፍሪካ የሚገኙ ሀገራትን ያጠቃልላል።
አምባሳደሮቹ እንዲመለሱ ስለተደረገበት ምክንያት እስካሁን የተሰጠ ይፋዊ ማብራሪያ የለም የተባለ ሲሆን፤ ክፍት የሆኑትን የሥራ መደቦች ለመተካት ግልጽ የሆነ የጊዜ ሰሌዳ አለመቀመጡም ተመላክቷል።
ውሳኔው በአፍሪካ ቀንድ በሶማሊያ የሚገኙ የአሜሪካ አምባሳደርን እንደሚመለከት የተነገረ ሲሆን ቀጠናው በዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች መተላለፊያነቱ፣ በአሜሪካ የጦር ሰፈር መገኘት እና በፀረ-ሽብር ተግባራት ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ ለዋሽንግተን ስልታዊ ፋይዳ ያለው አካባቢ መሆኑ ተጠቁሟል።
ተጨማሪ:-
https://www.facebook.com/share/1EaochTddW/
ዜና፡ በ #ትግራይ #ህጻፅ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ በርካታ ተፈናቃዮች ለከፋ ረሃብና ለሞት አደጋ መጋለጣቸው ተገለፀ
በትግራይ ክልል ህጻፅ መጠለያ ጣቢያ በሚገኙ በርካታ ተፈናቃዮች እየተባባሰ በመጣ የረሃብ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ። በከፋ የምግብ እጥረትና በውስን የህክምና አገልግሎት ምክንያት ተደጋጋሚ ሞት እየተመዘገበ መሆኑንና በርካታ ሰዎች በአስከፊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ዘገባዎች አመላክተዋል።
በክልሉ መገናኛ ብዙሃን ባወጡት ዘገባ መሠረት፣ ከሐምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በምግብ እጥረት ምክንያት ቢያንስ 50 ተፈናቃዮች ህይወታቸው አልፏል። ወደ 1,700 የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ ለተመሳሳይ አደጋ ተጋልጠዋል። አረጋውያን፣ ሴቶችና ህጻናት ዋነኛ ተጎጂዎች ሲሆኑ፣ ነዋሪዎች ለቀናት የሚበሉት በማጣታቸው ምክንያት ተዳክመው እንደሚወድቁ ተገልጿል።
ከምዕራብ ትግራይ ተፈናቅለው በህጻፅ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ቤተሰቦች ለመገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት፣ የምግብና የመድኃኒት እጥረት ሰዎች እንዲሞቱ ምክንያት ሆኗል።
የሚቀርብላቸው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነና አልፎ አልፎ የሚሰጣቸው 15 ኪሎ ግራም እህል መሰረታዊ ፍላጎታቸውን እንደማያሟላም ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ አክለውም፣ እህሉን ለማስፈጨትና ለሌሎች አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች ወጪም ለመሸፈን ግማሹን እህል ለመሸጥ እንደሚገደዱ ተናግረዋል። በተጨማሪም የሚቀርበው የእህል ዓይነት ለህጻናት፣ ለአረጋውያንና ለታመሙ ሰዎች ለመመገብ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምዕራብ ትግራይ አስተዳዳሪ አቶ ግደይ አዘናው ከ50 በላይ ተፈናቃዮች መሞታቸውን አረጋግጠዋል። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ከ300 በላይ ተፈናቃዮች ህይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጸው፣ አስቸኳይ ጣልቃ ገብነት ካልተደረገ ተጨማሪ የሰው ህይወት ሊጠፋ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የችግሩን አሳሳቢነት በመግለጽ መግለጫ አውጥተዋል፤ ለአብነትም የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ( #ኢሕአፓ) ትናንት ታህሳስ13 ቀን ባወጣው መግለጫ፤ “ከጦርነት የተረፉ ንጹሀን በረሀብ እየተገረፉ መሆኑ ትልቅ የሰብዓዊነት ልሽቀት ነው!” ሲል ገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10192
በትግራይ ክልል ህጻፅ መጠለያ ጣቢያ በሚገኙ በርካታ ተፈናቃዮች እየተባባሰ በመጣ የረሃብ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ። በከፋ የምግብ እጥረትና በውስን የህክምና አገልግሎት ምክንያት ተደጋጋሚ ሞት እየተመዘገበ መሆኑንና በርካታ ሰዎች በአስከፊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ዘገባዎች አመላክተዋል።
በክልሉ መገናኛ ብዙሃን ባወጡት ዘገባ መሠረት፣ ከሐምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በምግብ እጥረት ምክንያት ቢያንስ 50 ተፈናቃዮች ህይወታቸው አልፏል። ወደ 1,700 የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ ለተመሳሳይ አደጋ ተጋልጠዋል። አረጋውያን፣ ሴቶችና ህጻናት ዋነኛ ተጎጂዎች ሲሆኑ፣ ነዋሪዎች ለቀናት የሚበሉት በማጣታቸው ምክንያት ተዳክመው እንደሚወድቁ ተገልጿል።
ከምዕራብ ትግራይ ተፈናቅለው በህጻፅ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ቤተሰቦች ለመገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት፣ የምግብና የመድኃኒት እጥረት ሰዎች እንዲሞቱ ምክንያት ሆኗል።
የሚቀርብላቸው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነና አልፎ አልፎ የሚሰጣቸው 15 ኪሎ ግራም እህል መሰረታዊ ፍላጎታቸውን እንደማያሟላም ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ አክለውም፣ እህሉን ለማስፈጨትና ለሌሎች አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች ወጪም ለመሸፈን ግማሹን እህል ለመሸጥ እንደሚገደዱ ተናግረዋል። በተጨማሪም የሚቀርበው የእህል ዓይነት ለህጻናት፣ ለአረጋውያንና ለታመሙ ሰዎች ለመመገብ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምዕራብ ትግራይ አስተዳዳሪ አቶ ግደይ አዘናው ከ50 በላይ ተፈናቃዮች መሞታቸውን አረጋግጠዋል። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ከ300 በላይ ተፈናቃዮች ህይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጸው፣ አስቸኳይ ጣልቃ ገብነት ካልተደረገ ተጨማሪ የሰው ህይወት ሊጠፋ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የችግሩን አሳሳቢነት በመግለጽ መግለጫ አውጥተዋል፤ ለአብነትም የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ( #ኢሕአፓ) ትናንት ታህሳስ13 ቀን ባወጣው መግለጫ፤ “ከጦርነት የተረፉ ንጹሀን በረሀብ እየተገረፉ መሆኑ ትልቅ የሰብዓዊነት ልሽቀት ነው!” ሲል ገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10192
Addis standard
በትግራይ ህጻፅ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ በርካታ ተፈናቃዮች ለከፋ ረሃብና ለሞት አደጋ መጋለጣቸው ተገለፀ - Addis standard
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14/ 2018 ዓ/ም፦ በትግራይ ክልል ህጻፅ መጠለያ ጣቢያ በሚገኙ በርካታ ተፈናቃዮች እየተባባሰ በመጣ የረሃብ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ። በከፋ የምግብ እጥረትና በውስን የህክምና አገልግሎት ምክንያት ተደጋጋሚ ሞት እየተመዘገበ መሆኑንና በርካታ ሰዎች በአስከፊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ዘገባዎች አመላክተዋል። በክልሉ መገናኛ ብዙሃን ባወጡት ዘገባ መሠረት፣ ከሐምሌ 2017 ዓ.ም…
ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶች እገዳ ከጥር 23 ቀን ጀምሮ ተግባራዊ ሊደረግ ነው ተባለ
በአካባቢ ላይ የሚደርሰውን ብክለት ለመቀነስ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን ማምረት፣ መጠቀምና ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሕግ እንደሚያስቀጣ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ።
በባለሥልጣኑ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዴስክ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ዓለሙ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚከለክለው አዋጅ ከሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጸደቀ ቢሆንም ፣ ባለሥልጣኑ ለባለድርሻ አካላትና ለአምራቾች የስድስት ወራት የሽግግር ጊዜ ሰጥቶ መቆየቱን አውስተዋል።
አዋጁ በወጣበት ወቅት የወረቀትና ሌሎች አማራጭ ከረጢቶች ወደ ገበያ በመምጣታቸው የፕላስቲክ ስርጭት ቀንሶ እንደነበር ያነሱት ኃላፊው ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶች በድጋሚ በገበያው ውስጥ በስፋት መስተዋላቸዉን ገልጸዋል።
አክለውም ባለሥልጣኑ አዋጁን ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልፀው፣ ከአምራቾችና ከተጠቃሚዎች ጋር ውይይት መደረጉንም ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ አማራጭ የወረቀት ከረጢቶችን ለማምረት ለሚፈልጉ አካላት፣ የማምረቻ ማሽኖችን ከቀረጥ ነፃ ማስገባት አንዲችሉና የብድር አቅርቦት እንዲመቻች ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
የሽግግር ጊዜዉ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያበቃ የገለጹት ኃላፊው ፣ ከዚህ ዕለት በኋላ ስስ የፕላስቲክ ከርጢቶችን የሚያመረቱ፣ ወደ ሀገር የሚያስገቡና ይዘው የሚገኙ ኣካላት በህግ ተጠያቂ ይሆናሉ ሲሉ ማስጠንቀቃቸዉን የዘገበው ኢፕድ ነው።
በአካባቢ ላይ የሚደርሰውን ብክለት ለመቀነስ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን ማምረት፣ መጠቀምና ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሕግ እንደሚያስቀጣ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ።
በባለሥልጣኑ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዴስክ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ዓለሙ ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚከለክለው አዋጅ ከሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጸደቀ ቢሆንም ፣ ባለሥልጣኑ ለባለድርሻ አካላትና ለአምራቾች የስድስት ወራት የሽግግር ጊዜ ሰጥቶ መቆየቱን አውስተዋል።
አዋጁ በወጣበት ወቅት የወረቀትና ሌሎች አማራጭ ከረጢቶች ወደ ገበያ በመምጣታቸው የፕላስቲክ ስርጭት ቀንሶ እንደነበር ያነሱት ኃላፊው ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶች በድጋሚ በገበያው ውስጥ በስፋት መስተዋላቸዉን ገልጸዋል።
አክለውም ባለሥልጣኑ አዋጁን ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልፀው፣ ከአምራቾችና ከተጠቃሚዎች ጋር ውይይት መደረጉንም ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ አማራጭ የወረቀት ከረጢቶችን ለማምረት ለሚፈልጉ አካላት፣ የማምረቻ ማሽኖችን ከቀረጥ ነፃ ማስገባት አንዲችሉና የብድር አቅርቦት እንዲመቻች ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
የሽግግር ጊዜዉ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያበቃ የገለጹት ኃላፊው ፣ ከዚህ ዕለት በኋላ ስስ የፕላስቲክ ከርጢቶችን የሚያመረቱ፣ ወደ ሀገር የሚያስገቡና ይዘው የሚገኙ ኣካላት በህግ ተጠያቂ ይሆናሉ ሲሉ ማስጠንቀቃቸዉን የዘገበው ኢፕድ ነው።