በአዲስ አበባ የተሽከርካሪ የጭስ ብክለት ልቀት መጠን ደረጃ የአፈጻጸም መመሪያ ተዘጋጀ
*************
መመሪያውን ያዘጋጀው የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በሰነዱ ዙሪያ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።
ማንኛውም አሽከርካሪ የተሽከርካሪውን የጭስ ብክለት ልቀት መጠን በወጣው ደረጃ (ስታንዳርድ) አሟልቶ መንቀሳቀስ እንዳለበት በተዘጋጀው መመሪያ ተመላክቷል።
አሽከርካሪዎች የተሽከርካሪን የጭስ ብክለት ልቀት መጠን ሊቀንሱ የሚችሉ አማራጭ የቴክኖሎጂ ወጤቶችን ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባቸው ተጠቅሷል።
የተሽከርካሪውን የጭስ ብክለት ልቀት መጠን በየዓመቱ የማስመርመር ግዴታ እንዳለባቸውም ተጠቁሟል።
ድንገተኛ የጭስ ብክለት ልቀት መጠን ፍተሻ በሚደረግበት ጊዜም ተሽከርካሪውን የማስመርመር ግዴታ እንዳለባቸው ተመላክቷል።
የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ በውይይ መድረኩ እንደገለጹት፥ መመሪያው ከተሽከርካሪ የሚወጣውን የጭስ ብክለት ለመቀነስ የሚያስችል ነው።
ሰነዱ በዘርፉ ፍትኃዊና ተጠያቂነት ያለበት፣ ግልጽና ቀልጣፋ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያግዝ መሆኑንም ነው የጠቆሙት።
ይህም የአየር ብክለትን በመከላከል በጤና ላይ የሚደርሰውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለማስቀረት እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የበካይ ጋዝ ልቀት መቀነሻ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተሽከርካሪዎችን የነዳጅ ፍጆታ ለመቀነስ እንደሚያግዝም ገልጸዋል።
ይህም የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ወጪ ለመቀነስ እንደሚያስችልም ጠቁመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
*************
መመሪያውን ያዘጋጀው የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በሰነዱ ዙሪያ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።
ማንኛውም አሽከርካሪ የተሽከርካሪውን የጭስ ብክለት ልቀት መጠን በወጣው ደረጃ (ስታንዳርድ) አሟልቶ መንቀሳቀስ እንዳለበት በተዘጋጀው መመሪያ ተመላክቷል።
አሽከርካሪዎች የተሽከርካሪን የጭስ ብክለት ልቀት መጠን ሊቀንሱ የሚችሉ አማራጭ የቴክኖሎጂ ወጤቶችን ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባቸው ተጠቅሷል።
የተሽከርካሪውን የጭስ ብክለት ልቀት መጠን በየዓመቱ የማስመርመር ግዴታ እንዳለባቸውም ተጠቁሟል።
ድንገተኛ የጭስ ብክለት ልቀት መጠን ፍተሻ በሚደረግበት ጊዜም ተሽከርካሪውን የማስመርመር ግዴታ እንዳለባቸው ተመላክቷል።
የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ በውይይ መድረኩ እንደገለጹት፥ መመሪያው ከተሽከርካሪ የሚወጣውን የጭስ ብክለት ለመቀነስ የሚያስችል ነው።
ሰነዱ በዘርፉ ፍትኃዊና ተጠያቂነት ያለበት፣ ግልጽና ቀልጣፋ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያግዝ መሆኑንም ነው የጠቆሙት።
ይህም የአየር ብክለትን በመከላከል በጤና ላይ የሚደርሰውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለማስቀረት እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የበካይ ጋዝ ልቀት መቀነሻ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተሽከርካሪዎችን የነዳጅ ፍጆታ ለመቀነስ እንደሚያግዝም ገልጸዋል።
ይህም የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ወጪ ለመቀነስ እንደሚያስችልም ጠቁመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
👍24❤8👎5👏1
የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ3ኛው የብሪክስ አባል ሀገራት ተወካዮች ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው
***********
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እና በብሪክስ የኢትዮጵያ ዋና ተወካይ አቶ ማሞ ምህረቱ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ በሩስያ በጀመረው 3ኛው የብሪክስ የአባል ሀገራት ተወካዮች ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
አቶ ማሞ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር፥ በተለዋዋጭ እና ሊተነበይ በማይቻል የዓለም ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ ብሪክስ ሀገራትን እና ሃብቶችን በማሰባሰብ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን በአጋርነት መንፈስ ለመቅረፍ አረጋጊ ኃይል ሆኖ ሊያገለግል እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ የብሔራዊ የብሪክስ ተሳትፎ ስትራቴጂን በብሔራዊ የሚኒስትሮች አስተባባሪ ኮሚቴ ማፅደቋን ጨምሮ ወደ ብሪክስ ማዕቀፍ በተሳለጠ ሁኔታ መግባቷን ለማረጋገጥ የተወሰዱ እርምጃዎችንም አብራርተዋል።
በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ቱሪስት ፍሰትና ሌሎች መስኮች ያለውን የኢኮኖሚ ግንኙነት ማሳደግ እንደሚገባ እንዲሁም የልማት ፋይናንስን በመጨመር አካታች እና ዘላቂ ልማትን መደገፍ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
አዲሱ የልማት ባንክ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ከኢትዮጵያ የልማት ትልሞች ጋር የተጣጣሙ በመሆናቸው ኢትዮጵያ በተቻለ ፍጥነት ወደ ባንኩ ትቀላቀላለች ብለው እንደሚጠብቁም ተናግረዋል።
ስብሰባው ከሰኔ 3-4 ቀን 2016 ዓ.ም ለሚካሄደው የብሪክስ አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ግብዓት የሚሆኑ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከር መቀጠሉን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
***********
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እና በብሪክስ የኢትዮጵያ ዋና ተወካይ አቶ ማሞ ምህረቱ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ በሩስያ በጀመረው 3ኛው የብሪክስ የአባል ሀገራት ተወካዮች ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
አቶ ማሞ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር፥ በተለዋዋጭ እና ሊተነበይ በማይቻል የዓለም ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ ብሪክስ ሀገራትን እና ሃብቶችን በማሰባሰብ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን በአጋርነት መንፈስ ለመቅረፍ አረጋጊ ኃይል ሆኖ ሊያገለግል እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ የብሔራዊ የብሪክስ ተሳትፎ ስትራቴጂን በብሔራዊ የሚኒስትሮች አስተባባሪ ኮሚቴ ማፅደቋን ጨምሮ ወደ ብሪክስ ማዕቀፍ በተሳለጠ ሁኔታ መግባቷን ለማረጋገጥ የተወሰዱ እርምጃዎችንም አብራርተዋል።
በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ቱሪስት ፍሰትና ሌሎች መስኮች ያለውን የኢኮኖሚ ግንኙነት ማሳደግ እንደሚገባ እንዲሁም የልማት ፋይናንስን በመጨመር አካታች እና ዘላቂ ልማትን መደገፍ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
አዲሱ የልማት ባንክ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ከኢትዮጵያ የልማት ትልሞች ጋር የተጣጣሙ በመሆናቸው ኢትዮጵያ በተቻለ ፍጥነት ወደ ባንኩ ትቀላቀላለች ብለው እንደሚጠብቁም ተናግረዋል።
ስብሰባው ከሰኔ 3-4 ቀን 2016 ዓ.ም ለሚካሄደው የብሪክስ አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ግብዓት የሚሆኑ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከር መቀጠሉን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍54❤23👏6
“ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሉዓላዊ ሀገርነት” በሚል መሪ ሀሳብ በደሴ ከተማ ህዝባዊ ውይይት መካሄድ ጀምሯል
**************
“ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሉዓላዊ ሀገርነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው በደሴ ከተማ ህዝባዊ ውይይት መካሄድ ጀምሯል፡፡
የህዝባዊ ውይይቱን እየመሩ ያሉት የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ደሴ እንደ ስሟ የነበራትን የገናናነት ታሪክ እንደምትመለስ አሁን ላይ ያለችበት ልማትና የአመራር አሰላለፍ አመላካች ነው ሲሉ ገልፀዋል።
የልማት እንቅስቃሴዎችን ቀጣይነትን ማረጋገጥ ይገባል ከተረጂነት በሙሉ በመላቀቅ ሰርቶ መቀየርን ባህል ማድረግ ያስፈልጋልም ነው ያሉት፡፡
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው ህዝቡ በራሱ ሰርቶ በመለወጥ ከተረጂነት አስተሳሰብ የመውጣት ባህልን ሊያጎለብት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ፓርቲው ብልፅግናና መንግስት ተረጂነትን ወደ ትውልድ ማሸጋገር አለብን በማለት አቋም ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በደሴ ከተማ የአስፓልት መንገድን ጨምሮ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ተገንብተው የተጠናቀቁና በመሰራት ላይ ናቸው መሆናቸውን የደሴ ከተማተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው ህዝቡ በሰከነ መንገድ ነገሮችን በመመርመር ቅድሚያ ሰላሙን እያስጠበቀ የልማት ተሳትፎውን በማረጋገጥ የመንግስትና የህዝብ ትስስሩን እንዲጠናክር አሳስበዋል፡፡በህዝባዊ መድረኩ ላይ ከክልል ከዞን እና ከከተማው የተውጣጡ አመራሮች የተሳተፉበት ነው፡፡
በይመር አደም
**************
“ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሉዓላዊ ሀገርነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው በደሴ ከተማ ህዝባዊ ውይይት መካሄድ ጀምሯል፡፡
የህዝባዊ ውይይቱን እየመሩ ያሉት የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ደሴ እንደ ስሟ የነበራትን የገናናነት ታሪክ እንደምትመለስ አሁን ላይ ያለችበት ልማትና የአመራር አሰላለፍ አመላካች ነው ሲሉ ገልፀዋል።
የልማት እንቅስቃሴዎችን ቀጣይነትን ማረጋገጥ ይገባል ከተረጂነት በሙሉ በመላቀቅ ሰርቶ መቀየርን ባህል ማድረግ ያስፈልጋልም ነው ያሉት፡፡
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ በበኩላቸው ህዝቡ በራሱ ሰርቶ በመለወጥ ከተረጂነት አስተሳሰብ የመውጣት ባህልን ሊያጎለብት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ፓርቲው ብልፅግናና መንግስት ተረጂነትን ወደ ትውልድ ማሸጋገር አለብን በማለት አቋም ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በደሴ ከተማ የአስፓልት መንገድን ጨምሮ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች ተገንብተው የተጠናቀቁና በመሰራት ላይ ናቸው መሆናቸውን የደሴ ከተማተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው ህዝቡ በሰከነ መንገድ ነገሮችን በመመርመር ቅድሚያ ሰላሙን እያስጠበቀ የልማት ተሳትፎውን በማረጋገጥ የመንግስትና የህዝብ ትስስሩን እንዲጠናክር አሳስበዋል፡፡በህዝባዊ መድረኩ ላይ ከክልል ከዞን እና ከከተማው የተውጣጡ አመራሮች የተሳተፉበት ነው፡፡
በይመር አደም
👍26❤5
የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄዎች ሆነው ምላሽ እንዲያገኙ ጥረት እየተደረገ ነው፡- አቶ ደስታ ሊዳሞ
******************************
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድ አቶ ደስታ ሌዳሞ ከብልፅግና ፓርቲ አመራሮች እና የባሕር ዳር ከተማ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ከባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ኢትዮጵያውያን የሰላምን ዋጋን ጠንቅቀው የሚረዱ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ የአማራ ክልልን ሰላም ወደ ነበረበት ለመመለስ ህዝቡ እና መንግሥት በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በባሕር ዳር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራትን ተዘዋውረው ማየታቸውን የተናገሩት አቶ ደስታ፣ ልማቶቹ ተጠናክሩው መቀጠል እንዳለባቸውም ጠቁመዋል።
የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ ሆኖ ምላሽ ያገኛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ለዚህም የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
የአማራ ህዝብን ጥያቄ ሰላማዊ ባልሆነ መንገድ ለማሳካት የሚሞክሩ ኃይሎች ከዚህ ድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ ደስታ፣ ይህ አካሄድ የአማራ ህዝብን የሚጎዳ እና ጥያቄዎቹም እንዳይመለሱ እንቅፋት የሚፈጥር ነው ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ኢትዮጵያ ብሔሮችና ብሔረሰቦች በጋራ ተባብረው የገነቧት ብዝሃነት የሚታይባት ሀገር ናት ብለዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0uGpogi7RCbot9JHzGnVHiA1fvgDu5KoY8X2RigRLPBW8RRjxXEZnazBCA37GKZhFl
******************************
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድ አቶ ደስታ ሌዳሞ ከብልፅግና ፓርቲ አመራሮች እና የባሕር ዳር ከተማ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ከባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ኢትዮጵያውያን የሰላምን ዋጋን ጠንቅቀው የሚረዱ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ የአማራ ክልልን ሰላም ወደ ነበረበት ለመመለስ ህዝቡ እና መንግሥት በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በባሕር ዳር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራትን ተዘዋውረው ማየታቸውን የተናገሩት አቶ ደስታ፣ ልማቶቹ ተጠናክሩው መቀጠል እንዳለባቸውም ጠቁመዋል።
የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ ሆኖ ምላሽ ያገኛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ለዚህም የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
የአማራ ህዝብን ጥያቄ ሰላማዊ ባልሆነ መንገድ ለማሳካት የሚሞክሩ ኃይሎች ከዚህ ድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ ደስታ፣ ይህ አካሄድ የአማራ ህዝብን የሚጎዳ እና ጥያቄዎቹም እንዳይመለሱ እንቅፋት የሚፈጥር ነው ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ኢትዮጵያ ብሔሮችና ብሔረሰቦች በጋራ ተባብረው የገነቧት ብዝሃነት የሚታይባት ሀገር ናት ብለዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0uGpogi7RCbot9JHzGnVHiA1fvgDu5KoY8X2RigRLPBW8RRjxXEZnazBCA37GKZhFl
👍27👎9❤3👏1
"ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነት እና ክብር" በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ የህዝብ መድረክ እየተካሄደ ነው
**********************
መድረኩን የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ፣ የአፋር ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኤሌማ አቡበከር እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ እየመሩ ይገኛሉ።
በአካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ከህብረተሰቡ ጋር መወያየት የመድረኩ ዓላማ እንደሆነ ተገልጿል ።
በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን እና የከተማ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከከተማው የተለያዩ የማኅበራዊ መሠረቶች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎችም እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
በትዕግስቱ ቡቼ
**********************
መድረኩን የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ፣ የአፋር ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኤሌማ አቡበከር እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ እየመሩ ይገኛሉ።
በአካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ከህብረተሰቡ ጋር መወያየት የመድረኩ ዓላማ እንደሆነ ተገልጿል ።
በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን እና የከተማ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከከተማው የተለያዩ የማኅበራዊ መሠረቶች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎችም እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
በትዕግስቱ ቡቼ
👍40❤2
በመዲናዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለክልሎችም ተሞክሮ የሚሆኑ ናቸው - አቶ አረጋ ከበደ
********************
በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለክልሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ እና የግብርና ሚኒስትሩ ከጎበኟቸው ፕሮጀክቶች መካከል፤ የለሚ ኩራ የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከል፣ የእንስሳት ልማት እና ልህቀት ማዕከል፣ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶ እና ማበልፅጊያ ማዕከል እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች እና ታላላቅ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ርዕሰ መሥተዳድሩ ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡት የልማት ስራዎች የኑሮ ውድነቱን ከማቃለል አንጻር ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ማመላከታቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
********************
በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለክልሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ እና የግብርና ሚኒስትሩ ከጎበኟቸው ፕሮጀክቶች መካከል፤ የለሚ ኩራ የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከል፣ የእንስሳት ልማት እና ልህቀት ማዕከል፣ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶ እና ማበልፅጊያ ማዕከል እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች እና ታላላቅ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ርዕሰ መሥተዳድሩ ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡት የልማት ስራዎች የኑሮ ውድነቱን ከማቃለል አንጻር ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ማመላከታቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍30❤5👎1