ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶን ተቀበሉ
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶን ተቀብለዋል።
#PMOEthiopia
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶን ተቀብለዋል።
#PMOEthiopia
❤40👍16🔥7👏3🤣1
የፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጉብኝት በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዛሬ የኬንያ ፕሬዚደንት ዊልያም ሳሞይ ሩቶን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት መቀበላቸውን ገልጸዋል።
ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጥልቅ፣ ታሪካዊ እና ወንድማዊ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
በውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን አመልክተዋል።
ይህም በሰላም እና መረጋጋት፣ ብሎም በአፍሪካ መር መፍትሔዎች ላይ ያለንን የወል ጽኑ አቋም የሚያሳይ ነበር ሲሉ ገልጸዋል።
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዛሬ የኬንያ ፕሬዚደንት ዊልያም ሳሞይ ሩቶን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት መቀበላቸውን ገልጸዋል።
ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጥልቅ፣ ታሪካዊ እና ወንድማዊ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
በውይይቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን አመልክተዋል።
ይህም በሰላም እና መረጋጋት፣ ብሎም በአፍሪካ መር መፍትሔዎች ላይ ያለንን የወል ጽኑ አቋም የሚያሳይ ነበር ሲሉ ገልጸዋል።
❤21👍11🔥2
የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዱራህማን ሩቤ ሥርዓተ ቀብር ተፈፀመ
******
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት የአቶ አብዱራህማን ሩቤ ሥርዓተ ቀብር በኮልፌ የሙስሊም መካነ መቃብር ተፈፅሟል።
አቶ አብዱራህማን ሩቤ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ40 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አቶ አብዱራህማን በኢቢሲ እና በኦቢኤን ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት ያገለገሉ ሲሆን ሕይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስም የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ ነበር፡፡
አቶ አብዱራህማን ሩቤ ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት ነበሩ፡፡
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሥራ ባልደረቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብዱራህማን ሩቤ ኅልፈት የተሰማውን ኀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል።
በላሉ ኢታላ
******
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት የአቶ አብዱራህማን ሩቤ ሥርዓተ ቀብር በኮልፌ የሙስሊም መካነ መቃብር ተፈፅሟል።
አቶ አብዱራህማን ሩቤ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ40 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አቶ አብዱራህማን በኢቢሲ እና በኦቢኤን ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት ያገለገሉ ሲሆን ሕይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስም የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ ነበር፡፡
አቶ አብዱራህማን ሩቤ ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት ነበሩ፡፡
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሥራ ባልደረቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብዱራህማን ሩቤ ኅልፈት የተሰማውን ኀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል።
በላሉ ኢታላ
❤18😢18
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በጤናው ዘርፍ በአጋርነት መሥራት የሚያስችል የ1.6 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙ
**************
የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ መንግሥታት በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር የ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የጤና ትብብር ማዕቀፍ ተፈራርመዋል።
የትብብር ስምምነቱ በዘላቂ ልማት፣ በጋራ ኢንቨስትመንትና የጤና ሥርዓትን በማጠናከር ላይ ያተኮረ የኢትዮ-አሜሪካ አዲስ የጤና አጋርነት ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል።
የትብብር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ፈርመውታል።
የኢትዮጵያና የአሜሪካ የጤና የአጋርነት ስምምነት ለ5 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ የትብብር ማዕቀፉ በኤችአይቪ/ኤድስ፣ ቲቢ፣ ወባ፣ የእናቶች እና ህጻናት ጤና፣ የወረርሽኝ ምላሽ እና ዝግጁነትን የነበረውን ድጋፍ ለማስቀጠል እንዲሁም የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት የበለጠ ለማጠናከር ድጋፍ ለማድረግ ያቀደ ነው።
በኤዶሚያስ ንጉሴ
**************
የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ መንግሥታት በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር የ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የጤና ትብብር ማዕቀፍ ተፈራርመዋል።
የትብብር ስምምነቱ በዘላቂ ልማት፣ በጋራ ኢንቨስትመንትና የጤና ሥርዓትን በማጠናከር ላይ ያተኮረ የኢትዮ-አሜሪካ አዲስ የጤና አጋርነት ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል።
የትብብር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ፈርመውታል።
የኢትዮጵያና የአሜሪካ የጤና የአጋርነት ስምምነት ለ5 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ የትብብር ማዕቀፉ በኤችአይቪ/ኤድስ፣ ቲቢ፣ ወባ፣ የእናቶች እና ህጻናት ጤና፣ የወረርሽኝ ምላሽ እና ዝግጁነትን የነበረውን ድጋፍ ለማስቀጠል እንዲሁም የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት የበለጠ ለማጠናከር ድጋፍ ለማድረግ ያቀደ ነው።
በኤዶሚያስ ንጉሴ
❤35👍7🔥3👏2
ማስታወቂያ
*******
የልጅነት ሕልምዎን እና የወጣትነት አላማዎ የተሳካ እንዲሆን የሲንቄ ባንክ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግሎት በመጠቀም የኖሩለትን ራዕይ እውን ያድርጉ።
#Siinqee_Bank #Baankii_Siinqee #ሲንቄ_ባንክ #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan #Financial_Inclusion #EMPOWERED_TOGETHER
*******
የልጅነት ሕልምዎን እና የወጣትነት አላማዎ የተሳካ እንዲሆን የሲንቄ ባንክ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግሎት በመጠቀም የኖሩለትን ራዕይ እውን ያድርጉ።
#Siinqee_Bank #Baankii_Siinqee #ሲንቄ_ባንክ #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan #Financial_Inclusion #EMPOWERED_TOGETHER
❤11
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከሚሊዮኖች ጋር ትውውቅ የሚፈጥሩበትን ልዩ አጋጣሚ ይጠቀሙ
************
በኢቢሲ አዝናኝ የገና በዓል ዝግጅቶቻችን ላይ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ።
ለበለጠ መረጃ ወደ
📲 0968979797
📲 0947959595
ይደውሉ
************
በኢቢሲ አዝናኝ የገና በዓል ዝግጅቶቻችን ላይ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ።
ለበለጠ መረጃ ወደ
📲 0968979797
📲 0947959595
ይደውሉ
❤6