EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) – Telegram
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
138K subscribers
38.2K photos
458 videos
80 files
13.1K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
አምባሳደር ገነት ተሾመ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አቀረቡ
*****************

በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ለሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አቅርበዋል።

ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር ጠንካራ ወዳጅነት እና የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዳላት ገልጸዋል።

ሩሲያ በቅርቡ በካዛን ከተማ 16ተኛውን የብሪክስ መሪዎች ጉባኤ በስኬት ማጠናቀቋንና የሩሲያ-አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን ስብስባን ለማስተናገድ ዝግጅት ማጠናቀቋን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ሩሲያ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሰብዓዊ ጉዳዮች ከአጋር እና ወዳጅ አገራት ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጅት መሆኗን ፑቲን መግለጻቸውን በሩሲያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
👍427
የኤ350-1000 አውሮፕላን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬታማ ጉዞ ማሳያ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
****************

የኤ350-1000 አውሮፕላን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬታማ ጉዞ ማሳያ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ተናገሩ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 124 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ማዘዙን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡

ይህም አየር መንገዱ በተፋጠነ የስኬት ጉዞ ላይ መሆኑን የሚያመላክት እርምጃ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

በዚህም አየር መንገዱ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላንን ትናንት ከኤርባስ ኩባንያ የተረከበ ሲሆን፤ በዛሬው እለትም አውሮፕላኑ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፤ ኤ350-1000 አውሮፕላን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬታማ ጉዞ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02z3D8s8CkyjUkpQRJuj253wC7tH5hS7J7UN1gKn2tVa2umUJqpdtdzoeSA8zT6zmpl
👍211
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን የቡና ምርት
👍5113
የጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር አማዱ ኡሪ ባህ አዲስ አበባ ገቡ
**********************

የጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር አማዱ ኡሪ ባህ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው "የጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር አማዱ ኡሪ ባህ እንኳን ወደ ኢትዮጵያ መጡ እላለሁ" ብለዋል።

#etv #ኢቲቪ #ኢቢሲ #ዐቢይአሕመድ #Guinea #TheRepublicofGuinea
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02xA7Jsts1NpT1sB3yWUU3WYHBV6JnzRFSXLF5kBcWC3N6eMuCgBzTkW5XYaF56zrrl
👍183
ትራምፕ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን እየመሩ ነው
******************

የአለም ፖለቲካ ዘዋሪዋ ሀገር አሜሪካ 47ተኛውን ፕሬዝዳንቷን በመምረጥ ላይ ትገኛለች።

ፉክክሩ የጋለው እና እጩዎቹ አንገት ለአንገት የተያያዙበት ምርጫ ውጤት በዚህ ሰዐት የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ እየመሩ ይገኛሉ።

የዲሞክራቷ እጩ ካማላ ሀሪስም ሆኑ ሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ ለሀገራቸው ይበጃል ብለው የያዟቸው ፖሊሲዎች አሜሪካውያንና የቀረውን አለም ቀልብ ስቦ የምርጫውን ውጤት አለም በጉጉት እንዲከታተል አድርጎታል።

እስከመጨረሻ ውጤቱን ለመገመት አስቸጋረ የሚሆነው 47ተኛው የአሜሪካ ምርጫ ፉክክር ማንን ፕሬዝዳንት ያደርግ ይሆን?
አሁንም የሁለቱን ፉክክር እና ውጤት ለማወቅ "ስዊንግ ስቴት" የሚባሉትን 7 ግዛቶች የምርጫ ውጤት መጠበቅ አስገዳጅ ነው።

ካማላ ሀሪስ እስካሁን በብዙ ሴቶች በመመረጥ ቅድሚያውን ቢይዙም በአጠቃላይ የምርጫ ሂደቱ በሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ትራምፕ እየተመሩ ይገኛሉ።

አሁን ላይ ባለው መረጃ ትራምፕ ምርጫውን የማሸነፍ ዕድላቸው ወደ 89% ከፋ ማለቱ እየተዘገበ ነው::

በናርዶስ አዳነ
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0KCyGkjCneLH2FSW7h6aXeDNFwHm7QowbrpUpHpdEwvETxZVeREkDa2XDxp9Vnxfql
👍368👏3