Event Addis Media – Telegram
Event Addis Media
9.62K subscribers
6.11K photos
13 videos
4 files
4.73K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌የደጃፍ ፖድካስት ምዕራፍ ሶስት ነገ ይጀምራል።

በዳዊት ተስፋዬ የሚዘጋጀውና በበርካቶች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው "ደጃፍ ከዳዊት ተስፋዬ ጋር" የፖድካስት ዝግጅት ምዕራፍ ሶስቱ ነገ ሐሙስ ታህሳስ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

የምዕራፍ ሶስት ክፍል አንድ እንግዳ በመሆን በቅርቡ "አንድ ቃል" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች ያደረሰው ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በእንግድነት ይቀርባል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ተወዳጇ አርቲስት መሠረት መብራቴ በሎስአንጀለስ ሲቲ ካውንስል ተሸለመች።

በተለያዩ ፊልሞች፣ ቴአትሮች እና በማስታወቂያ ስራዎቿ አድናቆት የተቸራት፤ ጎን ለጎንም በምታበረክተው የበጎ አድራጎት አገልግሎት የበርካቶችን አክብሮትና ፍቅርን የተጎናፀፈችው አርቲስት መሠረት መብራቴ
በሎስአንጀለስ ከተማ Los Angeles city council እና U.S  Africa institute በጋራ ባዘጋጁት “Humanitarian Waward” የካውንስሉ አባላት በተገኙበት የእውቅና እና የክብር ሽልማት ተበርክቶላታል።

ካውንስሉ አርቲስቷ ለኢትዮጵያ የህፃት የልብ ህሙማን መርጃ ማእከል በበጎ ፈቃድ አምባሳደርነት እየሰጠች ያለውን አገልግሎት በማክበር በተለይም በአሜሪካን ሀገር የነበራትን  የተሳካ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር በመጥቀስ የተለየ እውቅና እንደሚሰጠውና ለዚህ አገልግሎቷም አክብሮት እንዳለው በመግለፅ የእውቅናና የክብር ሰርተፊኬት አበርክቶላታል።

Via ሔሎ ኢትዮጵያ

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ተወዳጁ "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ነገ አርብ በዓለም ሲኒማ በክብር ከመድረክ ይሰናበታል

ከአስር ዓመት በኃላ በድጋሚ ባሳለፍነው ዓመት ግንቦት 2 2016 ዓ.ም በዓለም ሲኒማ ወደ መድረክ የተመለሰው "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ነገ አርብ  ታህሳስ 4 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ በክብር ከመድረክ ይሰናበታል ተብሏል።

በአርቲስት ወይንሸት አበጀ ፕሮዲዩስ የተደረገው ይህ "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ድርሰትና ዝግጅቱ የአለልኝ መኳንንት ፅጌ ነው።

በተውኔቱ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ሚኪ ተስፋዬ ፣ ወይንሸት አበጀ ፣አሸናፊ ማህሌት በተዋናይነት ተሳትፉበታል።ተውኔቱም ዘወትር አርብ አመሻሽ ላይ ሲቀርብ ቆይቷል ።

በአርቡ የመዝጊያው መርሐግብር ላይ የቴአትር ወዳጆች እንድትገኙላቸው አዘጋጆቹ ጋብዘዋል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌መቅረዝ ሥነኪን ዝግጅት ዛሬ ይካሄዳል

አንጋፋ እና ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎችን እያጣመር የዘለቀው መቅረዝ ሥነኪን ወርሀዊ የኪነጥበብ  ዝግጅት ዛሬ ሐሙስ ታህሣሥ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር )አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

በዚህ ኪነጥበባዊ ዝግጅት ላይ አርክቴክት ሚካኤል ሽፈራው የክብር እንግዳ በመሆን የሚገኘ ሲሆን በተጨማሪም ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎች የግጥም ፣የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።

የዚህ ዝግጅት መግቢያ በነፃ ነው።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የቀን ለውጥ..

ውድ ቤተሰቦቻችን ለታህሳስ 5 የነበረው ቀጠሮአቸን ለታህሳስ 12,2017 ዓ.ም እንደተላለፈ ስናሳውቅ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው።

- በልባችሁ የፃፋችሁት የፍቅር ታሪክ ምንድነው?

- የህይወት መንገዳችሁ በትዳር እንዲሆን ከወሰናችሁ በኋላ የፍቅር ግንኙነት ለመጀመር ስታስቡ  "ትክክለኛው" ሰው ብላችሁ በልባችሁ ያሰባችሁት ሰው ለምን የለም?

- ያለፈው ያልተሳካው  የፍቅር ግንኙነት ለምን አልተሳካም? በልባችን ምንስ ጥሎ  አለፈ?

- የፍቅር ግንኙነት ከመጀመር በፊት እራሴ ጋር ምን ልጨርስ?

-በትክክል የምፈልገው ምንድነው?

ካነበብናቸው መፅሐፍት፣ከሰማናቸው ታሪኮች፣ሙዚቃዎች፣ካደግንበት ማህበረሰብ፣ከኖርነው ኑሮ፣ካልተሳኩ የፍቅር ግንኙነት/ቶች ተነስተን በልባችን የፃፍነው የፍቅር ታሪክ አለን።

- በፍቅር ግንኙነት መንገድ ላይ ከሚመጣው ሰው ጋር ይህን በልባችን የሰራነውን የፍቅር ታሪክ እንኖረዋለን።

እነዚህን ጉዳዮች እንመክርባቸው ዘንድ ቅድመ ጥምረት የተሰኘ  አስደሳች፣ መስተጋብራዊ እና ግንዛቤ የሚያስጨብጥ የስልጠና ፕሮግራም አዘጋጆተናል።

ስልጠናው የግንኙነት አቅምን ለማወቅ እና ለጤናማ፣ አስደሳች እና ዘላቂ አጋርነት የሚያስፈልጎትን  ክህሎቶች ለመማር የሚረዳ  የስልጠና ፕሮግራም ነው።
 
ካልተሳካ የፍቅር አዙሪት ለመላቀቅ ፣ እዉነተኛ የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ለመግባት እና ለዘላቂ ግንኙነት ጠንካራ መሰረት ለመገንባት አሁኑኑ ይደውሉ ...0946-444445
ቀን :-ቅዳሜ፣ታህሳስ 12/2017 ዓ.ም
ቦታ :- ሲ ኤም ሲ ሚካኤል ኢትዮጵያን ኢኮኖሚክ አሶሴሽን አዳራሽ
መግቢያ ዋጋ :-300 ብር ብቻ

       ኑ ና ለፍቅር ተዘጋጁ!!
ኦሲስ ሥልጠናና ማማከር ማዕከል
https://news.1rj.ru/str/+ESVZ5qsyls9lODJk

📌Ads
📌"ቀይ ካርድ" ፊልም ዛሬ ለእይታ በቃ።

በኖላዊ ፊልም ፕሮዳክሽን የተሰናዳው የየአብስራ ዶጮ "ቀይ ካርድ" የተሰኘው ሀገርኛ ፊልም  ዛሬ ታህሳስ 4 2017 ዓ.ም በሁሉም ሲኒማ ቤቶች ለእይታ በቅቷል።

"ቀይ ካርድ" የተሰኘው ፊውቸር ፊልም አንጋፋ እና አዳዲስ ተዋንያን የተሳተፉበት በድርጊት የታጀበ ልብ አንጠልጣይ የወንጀል ፊልም እንደሆነ ተገልጿል።

ቃልኪዳን ጥበቡ ፣ኤርሚያስ ታደሰ ፣ይሄነው አበበ ፣አንተነህ ጌታቸው እና ሌሎችም በትወና ተሳትፉበውታል።

1:30 ረዝማኔ ያለው ፊልሙ ሁለት አመት የፈጀ ሲሆን በአጠቃላይ ከ3 ሚልየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል።

"ቀይ ካርድ" ፊልሙ ውስጥ ባሉ ገፀ ባህሪያት የተፈጠረ እራሱን የቻለ ምናባዊ የፍትህ ስርዓት ሲሆን በዋናነት የሚያጠነጥነው በአንድ መስሪያ ቤት ውስጥ የተፈፀመን ሚስጥራዊ የወንጀል ታሪክ ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የሚጋጥመውን ውጣውረድ እና ካለፈ ህይወት ጋር የሚደረግ የአይምሮ ግጭትን የሚያሳይ ተጨባጫ እውነት ላይ ያተኮረ በድርጊት የታጀበ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ነው
ሲል የፊልሙ አዘጋጅ የአብስራ ዶጮ ለአርትስ ቴሌቪዥን ገልጿል።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ደራሲ አዳም ረታ ከደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ጋር ያደረጉት ሥነጽሑፋዊ ውይይት ተለቀቀ

አንጋፋው ደራሲ አዳም ረታ ከደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ጋር "በነገረ-መጻሕፍት" ልዩ ዝግጅት ያካሄዱት ሥነጽሑፋዊ ውይይት በእንዳለጌታ ከበደ መልቲሚዲያ ዩቲዩብ ቻናል በኩል ለተመልካች ቀርቧል።

በዚህ ከአንድ ሠዓት በላይ በወሰደው ውይይት ላይ በርካታ ሥነጽሑፍ ጉዳዮች ተነስተዋል።

ደራሲ አዳም ረታ እንዲህ ዓይነት ረጅም ቃለመጠይቅ ሲያደርግ ከበርካታ ዓመታት በኃላ ይህ የመጀመሪያው ነው።

ሙሉ ውይይቱን በዚህ ሊንክ መከታተል ትችላላችሁ:

https://youtu.be/MpI5r6JjCwY?si=E2mtRmmWciKWPYO0


ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የየሺህ ጋብቻ ብራንድ አምባሳደሮች

አርቲስት ተስፋዓለም ታምራትና ቃልኪዳን አበራ እንዲሁም አርቲስት ይገረም ደጀኔ እና ፅዮን ዮሴፍ የዘንድሮው የ"የሺህ ጋብቻ" የጋብቻ ፌስቲቫል ብራንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል።

በያሜንት ኤቨንትስ የሚዘጋጀው "የሺህ ጋብቻ" የዘንድሮው የጋብቻ ሥነሥርዓት ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል ተብሏል።

ዘንድሮ ከሀገር ውስጥ 1ሺህ ጥንዶችን እንዲሁም 250 የሚደርሱ ጥንዶችን ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በማካተት በአጠቃላይ ከ1250 በላይ ጥንዶች የፊታችን ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጋብቻቸውን ይፈፀማሉ።

በዚህ ግዙፍ የጋብቻ ሥነሥርዓት በተለየ መልኩ ከሚኖሩ ክንውኖች መካከል ከ25 ሺህ በላይ የቡና ሲኒ እንዲሁም 2017 ኪ.ግ የሚመዝን ባህላዊ ዳቦ ለታዳሚዎች  ይቀርባል ተብሏል።

ሁነቱንም በዓለም ድቃድንቅ መዝገብ ላይ እንዲስፍር ለማድረግ የሚሠራበት ታላቅ ዝግጅት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የሺህ ጋብቻ ትልቅ ዓላማ የኢትዮጵያን እንዲሁም የአፍሪካ ሀገራት ህዝቦችን የካበተ ባህላዊ የሰርግ ሥነ-ሥርዓት አጉልቶ በማሳየት አዲስ አበባን የሃኒሙን ማዕከል ማድረግ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጿል።

አጠቃላይ ለዚህ ፕሮጀክት ዕውን መሆን ያስፈልጋል ተብሎ የታቀደው በጀት 68,997,500 ብር እንደሆነ ተነግሯል።

"የሺህ ጋብቻ"  ከዚህ ቀደም በ2005 እና በ2016 ዓ.ም ስኬታማ የብዙኃን  ጋብቻዎችን አከናውኗል።

የጋብቻ ፌስቲቫሉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የፎቶግራፍ አውደርዕይ በሳይንስ አካዳሚ

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል ከአዲስ አበባ ፎቶግራፍ ባለሙያዎች ማኅበር ጋር በመተባበር የፎቶግራፍ አውደርዕይ አዘጋጅቷል፡፡

በዚህ አውደርዕይ ታዋቂ ባለሙያዎች አንቶኒዮ ፍዮሬንቴ፣ ሙሉጌታ አየነ፣ ማኅደር ኃይለሥላሴ፣ ናሆም ተስፋዬና ሚካኤል ጸጋዬ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡

አውደርዕዩ ቅዳሜ ታህሳስ 12 2017 ዓ.ም 10፡00 ላይ በአካዳሚው ሙዚየም በይፋ ይከፈታል፡፡ እርስዎም በአክብሮት እንዲገኙ ተጋብዘዋል፡፡

የዝግጅቱ ቦታ:- በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል፡፡
ከፒያሳ ወደ ውንጌት መስመር በሚወስደው ጎዳና - ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ -
በተለምዶ ወረዳ ስምንት ተብሎ በሚጠራው ቀጭን መንገድ 500 ሜትር ገባ ብሎ
ወይንም ንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል
https://maps.app.goo.gl/GwKfjcwg1jmqsfG76

ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡፡
https://news.1rj.ru/str/+VZQIhKm-NoAwYjM0

ለተጨማሪ መረጃ በ0911838281 ይደውሉ

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በደራሲ ሕይወት ተፈራ "ተድባብ" መጽሐፍ ላይ የፊታችን ቅዳሜ ዳሰሳና ውይይት ይካሄዳል

ልዩ መርሐግብር:- የመፅሐፍ ዳሰሳ እና ውይይት

የመፅሐፉ ደራሲ :- ሕይወት ተፈራ

ዳሰሳ አቅራቢዎች :
1.በድሉ ዋቅጅራ /ዶክተር ደራሲ ገጣሚ /
2.ይኩኖአምለክ መዝገቡ / ወመዘክር ዳይሬክተር/
3.ተስፋዬ እሸቱ /ተባባሪ ኘሮፌሰር/
4.ሀብቱ ግርማ /ጋዜጠኛ/
5. ኤፍሬም ስዩም (ገጣሚ እና ደራሲ)

የፕሮግራም አወያይ :- መሰረት አበጀ /መምህር/

ለውይይት የተመረጠው መጽሐፍ:- ተድባብ

የመርሐግብሩ አሰናጅ:- ዋልያ መጻሕፍት

ቦታ:- አራት ኪሎ ዋልያ መጻሕፍት አዳራሽ ውስጥ

ቀን:- ቅዳሜ: ታህሳስ 12 2017 ዓ. ም : ጠዋት ከ4:00 እስከ 6:30 ድረስ::

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📌የኢሳት ቲቪ ዜና አንባቢ ከስራ ታገደች

ሰሞኑን የኢሳት ቴሌቪዥን የዜና አንባቢ ትዕግሥት ተስፋዬ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቆሴ ወረዳ የተመለከተ ዜና ስታነብ ቆሴ የሚለውን ስም ለመጥራት ሲያስቸግራት ያለውን ቪዲዮ በቲክቶክ ገጿ ላይ በመለጠፍ የተለያዩ ትችቶችን ስታስተናግድ ነበር።

ኢሳት ቴሌቪዥን ይህን ተመልክቶ ዜና አንባቢዋን እና የተቆረጠውን ቪዲዮ አሳልፎ የሰጣትን ባልደረባ ከስራ ማገዱ ተሰምቷል።

ዜና አንባቢዋ በማህበራዊ ትስስር ገጿ ይቅርታ መጠይቋ ይታወቃል።

📍መረጃው የፋስት መረጃ ነው።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
🤣1
📌የጃዋር መሐመድ መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል

የፖለቲከኛ ጃዋር መሐመድ "HIN GAABBU" ወይንም "አልፀፀትም" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው መጽሐፍ ዛሬ ሐሙስ በፈረንጆች  December 19,2024 በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር ታህሳስ 10 2017 ዓ.ም በኬንያ ናይሮቢ ይመረቃል ተብሏል።

መጽሐፉ ከኬንያ ናይሮቢ በተጨማሪም በተለያዩ ሀገራት እንደሚመረቅም ኤቨንት አዲስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ዋዋጎ ትውፊታዊ ተውኔት ለመድረክ ሊበቃ ነው

በታረቀኝ ብርሃኑ ተደርሶ በጥላሁን ዘውገ የተዘጋጀው "ዋዋጎ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ ትውፊታዊ ተውኔት ለመድረክ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በዚህ ትውፊታዊ ተውኔት ላይ  ተስፋዬ ይማም፣በፍቃዱ ከበደ፣ ጥላሁን ዘውገ ፣ወይንሸት አበጀ እና ሌሎችም እንደሚተውኑበት ተገልጿል።ተውኔቱም አርብ ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ለመድረክ እንደሚበቃ ተገልጿል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ቅደመ ጥምረት ለመገናኘት መዘጋጀት"የተሰኘ ልዩ የፍቅር ግንኙነት ስልጠና ቅዳሜ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ይካሄዳል።

- በልባችሁ የፃፋችሁት የፍቅር ታሪክ ምንድነው?

- የህይወት መንገዳችሁ በትዳር እንዲሆን ከወሰናችሁ በኋላ የፍቅር ግንኙነት ለመጀመር ስታስቡ  "ትክክለኛው" ሰው ብላችሁ በልባችሁ ያሰባችሁት ሰው ለምን የለም?

- ያለፈው ያልተሳካው  የፍቅር ግንኙነት ለምን አልተሳካም? በልባችን ምንስ ጥሎ  አለፈ?

- የፍቅር ግንኙነት ከመጀመር በፊት እራሴ ጋር ምን ልጨርስ?

-በትክክል የምፈልገው ምንድነው?

ካነበብናቸው መፅሐፍት፣ከሰማናቸው ታሪኮች፣ሙዚቃዎች፣ካደግንበት ማህበረሰብ፣ከኖርነው ኑሮ፣ካልተሳኩ የፍቅር ግንኙነት/ቶች ተነስተን በልባችን የፃፍነው የፍቅር ታሪክ አለን።

-በፍቅር ግንኙነት መንገድ ላይ ከሚመጣው ሰው ጋር ይህን በልባችን የሰራነውን የፍቅር ታሪክ እንኖረዋለን።

እነዚህን ጉዳዮች እንመክርባቸው ዘንድ ቅድመ ጥምረት የተሰኘ  አስደሳች፣ መስተጋብራዊ እና ግንዛቤ የሚያስጨብጥ የስልጠና ፕሮግራም አዘጋጆተናል።

ስልጠናው የግንኙነት አቅምን ለማወቅ እና ለጤናማ፣ አስደሳች እና ዘላቂ አጋርነት የሚያስፈልጎትን  ክህሎቶች ለመማር የሚረዳ  የስልጠና ፕሮግራም ነው።
 
ካልተሳካ የፍቅር አዙሪት ለመላቀቅ ፣ እዉነተኛ የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ለመግባት እና ለዘላቂ ግንኙነት ጠንካራ መሰረት ለመገንባት አሁኑኑ ይደውሉ ...0946-444445
ቀን :-ቅዳሜ፣ታህሳስ 12/2017 ዓ.ም
ሠዓት:ከቀኑ 8:00 ጀምሮ
ቦታ :- ሲ ኤም ሲ ሚካኤል ኢትዮጵያን ኢኮኖሚክ አሶሴሽን አዳራሽ
መግቢያ ዋጋ :-300 ብር ብቻ

       ኑ ና ለፍቅር ተዘጋጁ!!
ኦሲስ ሥልጠናና ማማከር ማዕከል
https://news.1rj.ru/str/+ESVZ5qsyls9lODJk

📌Ads
📌የጃዋር መሐመድ መጽሐፍ ምርቃት ተሰረዘ

ጃዋር መሐመድ 'አልጸጸትም' በሚል ርዕስ ዛሬ ሐሙስ ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በናይሮቢ ሊያስመርቀው የነበረው መጽሐፍ ከተለያዩ አካላት በደረሱ ማስፈራሪያዎች እና ዛቻዎች ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

ረቡዕ፣ ታህሳስ 9/ 2017 ዓ.ም ይፋዊ የሆነ ዛቻ/ተቃውሞ ከኢትዮጵያ መንግሥት መድረሱን እኚሁ ምንጭ ገልጸዋል።

ፖለቲከኛው ጃዋር መሐመድ በኬንያ መዲና ናይሮቢ ዛሬ ሐሙስ ታሕሳስ 10 2017 ዓ.ም. ሊካሄድ የነበረው የመፅሐፍ ምርቃት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ አስታውቋል ሲል ቢቢሲ አማርኛ ነው የዘገበው።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የቀለም ጨዋታ" ፊልም ዛሬ ለእይታ ይበቃል

በብርሃኑ መብሬ ተደርሶ በኪሩቤል ስዩም የተዘጋጀው "የቀለም ጨዋታ" የተሰኘ አዲስ ፊልም ዛሬ ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በተለያዩ ሲኒማ ቤቶች ለእይታ ይበቃል።

"የቀለም ጨዋታ" ፊልም አንድ ዓመት ከ4 ወር በላይ ጊዜን የወሰደ ሲሆን  ደረጄ ሀይሌ፣ሙሉዓለም ጌታቸዉ፣ሱራፌል ብስራት፣አለምፀሀይ እሸቱ፣ተመስገን ሚካኤል፣ ሳባ ታደሰን ጨምሮ ከ85 ተዋናኒያን እንደተሳተፉበት ተገልጿል።

በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተሰራው "የቀለም ጨዋታ" ፊልም ታህሳስ 11፣12 ፣13 እና 18፣19፣20 በተመረጡ ሲኒማ ቤቶች መታየት ይጀምራል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የድምጻዊ ፍቃዱ ትዕዛዙ "ባለውለታዬ" የሙዚቃ ቪዲዮ ዛሬ ይለቀቃል

የቀደሞ ድምጻዊ ተፈራ ነጋሽ የሙዚቃ ስራዎችን በድጋሚ የተጫወተውና "ዘንድሮ" በሚል ርዕስ በአልበም መልክ ለአድማጮች ያደረሰው ድምጻዊ ፍቃዱ ትዕዛዙ "ባለውለታዬ" የሙዚቃ ቪዲዮውን ዛሬ ታህሥሥ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ለአድማጮች ያደርሳል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የሜላት ቀለመወርቅ ነጠላ ሙዚቃ ዛሬ ይለቀቃል

የድምጻዊት ሜላት ቀለመወርቅ "ዜሮ" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ዛሬ ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በራሷ ዩቲዩብ ቻናል ለአድማጮች ይደርሳል።

ድምጻዊት ሜላት በማህበራዊ ትስስር ገጿ"አዲሱን የሙዚቃ ቪድዮ  ስራዬን በራሴ ዩትዩብ ቻናል ወደናንተ አደርሳለው። ሁሌም በስራዎቼ ስለምታበረታቱኝ በጣም አመሰግናለው" ብላለች።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አውደ ፋጎስ" የውይይት መድረክ ነገ ይካሄዳል

52ኛው ዙር አውደ ፋጎስ የውይይት መድረክ እሁድ ይካሄዳል። በዚህኛው ዙር ዮናስ ታረቀኝ " ፍራንስ ካፋካንና ሥራዎቹን በጨረፍታ" በሚል ርዕስ መነሻ ሀሳብ ያቀርባል።

ይህም ውይይት እሁድ ታህሣሥ 13 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አግልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

ለተጨማሪው:Tiktok:https://www.tiktok.com/@eventaddis1?_t=8rbUqppyscx&_r=1

Telegram: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በአርቲስት ዘነበች ታደሰ"ጭራ ቀረሽ" ህይወትና ሥራ ላይ ያተኮረ መፅሀፍ ዛሬ ይመረቃል።

በሀገራችን በቴያትርና ሙዚቃ ዘርፍ በሁለገብ ሙያተኛነት ደምቀው ሲያበሩ ከነበሩ ከያኒያኒን መካከል አንዷ የነበረችው አርቲስት ዘነበች ታደሰ (ጭራ ቀረሽ) ሕይወትና ስራዎች ላይ የሚያጠንጥን መጽሐፍ ዛሬ ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓ.ም ለንባብ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ሰምቷል።

በዶ/ር ጌታቸው ተድላ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ አርቲስት ዘነበች ታደሰ ማን ነች? ለምንስ ጭራ ቀረሽ የሚል ስያሜ ተሰጣት? ለጥበብ ምን አበረከተች? የሚሉ ጥያቄዎችን ሊመልስ የሚችል በፅሁፍና በምስል የተደራጀ መፅሐፍ  እንደሆነ ተገልጿል።

አርቲስት ዘነበች ታደሰ  'ሎሚ ብወረውር' በሚለው ዘፈኗና በመድረክ ላይ ውዝዋዜዋ ይበልጡን በህዝብ ልብ ውስጥ የምትታወስ ትሁን እንጂ ጥቂት በማይባሉ የመድረክ ቴያትሮችና የቴሌቪዥን ድራማ ብሎም ፊልም ላይ  በመሳተፍ አቅሟን አሳይታለች።

ለአብነት ያህል (Shaft in Africa) ላይ ከታዋቂው የሆሊዉድ ተዋናይ ሪቻርድ ራውንድትሪ ጋር የመተወን እድል ሲገጥማት በጥሩ ብቃት የተሰጣትን ሚና ለመወጣት የቻለች ብቁ ሙያተኛ ነበረች።

'ጭራ ቀረሽ' የሚል ርዕስ የተሰጠው ይህ መፅሀፍ  ዛሬ ታህሳስ 12 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተመርቆ ለንባብ ይበቃል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1