📌የአዲስ ጌራ "ወዳጅ" ሙዚቃ ዛሬ ይለቀቃል
የወጣቷ ድምጻዊት አዲስ ጌራ "ወዳጅ" የተሰኘ አዲስ ሙዚቃ ዛሬ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም በራሷ የዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃል ተብሏል።
የሙዚቃው ግጥምና ዜማ በራሷ በድምጻዊዋ የተሰራ ሲሆን በሙዚቃ ቅንብር ሀብታሙ ነጋሽ በሚክሲንግና ማስተሪንግ ኤንዲ ቤተ ዜማ ተሳትፈውበታል።
የሙዚቃ ቪዲዮው ዳይሬክተር ዘመን እሸቱ ነው።
ድምጻዊት አዲስ ጌራ ከዚህ ቀደም "ማን ያውቃል " እና "መስከረሜ" የተሰኙ ሙዚቃዎችን ለአድማጮች አድርሳለች።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የወጣቷ ድምጻዊት አዲስ ጌራ "ወዳጅ" የተሰኘ አዲስ ሙዚቃ ዛሬ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም በራሷ የዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃል ተብሏል።
የሙዚቃው ግጥምና ዜማ በራሷ በድምጻዊዋ የተሰራ ሲሆን በሙዚቃ ቅንብር ሀብታሙ ነጋሽ በሚክሲንግና ማስተሪንግ ኤንዲ ቤተ ዜማ ተሳትፈውበታል።
የሙዚቃ ቪዲዮው ዳይሬክተር ዘመን እሸቱ ነው።
ድምጻዊት አዲስ ጌራ ከዚህ ቀደም "ማን ያውቃል " እና "መስከረሜ" የተሰኙ ሙዚቃዎችን ለአድማጮች አድርሳለች።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የአስቻለው ፈጠነ አዲስ ሙዚቃ በተለቀቀ በአጭር ቀናት ውስጥ ከአንድ ሚሊየን በላይ እይታን አገኘ
የድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ(አርዲ) "አሞራው ካሞራ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ ሙዚቃ በብርቧክስ ሪከርድስ ዩቲዩብ ቻናል በተለቀቀ በሁለት ቀናት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን እይታ እንዳገኘ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።
አስቻለው ፈጠነ (አርዲ) ከዚህ ቀደም "እናትዋ ጎንደር" እና "ካሲናው ጎጃም" በተሰኙ ሙዚቃዎች ከፍተኛ ተደማጭነትን አግኝቷል።
በተጨማሪም ባሳለፍነው ዓመት ጥር ወር በለቀቀው "አስቻለ" የሙዚቃ አልበም ተወዳጅነትን አትርፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ(አርዲ) "አሞራው ካሞራ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ ሙዚቃ በብርቧክስ ሪከርድስ ዩቲዩብ ቻናል በተለቀቀ በሁለት ቀናት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን እይታ እንዳገኘ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።
አስቻለው ፈጠነ (አርዲ) ከዚህ ቀደም "እናትዋ ጎንደር" እና "ካሲናው ጎጃም" በተሰኙ ሙዚቃዎች ከፍተኛ ተደማጭነትን አግኝቷል።
በተጨማሪም ባሳለፍነው ዓመት ጥር ወር በለቀቀው "አስቻለ" የሙዚቃ አልበም ተወዳጅነትን አትርፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ተወዳጁ "ዘ-ገሊላ" ሙዚቃ 20 ዓመት ሞላው
የበርካቶች ትዝታ የሆነውና የጥምቀት ሰሞን የቴሌቪዥንና ሬድዮ ጣቢያዎች የሚቀባበሉት የድምጻዊ ይሁኔ በላይ "ዘ-ገሊላ" ሙዚቃ ዘንድሮ ድፍን 20 ዓመት ሞልቶታል። ይህ ተወዳጅና ዘመን አይሸሬ ሙዚቃ ለአድማጮች የደረሰው በ1997 ዓ.ም ነበር።
"ወርዉሬ መታሁት ጥላሽን በእምቧይ፣
ደሞ ባንች በኔ ከልካይ አለን ወይ።
ወደአንች ስመጣ ተመለስ የሚለኝ፣
ማን ይሆን ወገኛዉ የሚከለክለኝ።
***
ወንዞ አይፈሬዉ ቀሚስ የተሸነሸነዉ፣
ትፍትፉ መቀነት ወገቧን የዞረዉ፣
ልቤን በጉንፏ አዉሎ አሳደረዉ።
***
እንኳን ዛጎል ማርዳዉ አምባሩም መስቀሉ፣
ሽርብት አደሬ ማተብሽ ድንግሉ፣
አንችን ለማሳመር መች አነሰ ባሉ።"
ርዕስ: ዘገሊላ
ድምጻዊ: ይሁኔ በላይ
ግጥም: አቤል መልካሙ
ዜማ: አስቻለው አየለ
ሙዚቃ ቅንብር: ዳዊት ጥላሁን
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የበርካቶች ትዝታ የሆነውና የጥምቀት ሰሞን የቴሌቪዥንና ሬድዮ ጣቢያዎች የሚቀባበሉት የድምጻዊ ይሁኔ በላይ "ዘ-ገሊላ" ሙዚቃ ዘንድሮ ድፍን 20 ዓመት ሞልቶታል። ይህ ተወዳጅና ዘመን አይሸሬ ሙዚቃ ለአድማጮች የደረሰው በ1997 ዓ.ም ነበር።
"ወርዉሬ መታሁት ጥላሽን በእምቧይ፣
ደሞ ባንች በኔ ከልካይ አለን ወይ።
ወደአንች ስመጣ ተመለስ የሚለኝ፣
ማን ይሆን ወገኛዉ የሚከለክለኝ።
***
ወንዞ አይፈሬዉ ቀሚስ የተሸነሸነዉ፣
ትፍትፉ መቀነት ወገቧን የዞረዉ፣
ልቤን በጉንፏ አዉሎ አሳደረዉ።
***
እንኳን ዛጎል ማርዳዉ አምባሩም መስቀሉ፣
ሽርብት አደሬ ማተብሽ ድንግሉ፣
አንችን ለማሳመር መች አነሰ ባሉ።"
ርዕስ: ዘገሊላ
ድምጻዊ: ይሁኔ በላይ
ግጥም: አቤል መልካሙ
ዜማ: አስቻለው አየለ
ሙዚቃ ቅንብር: ዳዊት ጥላሁን
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ዛኘ" ነጠላ ሙዚቃ ተለቀቀ
የድምፃዊ ፈለቀ ማሩ ''ዛኘ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የጉራጊኛ ነጠላ ሙዚቃ በሪቦ አዲስ ዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮች ደርሷል።
የሙዚቃው ግጥም በፈለቀ ማሩ የተሰራ ሲሆን በሙዚቃ ቅንብር በኩል በኃይሉ ዘርይሁን ተሳትፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምፃዊ ፈለቀ ማሩ ''ዛኘ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የጉራጊኛ ነጠላ ሙዚቃ በሪቦ አዲስ ዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮች ደርሷል።
የሙዚቃው ግጥም በፈለቀ ማሩ የተሰራ ሲሆን በሙዚቃ ቅንብር በኩል በኃይሉ ዘርይሁን ተሳትፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የሕይወት ታሪክ" ተውኔት በልዩ ፕሮግራም ዛሬ ይቀርባል።
ድርሰቱ እና ዝግጅቱ የነብዩ ባዬ እና የቢንያም ወርቁ የሆነው "የሕይወት ታሪክ" አዲስ ተውኔት ዛሬ ጥር 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በልዩ ዝግጅት ይቀርባል።
ይህ ተውኔት ከዚህ ቀደም በሸገር ራዲዮ በሬድዮ ድራማ መልክ ቀረቡ የነበረ ሲሆን አሁን በመድረክ ተውኔት ቅርጽ ተሰርቷል ተብሏል።
በ"ሕይወት ታሪክ" በተውኔት ላይ ቢንያም ወርቁ እና ፀደይ ፋንታሁን ለሁለት ይተውናሉ።
ተውኔቱ በነባ ጥበባት እና ኮምኒኬሽን የቀረበ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ድርሰቱ እና ዝግጅቱ የነብዩ ባዬ እና የቢንያም ወርቁ የሆነው "የሕይወት ታሪክ" አዲስ ተውኔት ዛሬ ጥር 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በልዩ ዝግጅት ይቀርባል።
ይህ ተውኔት ከዚህ ቀደም በሸገር ራዲዮ በሬድዮ ድራማ መልክ ቀረቡ የነበረ ሲሆን አሁን በመድረክ ተውኔት ቅርጽ ተሰርቷል ተብሏል።
በ"ሕይወት ታሪክ" በተውኔት ላይ ቢንያም ወርቁ እና ፀደይ ፋንታሁን ለሁለት ይተውናሉ።
ተውኔቱ በነባ ጥበባት እና ኮምኒኬሽን የቀረበ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ አረፈ
አንጋፋው አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡አርቲስት እንቁስላሴ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሕይወቱ ማለፉን የአርቲስቱ ቤተሰቦች ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡
አርቲስት እንቁስላሴ 30 በሚሆኑ ፊልሞች እና ቴአትሮች ላይ በትወና በመሳተፍ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አገኝቷል፡፡
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡አርቲስት እንቁስላሴ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሕይወቱ ማለፉን የአርቲስቱ ቤተሰቦች ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡
አርቲስት እንቁስላሴ 30 በሚሆኑ ፊልሞች እና ቴአትሮች ላይ በትወና በመሳተፍ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አገኝቷል፡፡
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በፎቶግራፍ ጥበብ ላይ ሙያዊ ውይይት ተከናወነ
በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል ከአዲስ አበባ ፎቶግራፍ ባለሙያዎች ማኅበር ጋር በመተባበር "በፎቶግራፍ ጥበብና በለውጥ ሰበዞች" ዙሪያ ሙያዊ ውይይት ጥር 9 2017 ዓ.ም በአካዳሚው ውስጥ አከናውኗል።
በሙያዊ ውይይቱ ላይ የሥነጥበብ ባለሙያና ኲሬተር ቆንጅት ሥዩም፣ ማኅደረ ኃይለሥላሴ፣ ሙሉጌታ አየነ፣ አንቶኒዮ ፊዮሬንቴ እና ሚካኤል ፀጋዬ የተሳተፉ ሲሆን፣ ወ/ሮ ቆንጅት የውይይት ሐሳቦችን በማንሳትና ጥያቄዎችን በማጫር ውይይቱን አጋፍራለች።
ከታኅሳስ 12 2017 ዓ.ም አንስቶ ለሕዝብ ክፍት ሆኖ በቆየው "የለውጥ ሰበዞች" የተሰኘውን የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ መነሻ በማድረግ አራቱም ፎቶግራፈሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ስላገኟቸው ዕውቅናዎችና በሙያቸው ስላጋጠሟቸው ፈተናዎች በማንሳት ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡
አካዳሚውና ማኅበሩ ከታህሳስ 12 እስከ ጥር 9-2017 ድረስ ያሰናዱት ዐውደ ርዕይና ውይይት የፎቶግራፍ ጥበብ በሀገሪቱ እንዲጎለብት መሰል ዝግጅቶች እንዲቀጥሉ የሚያበረታታ መሆኑን ያነሱት ተሳታፊዎችና ተወያዮች ሰፊና ጥልቅ ሙያዊ ሀሳቦችን በማንሳት ደማቅ ተዋስዖ አድርገዋል።
Via የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ የሥነ-ጥበባት ማዕከል ከአዲስ አበባ ፎቶግራፍ ባለሙያዎች ማኅበር ጋር በመተባበር "በፎቶግራፍ ጥበብና በለውጥ ሰበዞች" ዙሪያ ሙያዊ ውይይት ጥር 9 2017 ዓ.ም በአካዳሚው ውስጥ አከናውኗል።
በሙያዊ ውይይቱ ላይ የሥነጥበብ ባለሙያና ኲሬተር ቆንጅት ሥዩም፣ ማኅደረ ኃይለሥላሴ፣ ሙሉጌታ አየነ፣ አንቶኒዮ ፊዮሬንቴ እና ሚካኤል ፀጋዬ የተሳተፉ ሲሆን፣ ወ/ሮ ቆንጅት የውይይት ሐሳቦችን በማንሳትና ጥያቄዎችን በማጫር ውይይቱን አጋፍራለች።
ከታኅሳስ 12 2017 ዓ.ም አንስቶ ለሕዝብ ክፍት ሆኖ በቆየው "የለውጥ ሰበዞች" የተሰኘውን የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ መነሻ በማድረግ አራቱም ፎቶግራፈሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ስላገኟቸው ዕውቅናዎችና በሙያቸው ስላጋጠሟቸው ፈተናዎች በማንሳት ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡
አካዳሚውና ማኅበሩ ከታህሳስ 12 እስከ ጥር 9-2017 ድረስ ያሰናዱት ዐውደ ርዕይና ውይይት የፎቶግራፍ ጥበብ በሀገሪቱ እንዲጎለብት መሰል ዝግጅቶች እንዲቀጥሉ የሚያበረታታ መሆኑን ያነሱት ተሳታፊዎችና ተወያዮች ሰፊና ጥልቅ ሙያዊ ሀሳቦችን በማንሳት ደማቅ ተዋስዖ አድርገዋል።
Via የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የኢትዮ ጃዝ ፈጣሪ የሆነው ሙላቱ አስታጥቄ ‹‹ሙዚቃ ሳይንስ ነው ስለዚህም ሳይንቲስቶቹን ማክበር ይገባናል›› ሲል ተናገረ፡፡
ሙላቱ ከፎርቹን ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ እንደገለፀው ሙዚቃ ልክ እንደኬሚስትሪ ሁሉ የተለያዩ ድምፆች ተደባልቀውና ተዋህደው ጣእመ ዜማን ይፈጥራሉ፡፡
ሲናገርም ‹‹አውሮፓዊያን ሙዚቃን እንደሳይንስ ይመለከቱታል፡፡ አስፕሪንን ለመፍጠር የተለያዩ ኬሜካሎችን እንደሚያዋህዱት ሁሉ ሙዚቃንም እንደሳይንስ ቆጥረው ጥልቅ ምርምር በማድረግ ሙዚቃን ያመርታሉ፡፡ ስለዚህም በሳይንስና በሙዚቃ መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡›› ብሏል፡፡ ጨምሮም አፍሪካዊያን ደግሞ ለሙዚቃ ግብአት የሚሆኑትን ለአውሮፓ እንደሚያበረክቱ አስረድቷል፡፡
በአንድ ወቅት የድሮው አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ከፍቶ እንደነበር ያወሳው ሙላቱ በተለያዩ ምክንያቶች መቀጠል እንዳልቻለ ጠቅሷል፡፡ ይሁንና በርካታ ልጆች በትክክለኛው መንገድ ላይ መሄድ አለመቻላቸው እንደሚያሳዝነው አስረድቶ ‹‹ሙዚቃ ሳይንስ ቢሆንም አፍሪካዊያን ግን እንደጊዜ ማሳለፊያና ለዳንስ ብቻ ይጠቀሙበታል›› ካለ በኋላ ሙዚቃ እንደማንኛውም ጥበብ የትምህርት ስርአቱ ውስጥ መካተት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ሙዚቃ በትምህርት ካሪኩለም ውስጥ ቢካተት ወጣቶች የሙዚቃን ሳይንስነት እንደሚረዱትም አስታውቋል፡፡
Via ዘሀበሻ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሙላቱ ከፎርቹን ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ እንደገለፀው ሙዚቃ ልክ እንደኬሚስትሪ ሁሉ የተለያዩ ድምፆች ተደባልቀውና ተዋህደው ጣእመ ዜማን ይፈጥራሉ፡፡
ሲናገርም ‹‹አውሮፓዊያን ሙዚቃን እንደሳይንስ ይመለከቱታል፡፡ አስፕሪንን ለመፍጠር የተለያዩ ኬሜካሎችን እንደሚያዋህዱት ሁሉ ሙዚቃንም እንደሳይንስ ቆጥረው ጥልቅ ምርምር በማድረግ ሙዚቃን ያመርታሉ፡፡ ስለዚህም በሳይንስና በሙዚቃ መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡›› ብሏል፡፡ ጨምሮም አፍሪካዊያን ደግሞ ለሙዚቃ ግብአት የሚሆኑትን ለአውሮፓ እንደሚያበረክቱ አስረድቷል፡፡
በአንድ ወቅት የድሮው አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ከፍቶ እንደነበር ያወሳው ሙላቱ በተለያዩ ምክንያቶች መቀጠል እንዳልቻለ ጠቅሷል፡፡ ይሁንና በርካታ ልጆች በትክክለኛው መንገድ ላይ መሄድ አለመቻላቸው እንደሚያሳዝነው አስረድቶ ‹‹ሙዚቃ ሳይንስ ቢሆንም አፍሪካዊያን ግን እንደጊዜ ማሳለፊያና ለዳንስ ብቻ ይጠቀሙበታል›› ካለ በኋላ ሙዚቃ እንደማንኛውም ጥበብ የትምህርት ስርአቱ ውስጥ መካተት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ሙዚቃ በትምህርት ካሪኩለም ውስጥ ቢካተት ወጣቶች የሙዚቃን ሳይንስነት እንደሚረዱትም አስታውቋል፡፡
Via ዘሀበሻ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ተወዳጁ ጋዜጠኛና ደራሲ ገነነ መኩሪያ ሊብሮ በሞት ከተለየ ዛሬ አንድ አመት ሆነው ።
ጋዜጠኛ ፥ ፀሀፊ ፥ ደራሲ ፥ ታሪክ አሻጋሪና ፥ የተራማጅ ሀሳብ ባለቤት ፥ እንዲሁም የአዲስ ሀሳቦች አፍላቂ የሆነው ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) በሞት ከተለየን ዛሬ አንድ ዓመት ሆነው።
የገነነ ቤተሰቦቹም " የገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ሞት ለታሪክ አድማጭና ፥ ለታሪክ አንባቢው ፥ ለታሪክ ነጋሪና ለታሪክ ተረካቢው እንዲሁም ሁሌም አዲስ ሀሳብና መንገድን ለሚናፍቀው ለሀገራችን የእግር ኳስ ስፖርት ትልቅ ሞት ሲሆን ከሁሉ በላይ ደግሞ ለእኛ ለቤተሰቦቹ ሀዘኑ በቃል የማይገለፅ እጅግ ከባድ ሀዘን ነው" ብለዋል።
የጋዜጠኛና ደራሲ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) የአንደኛ የሙት ዓመት መታሰቢያንም ነፍሱ ባረፈችበት በዛሬዋ ዕለት ኃይማኖታዊ ስርዓቱን በጠበቀ አካሄድ መሠረት በእንጦጦ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን በፀሎት እንደታሰበ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቤተሰቡ በተጨማሪ " እኛ ቤተሰቦቹ እርሱን ለማሰብም በቁስቋም ጌርጌሴኖን የመርጃና ማገገሚያ ማዕከል የሚገኙ ወገኖቻችንን በመመገብም እንዘክረዋለን" ብለዋል።
"የገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) እልፈት ከተሰማ ጀምሮ ሀዘናችንን ሀዘናችሁ አድርጋችሁ ከሀገር ውስጥም ይሁን ከውጪ ሀገር ያፅናናችሁን ወዳጆቹ በሙሉ ስለሁሉም ነገር በፈጣሪ ስም እጅግ አድርገን ዛሬም እናመሰግናችኋለን" ሲሉም ምስጋናቸውን አቅረበዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ጋዜጠኛ ፥ ፀሀፊ ፥ ደራሲ ፥ ታሪክ አሻጋሪና ፥ የተራማጅ ሀሳብ ባለቤት ፥ እንዲሁም የአዲስ ሀሳቦች አፍላቂ የሆነው ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) በሞት ከተለየን ዛሬ አንድ ዓመት ሆነው።
የገነነ ቤተሰቦቹም " የገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ሞት ለታሪክ አድማጭና ፥ ለታሪክ አንባቢው ፥ ለታሪክ ነጋሪና ለታሪክ ተረካቢው እንዲሁም ሁሌም አዲስ ሀሳብና መንገድን ለሚናፍቀው ለሀገራችን የእግር ኳስ ስፖርት ትልቅ ሞት ሲሆን ከሁሉ በላይ ደግሞ ለእኛ ለቤተሰቦቹ ሀዘኑ በቃል የማይገለፅ እጅግ ከባድ ሀዘን ነው" ብለዋል።
የጋዜጠኛና ደራሲ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) የአንደኛ የሙት ዓመት መታሰቢያንም ነፍሱ ባረፈችበት በዛሬዋ ዕለት ኃይማኖታዊ ስርዓቱን በጠበቀ አካሄድ መሠረት በእንጦጦ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን በፀሎት እንደታሰበ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቤተሰቡ በተጨማሪ " እኛ ቤተሰቦቹ እርሱን ለማሰብም በቁስቋም ጌርጌሴኖን የመርጃና ማገገሚያ ማዕከል የሚገኙ ወገኖቻችንን በመመገብም እንዘክረዋለን" ብለዋል።
"የገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) እልፈት ከተሰማ ጀምሮ ሀዘናችንን ሀዘናችሁ አድርጋችሁ ከሀገር ውስጥም ይሁን ከውጪ ሀገር ያፅናናችሁን ወዳጆቹ በሙሉ ስለሁሉም ነገር በፈጣሪ ስም እጅግ አድርገን ዛሬም እናመሰግናችኋለን" ሲሉም ምስጋናቸውን አቅረበዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የአርቲስት እንቁስላሴ የቀብር ሥነሥርዓት ተፈፀመ
የአርቲስት እንቁስላሴ ወ/አገኘሁ የቀብር ሥነሥርዓት ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እንደተፈጸመ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአርቲስት እንቁስላሴ ወ/አገኘሁ በተወለደ በ71 ዓመቱ ባደረበት ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ጥር 11/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ይታወሳል፡፡
አርቲስት እንቁስላሴ ወ/አገኘሁ ከአባታቸው ከአቶ ወ/አገኘሁ ኃይሌ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ዘውድነሽ ብሩ በጥቅምት 27/1946 በአዲስ አበባ ከተማ መወለዱን የህይወት ታሪኩ ያትታል።
ከባለቤቱ ወይዘሮ አይናለም ወርቁ 3 ሴቶች እና 3 ወንድ ልጆች ያፈራ ሲሆን እንዲሁም 12 የልጅ ልጆችን አፍርቷል፡፡
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአርቲስት እንቁስላሴ ወ/አገኘሁ የቀብር ሥነሥርዓት ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እንደተፈጸመ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአርቲስት እንቁስላሴ ወ/አገኘሁ በተወለደ በ71 ዓመቱ ባደረበት ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ጥር 11/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ይታወሳል፡፡
አርቲስት እንቁስላሴ ወ/አገኘሁ ከአባታቸው ከአቶ ወ/አገኘሁ ኃይሌ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ዘውድነሽ ብሩ በጥቅምት 27/1946 በአዲስ አበባ ከተማ መወለዱን የህይወት ታሪኩ ያትታል።
ከባለቤቱ ወይዘሮ አይናለም ወርቁ 3 ሴቶች እና 3 ወንድ ልጆች ያፈራ ሲሆን እንዲሁም 12 የልጅ ልጆችን አፍርቷል፡፡
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የአስትሮ ፎቶግራፊና የከዋክብት ምልከታ ተካሄደ
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የሥነ - ጥበብና የሳይንስ ማዕከላት ጋር በመተባበር የአስትሮ ፎቶግራፊና የከዋክብት ምልከታ አከናውኗል፡፡
በፀሐይ ምልከታ መርሐግብር ቴሌስኮፕን በመጠቀም የፀሐይን ፎቶስፊር እንዲሁም የፀሀይን ስፖቶች ታዳሚያን መመልከት ችለዋል፡፡ ይህንን ተከትሎም አስትሮ ፎቶግራፈር ክብረት አፅባሓ በቴሌስኮፕ ታግዘው የተነሱ የሰማይ አካላት ፎቶግራፎችን ያሳዩ ሲሆን ስለአስትሮ ፎቶግራፊ ሙያ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በማታው መርሐግብር በሶሳይቲው ባለሙያ ሊዲያ ዲንሳ አስተባባሪነት ተሳታፊዎች ቬነስን እና ጁፒተርን ከአራት ጨረቃዎችዋ ጋር መመልከት እንዲሁም ሌዘር ፖይንተር/ የብርሃን መጠቆሚያ በመጠቀም ስለተለያዩ የሰማይ አካላት አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል።
ይህም ተሳታፊዎችን የሚያስተምር እንዲሁም የተማሩትን በተግባር ለማስደገፍ ያገዘ መርሐግብር ሆኖ አልፏል፡፡
ጥር 9/2017 በተካሄደው በዚህ ፕሮግራም በርካታ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎችና ታዳሚያን ተገኝተዋል፡፡
©️መረጃው የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የሥነ - ጥበብና የሳይንስ ማዕከላት ጋር በመተባበር የአስትሮ ፎቶግራፊና የከዋክብት ምልከታ አከናውኗል፡፡
በፀሐይ ምልከታ መርሐግብር ቴሌስኮፕን በመጠቀም የፀሐይን ፎቶስፊር እንዲሁም የፀሀይን ስፖቶች ታዳሚያን መመልከት ችለዋል፡፡ ይህንን ተከትሎም አስትሮ ፎቶግራፈር ክብረት አፅባሓ በቴሌስኮፕ ታግዘው የተነሱ የሰማይ አካላት ፎቶግራፎችን ያሳዩ ሲሆን ስለአስትሮ ፎቶግራፊ ሙያ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በማታው መርሐግብር በሶሳይቲው ባለሙያ ሊዲያ ዲንሳ አስተባባሪነት ተሳታፊዎች ቬነስን እና ጁፒተርን ከአራት ጨረቃዎችዋ ጋር መመልከት እንዲሁም ሌዘር ፖይንተር/ የብርሃን መጠቆሚያ በመጠቀም ስለተለያዩ የሰማይ አካላት አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል።
ይህም ተሳታፊዎችን የሚያስተምር እንዲሁም የተማሩትን በተግባር ለማስደገፍ ያገዘ መርሐግብር ሆኖ አልፏል፡፡
ጥር 9/2017 በተካሄደው በዚህ ፕሮግራም በርካታ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎችና ታዳሚያን ተገኝተዋል፡፡
©️መረጃው የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የሎሚ ጭማቂ ትዝታ" አርብ ይመረቃል
በደራሲ አህመድ ሁስ የተዘጋጀው "የሎሚ ጭማቂ ትዝታ" የተሰኘ የረጅም ልቦለድ መጽሐፍ አርብ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመረቃል።
በዚህ የመጽሐፍ ምርቃት ላይ አርቲስት ሚካኤል ታምሬ፣ደራሲ ህይወት እምሻው፣ ገጣሚ ሚካኤል ምናሴ፣ ገጣሚ ኪሩቤል ዘርፉ ፣ገጣሚ ባንቺአየሁ አሰፋና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲ አህመድ ሁስ የተዘጋጀው "የሎሚ ጭማቂ ትዝታ" የተሰኘ የረጅም ልቦለድ መጽሐፍ አርብ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመረቃል።
በዚህ የመጽሐፍ ምርቃት ላይ አርቲስት ሚካኤል ታምሬ፣ደራሲ ህይወት እምሻው፣ ገጣሚ ሚካኤል ምናሴ፣ ገጣሚ ኪሩቤል ዘርፉ ፣ገጣሚ ባንቺአየሁ አሰፋና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በእረፍት ቀንዎ ቴአትር ይመለከቱ !
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ ሐሙስ፣ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 ጎዶ'ን ጥበቃ
ድርሰት: ሳሙኤል ቤኬት
ትርጉም: ሀይከል ሙባረክ
አዘጋጅ: ዳግም ሲሳይ
ቀን: ሐሙስ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ዋዋጎ
ድርሰት: ታረቀኝ ብርሃኑ
አዘጋጅ: ጥላሁን ዘውገ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍የሕይወት ታሪክ
ድርሰትና ዝግጅት ነብዩ ባዬ እና ቢንያም ወርቁ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ ሐሙስ፣ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 ጎዶ'ን ጥበቃ
ድርሰት: ሳሙኤል ቤኬት
ትርጉም: ሀይከል ሙባረክ
አዘጋጅ: ዳግም ሲሳይ
ቀን: ሐሙስ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ዋዋጎ
ድርሰት: ታረቀኝ ብርሃኑ
አዘጋጅ: ጥላሁን ዘውገ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍የሕይወት ታሪክ
ድርሰትና ዝግጅት ነብዩ ባዬ እና ቢንያም ወርቁ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የሙዚቃ ባለሞያ ተፈሪ አሰፋ አረፈ
የድራም የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቹ እና የነጋሪት ባንድ መስራች የሆነው ተፈሪ አሰፋ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ተሰምቷል።
ተፈሪ አሰፋ የኢትዮጵይ ሙዚቃ ካለበት ደረጃ ከፍ ለማድረግ የያዘውን ሞያ በውጭ ሃገር ተምሮ እና በሚገባ አጠናቆ ወደ ሃገሩ ኢትዮጵያ በመመለስ የድራም አጨዋወት ሞያ በሃገራችን በብዙ ሰው እንዲወደድ ያደረገ ታታሪ የሙዚቃ ሰው ነበር።
የሃገራችንን ሙዚቃ ድምበር ተሻጋሪ እንዲሆን እና በመላው ዓለም ተድማጭ እንዲሆን ጥናት አድርጎ የሙዚቃ አልበም በማስቀረፅ በዓለም ገበያ ላይ እንዲውል ያስቻለ ፣የድርሻውን የተወጣ እና እየተውጣ የሚገኝ ትጉህ፣ ታታሪ፣እውቀቱን ለሌሎች አሳልፎ መስጠትን የማይሰስት፣ ብዙ የድራም ተጫዋቾችን ያፈራ፣የድራም አጨዋወት ጥበብን በሚገባ በተማሪዋቹ አዕምሮ ውስጥ ያፅነሰ፣ ቀና ፣ልበ እሩሩህ እና ከሁሉም ሰው ጋር ተግባቢ እና መልካም ሰው ነበር።
Via አክሊሉ ወልደዮሀንስ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድራም የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቹ እና የነጋሪት ባንድ መስራች የሆነው ተፈሪ አሰፋ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ተሰምቷል።
ተፈሪ አሰፋ የኢትዮጵይ ሙዚቃ ካለበት ደረጃ ከፍ ለማድረግ የያዘውን ሞያ በውጭ ሃገር ተምሮ እና በሚገባ አጠናቆ ወደ ሃገሩ ኢትዮጵያ በመመለስ የድራም አጨዋወት ሞያ በሃገራችን በብዙ ሰው እንዲወደድ ያደረገ ታታሪ የሙዚቃ ሰው ነበር።
የሃገራችንን ሙዚቃ ድምበር ተሻጋሪ እንዲሆን እና በመላው ዓለም ተድማጭ እንዲሆን ጥናት አድርጎ የሙዚቃ አልበም በማስቀረፅ በዓለም ገበያ ላይ እንዲውል ያስቻለ ፣የድርሻውን የተወጣ እና እየተውጣ የሚገኝ ትጉህ፣ ታታሪ፣እውቀቱን ለሌሎች አሳልፎ መስጠትን የማይሰስት፣ ብዙ የድራም ተጫዋቾችን ያፈራ፣የድራም አጨዋወት ጥበብን በሚገባ በተማሪዋቹ አዕምሮ ውስጥ ያፅነሰ፣ ቀና ፣ልበ እሩሩህ እና ከሁሉም ሰው ጋር ተግባቢ እና መልካም ሰው ነበር።
Via አክሊሉ ወልደዮሀንስ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ነገረ መጻሕፍት" ዛሬ ይካሄዳል
በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል። በዚህ መሰናዶ ላይ ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ እና ዶ/ር አንዱዓለም አባተ ተጋባዥ እንግዶች ሲሆኑ ለውይይት የሚቀርቡ አብይ ርዕሰ ጉዳይ "የተደበቁ እውነቶች የተጋረዱ ሀቆች" ይሰኛል።የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል። በዚህ መሰናዶ ላይ ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ እና ዶ/ር አንዱዓለም አባተ ተጋባዥ እንግዶች ሲሆኑ ለውይይት የሚቀርቡ አብይ ርዕሰ ጉዳይ "የተደበቁ እውነቶች የተጋረዱ ሀቆች" ይሰኛል።የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1