ብሪክስ ከኢኮኖሚ ጥምረት ባለፈ የራሱ “የፀጥታ ምክር ቤት” ሊኖረው ይገባል፡- ደቡብ አፍሪካዊት ምሁር
*********
ብሪክስ እስከ አሁን ሲከተለው የነበረው “ዝግ ዲፕሎማሲ” (Quiet Diplomacy) ፋይዳው እንዳከተመ ደቡብ አፍሪካዊቷ ምሁር ጊሊያን ሹት ገልፀዋል።
ምዕራባውያን ታዳጊ ሀገራትን እንደ እኩል አጋር ከማየት ይልቅ እንደ ስጋት ፈርጀው ለመቆጣጠር እየሞከሩ በመሆኑ፣ ብሪክስ ከጥንቃቄ ወጥቶ ራሱን መከላከል አለበት ይላሉ እኚህ ምሁር።
የኢኮኖሚ ማዕቀቦች፣ የሳይበር ጥቃቶች እና የመረጃ ጦርነቶች የብሪክስ አባል ሀገራትን አንድነት ለመሸርሸር ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው የሚሉት ምሁሯ የ“ዝግ ዲፕሎማሲ” አካሄድ ማብቃቱን ያመላክታሉ ነው የሚሉት።
በተለይም እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ብራዚል ያሉ ሀገራት በውጭ በሚደገፉ ሚዲያዎችና ተቋማት አማካኝነት ለውስጥ አለመረጋጋት ተጋልጠዋል።
ይህን መሰለ ችግሮችን ለመፍታት ብሪክስ የራሱ የፀጥታው ምክር ቤት ቢኖረው፣ አባል ሀገራቱ የሚያደርጓቸው ወታደራዊ ልምምዶችና ትብብሮች በጠላቶቻቸው እንዳይጠመዘዙ ሕጋዊ ጥበቃ ይሰጣቸዋል የሚል ሃሳብ ይዘው ነው የመጡት ምሁሯ።
እንዲሁም አንዲት ሀገር ላይ የሚሰነዘርን ሁለንተናዊ ጫና ሁሉም በጋራ እንዲመክቱት የሚያስችል ዕድልንም ይፈጥራል።
ከምዕራባውያን ተጽዕኖ ነፃ የሆነ፣ በምርምርና በእውነት ላይ የተመሠረተ የብሪክስ ሚዲያና የምርምር ተቋማት (Think Tanks) መገንባት ለህልውና ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
በሰለሞን ገዳ
*********
ብሪክስ እስከ አሁን ሲከተለው የነበረው “ዝግ ዲፕሎማሲ” (Quiet Diplomacy) ፋይዳው እንዳከተመ ደቡብ አፍሪካዊቷ ምሁር ጊሊያን ሹት ገልፀዋል።
ምዕራባውያን ታዳጊ ሀገራትን እንደ እኩል አጋር ከማየት ይልቅ እንደ ስጋት ፈርጀው ለመቆጣጠር እየሞከሩ በመሆኑ፣ ብሪክስ ከጥንቃቄ ወጥቶ ራሱን መከላከል አለበት ይላሉ እኚህ ምሁር።
የኢኮኖሚ ማዕቀቦች፣ የሳይበር ጥቃቶች እና የመረጃ ጦርነቶች የብሪክስ አባል ሀገራትን አንድነት ለመሸርሸር ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው የሚሉት ምሁሯ የ“ዝግ ዲፕሎማሲ” አካሄድ ማብቃቱን ያመላክታሉ ነው የሚሉት።
በተለይም እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ብራዚል ያሉ ሀገራት በውጭ በሚደገፉ ሚዲያዎችና ተቋማት አማካኝነት ለውስጥ አለመረጋጋት ተጋልጠዋል።
ይህን መሰለ ችግሮችን ለመፍታት ብሪክስ የራሱ የፀጥታው ምክር ቤት ቢኖረው፣ አባል ሀገራቱ የሚያደርጓቸው ወታደራዊ ልምምዶችና ትብብሮች በጠላቶቻቸው እንዳይጠመዘዙ ሕጋዊ ጥበቃ ይሰጣቸዋል የሚል ሃሳብ ይዘው ነው የመጡት ምሁሯ።
እንዲሁም አንዲት ሀገር ላይ የሚሰነዘርን ሁለንተናዊ ጫና ሁሉም በጋራ እንዲመክቱት የሚያስችል ዕድልንም ይፈጥራል።
ከምዕራባውያን ተጽዕኖ ነፃ የሆነ፣ በምርምርና በእውነት ላይ የተመሠረተ የብሪክስ ሚዲያና የምርምር ተቋማት (Think Tanks) መገንባት ለህልውና ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
በሰለሞን ገዳ
❤2
አርሰናል እና ሊቨርፑል በ2024 እና በ2025 ከ17 ጨዋታ በኋላ
****
አርሰናል የፈረንጆቹን ገና በ39 ነጥብ ሊጉን እየመራ ተቀብሏል፡፡ የባለፈው ዓመት ሻምፒዮን ሊቨርፑል ደግሞ ከአርሰናል በ10 ነጥብ አንሶ በ29 ነጥብ ነው የእነሱን ገና የተቀበለው፡፡
ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ሰዓት ሊቨርፑል ካደረጋቸው 17 ጨዋታዎች 40 ነጥቦችን በመሰብሰብ ነበር የገናን በዓል ያከበረው፡፡ አርሰናል ደግሞ ከሊጉ መሪ ሊቨርፑል በ ስድስት ነጥብ ዝቅ ብሎ በ33 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ በመቀጥ ነው የ2024 ገናን ያሳለፈው፡፡
በዚህ ዓመት ነገሮች በብዙ ተቀይረዋል፡፡ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ባለፈው ዓመት ከ17 ጨዋታ ካገኘው 33 ነጥብ በስድስት አሻሽሎ ሊጉን እየመራ ሲሆን የመርሲሳይዱ ክለብ ደግሞ ከነበረበት 40 ነጥብ በ11 ነጥብ አሽቆልቁሎ 5ኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ ተገዷል፡፡
የፈረንጆች ገናን እና አዲስ ዓመትን ሊጉ እየመሩ የተረከቡ በርካታ ቡድኖች ከዋንጫ ጋር የመገናኝት ዕድላቸው ሰፊ ቢሆንም አርሰናል ግን የዚህ ዓመቱን ጨምሮ ከባለፉት አራት ዓመታት በሦስቱ በአዲስ ዓመት ሊጉን ቢመራም ዋንጫውን ማሳካት አልቻለም፡፡
በዚህ ዓመትስ ቀሪዎቹ 21 የሊግ ጨዋታዎች መልስ የሚሰጡ ይሆናል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
****
አርሰናል የፈረንጆቹን ገና በ39 ነጥብ ሊጉን እየመራ ተቀብሏል፡፡ የባለፈው ዓመት ሻምፒዮን ሊቨርፑል ደግሞ ከአርሰናል በ10 ነጥብ አንሶ በ29 ነጥብ ነው የእነሱን ገና የተቀበለው፡፡
ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ሰዓት ሊቨርፑል ካደረጋቸው 17 ጨዋታዎች 40 ነጥቦችን በመሰብሰብ ነበር የገናን በዓል ያከበረው፡፡ አርሰናል ደግሞ ከሊጉ መሪ ሊቨርፑል በ ስድስት ነጥብ ዝቅ ብሎ በ33 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ በመቀጥ ነው የ2024 ገናን ያሳለፈው፡፡
በዚህ ዓመት ነገሮች በብዙ ተቀይረዋል፡፡ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ባለፈው ዓመት ከ17 ጨዋታ ካገኘው 33 ነጥብ በስድስት አሻሽሎ ሊጉን እየመራ ሲሆን የመርሲሳይዱ ክለብ ደግሞ ከነበረበት 40 ነጥብ በ11 ነጥብ አሽቆልቁሎ 5ኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ ተገዷል፡፡
የፈረንጆች ገናን እና አዲስ ዓመትን ሊጉ እየመሩ የተረከቡ በርካታ ቡድኖች ከዋንጫ ጋር የመገናኝት ዕድላቸው ሰፊ ቢሆንም አርሰናል ግን የዚህ ዓመቱን ጨምሮ ከባለፉት አራት ዓመታት በሦስቱ በአዲስ ዓመት ሊጉን ቢመራም ዋንጫውን ማሳካት አልቻለም፡፡
በዚህ ዓመትስ ቀሪዎቹ 21 የሊግ ጨዋታዎች መልስ የሚሰጡ ይሆናል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
❤2
ከግጭት ማንም አትራፊ አይሆንም ፤ መጨረሻውም ድርድር እና ስምምነት ነው፡፡
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል በቅርቡ የሰላም ስምምነት መደረጉ ይታወሳል፡፡ በዚህን ወቅት ከግጭት አትራፊ እንደሌለ እና ችግሮችን በውይይት መፍታት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ)ን ወክለው ከክልሉ መንግስት ጋር ዘላቂ ስምምነቱን የተፈራረሙት ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው የግጭቶች መቋጫ ውይይት መሆኑም አንስተዋል፡፡
የህዝብን ጥያቄ ለማስመለስ ወደ ትግል ብንገባም የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዳ እና ሉዓላዊነትን የሚዳፈር ሁኔታ ሲፈጠር ወደ ሰላም አማራጭ መጥተናል ብዋል- የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች ፡፡
ስምምነቱ በህዝቡ ዘንድ ትልቅ ደስታን ፈጥሯል፡፡ ከግጭት እና አለመግባባት ወደ ጠረንጴዛ ውይይት መምጣት እና መደራደር ሁለቱን ወገኖች ከፍ ሲልም ሀገር እና ህዝብን አትራፊ ስለሚያደርግ ተጠናክሮ ይቀጥል ብለዋል- አስተያየት ሰጪዎች፡፡
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ወደ ሰላም ውይይት እና ድርድር ያልመጡ የታጠቁ ሀይሎች እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የሰላም ስምምነቱ በአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን እና በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) አማካኝነት መከናወኑ ይታወሳል፡፡
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል በቅርቡ የሰላም ስምምነት መደረጉ ይታወሳል፡፡ በዚህን ወቅት ከግጭት አትራፊ እንደሌለ እና ችግሮችን በውይይት መፍታት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ)ን ወክለው ከክልሉ መንግስት ጋር ዘላቂ ስምምነቱን የተፈራረሙት ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው የግጭቶች መቋጫ ውይይት መሆኑም አንስተዋል፡፡
የህዝብን ጥያቄ ለማስመለስ ወደ ትግል ብንገባም የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዳ እና ሉዓላዊነትን የሚዳፈር ሁኔታ ሲፈጠር ወደ ሰላም አማራጭ መጥተናል ብዋል- የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች ፡፡
ስምምነቱ በህዝቡ ዘንድ ትልቅ ደስታን ፈጥሯል፡፡ ከግጭት እና አለመግባባት ወደ ጠረንጴዛ ውይይት መምጣት እና መደራደር ሁለቱን ወገኖች ከፍ ሲልም ሀገር እና ህዝብን አትራፊ ስለሚያደርግ ተጠናክሮ ይቀጥል ብለዋል- አስተያየት ሰጪዎች፡፡
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ወደ ሰላም ውይይት እና ድርድር ያልመጡ የታጠቁ ሀይሎች እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የሰላም ስምምነቱ በአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን እና በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) አማካኝነት መከናወኑ ይታወሳል፡፡
❤3
ፉልሀም 1 ፡ 0 ሊቨርፑል (የመጀመርያ ግማሽ ውጤት)
****
ፉልሀም በሃሪ ዊልሰን ግብ ሊቨርፑልን 1 ለ 0 እየመራ የመጀመርያው 45 ደቂቃ ተጠናቋል፡፡
👉ቶተንሀም ሆትስፐር 1 ፡ 0 ሰንደርላንድ
👉ኤቨርተን 0 ፡ 1 ብሬንትፎርድ
👉ኒውካስትል ዩናይትድ 0 ፡ 0 ክሪስታል ፓላስ
****
ፉልሀም በሃሪ ዊልሰን ግብ ሊቨርፑልን 1 ለ 0 እየመራ የመጀመርያው 45 ደቂቃ ተጠናቋል፡፡
👉ቶተንሀም ሆትስፐር 1 ፡ 0 ሰንደርላንድ
👉ኤቨርተን 0 ፡ 1 ብሬንትፎርድ
👉ኒውካስትል ዩናይትድ 0 ፡ 0 ክሪስታል ፓላስ
❤1👍1
ድራማዊ ክስተት በተስተዋለበት ጨዋታ ሊቨርፑል ከፉልሀም አቻ ተለያየ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት ሊቨርፑል ከሜዳው ውጭ ከፉልሀም ባደረገው ጨዋታ ሁለት አቻ ተለያይቷል፡፡
በክራቨንኮቴጅ በተደረገው ጨዋታ ፉልሀም ሃሪ ዊልሰን ያደገበት ክለብ ላይ ባስቆጠራት ግብ መምራት ቢችልም ሊቨርፑል በፍሎሪያን ቨርዝ አቻ ሆኖ ነበር፡፡
ሁለቱ ቡድኖች ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቀቀ ተብሎ ሲጠበቅ ኮዲ ጋክፖ በባከነ ሰዓት ሊቨርፑልን አሸናፊ ለማድረግ የተቃረበች ግብ አስቆጥሯል፡፡
ቢሆንም የተጨመረው ደቂቃ ተጠናቆ የዳኛው ፊሽካ ሲጠበቅ ሃሪሰን ሪድ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ የአቻነት ግብ እንዲሁም የሊቨርፑልን የአሸናፊነት ተስፋ የነጠቀች ግብ አስቆጥሯል፡፡
በባከነ ሰዓት ሁለት ግቦች የተቆጠሩበት አዝናኝ ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል፡፡
በአውሮፓ መድረክ ለመሳተፍ እየታገለ የሚገኘው ሊቨርፑል በውድድር ዓመቱ ለ4ኛ ጊዜ አቻ የተለያየ ሲሆን በ34 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት ሊቨርፑል ከሜዳው ውጭ ከፉልሀም ባደረገው ጨዋታ ሁለት አቻ ተለያይቷል፡፡
በክራቨንኮቴጅ በተደረገው ጨዋታ ፉልሀም ሃሪ ዊልሰን ያደገበት ክለብ ላይ ባስቆጠራት ግብ መምራት ቢችልም ሊቨርፑል በፍሎሪያን ቨርዝ አቻ ሆኖ ነበር፡፡
ሁለቱ ቡድኖች ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቀቀ ተብሎ ሲጠበቅ ኮዲ ጋክፖ በባከነ ሰዓት ሊቨርፑልን አሸናፊ ለማድረግ የተቃረበች ግብ አስቆጥሯል፡፡
ቢሆንም የተጨመረው ደቂቃ ተጠናቆ የዳኛው ፊሽካ ሲጠበቅ ሃሪሰን ሪድ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ የአቻነት ግብ እንዲሁም የሊቨርፑልን የአሸናፊነት ተስፋ የነጠቀች ግብ አስቆጥሯል፡፡
በባከነ ሰዓት ሁለት ግቦች የተቆጠሩበት አዝናኝ ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል፡፡
በአውሮፓ መድረክ ለመሳተፍ እየታገለ የሚገኘው ሊቨርፑል በውድድር ዓመቱ ለ4ኛ ጊዜ አቻ የተለያየ ሲሆን በ34 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
❤1
ካሜሩን ደቡብ አፍሪካን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች
****
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በተደረገ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ካሜሩን ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 1 አሸንፋለች፡፡
ጁኒየር ቻማዱ እና ክርስቲያን ኮፋን የካሜሩንን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ማክጎፓ የደቡብ አፍሪካን አንድ ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡
የኮትዲቯር አፍሪካ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ የነበረችው ደቡብ አፍሪካ ገና በጊዜ ከአህጉሩ ውድድር ተሰናባች ሆናለች፡፡
በሩብ ፍጻሜው ካሜሩን ከ አስተናጋጇ ሞሮኮ የምትጫወት ይሆናል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
****
በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በተደረገ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ካሜሩን ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 1 አሸንፋለች፡፡
ጁኒየር ቻማዱ እና ክርስቲያን ኮፋን የካሜሩንን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ማክጎፓ የደቡብ አፍሪካን አንድ ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡
የኮትዲቯር አፍሪካ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ የነበረችው ደቡብ አፍሪካ ገና በጊዜ ከአህጉሩ ውድድር ተሰናባች ሆናለች፡፡
በሩብ ፍጻሜው ካሜሩን ከ አስተናጋጇ ሞሮኮ የምትጫወት ይሆናል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
❤2🥰1