TEMARI-NET – Telegram
TEMARI-NET
4.11K subscribers
911 photos
17 videos
167 files
288 links
This Channel is created to disseminate proper, timely information and news for Students
Download Telegram
Forwarded from Alpha Market
💠Shop @AlphaMarket21 at a discount price

Airpods Pro(USA) white color 1899 birr
Airpods pro (USA) Black color 1899 birr

Calculator (Scientific) : 800 birr
P9 headset 1599 birr


u can check additional products @alphamarket21

contact us @ordernow21 or 0931463406
with free delivery

We Don’t Just Sell — We Guarantee!
82 ሺህ በላይ ተማሪዎች በ2018 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ትምህርት ይወስዳሉ፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር

በ2018 የትምህርት ዓመት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ከ82 ሺህ በላይ ተፈታኞች ለአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ትምህርት ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

82,838 ተፈታኞች በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ለመውሰድ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚገቡ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ጡሽኔ ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ ትናንት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በግልም ሆነ በመንግሥት ተቋማት የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚችሉት፣ እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች እንደሆኑ መግለፁ ይታወቃል፡፡

@TEMARI_Net1
Forwarded from AAU MEREJA
#FYI
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ።

የዩኒቨርስቲ ምደባ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤
የዩኒቨርስቲ ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ በሚከተሉት ሊንኮች ማየት የምትችሉ መሆኑነ እንገልጻለን።

Website: https://student.ethernet.edu.et
Telegram bot: @moestudentbot

@AAUMEREJA
#ጥቆማ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2018 የትምህርት ዓመት የቴአትር እና የፊልም ጥበባት ትምህርት ቤት በቅድመ ምረቃ በማታው መርሃ ግብር ገብተው መማር ለሚፈልጉ አመልካቾች ጥሪ አቅርቧል።

በማስታወቂያውም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አመልካቾች ከመስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በመደበኛ የስራ ቀናት OCR እንደኛ ፎቅ ቢሮ 224 በስራ ሰዓት ተገኝተው መመዝገብ ይችላሉ ብሏል።

ምን ያስፈልጋል ?

1. 2015፣ 2016 እና 2017 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ተፈትናችሁ በወቅቱ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላቸው፤

2. 2015፣ 2016 እና 2017 ዓ.ም የመልቀቂያ ፈተና ተፈትናችሁ ከመንግስት ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ውጤት ያላቸው፤

3. ከሙያ ትምህርት ቤቶች(TVET) ተመርቀው የአራተኛ (COC) ማስረጃ ያላቸው፤

4. ዲግሪ እና ዲፕሎማ ያላቸው፤

በዚህም ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች

- የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት፤

- ከሙያ ትምህርት ቤቶች የጨረሳችሁ ከላይ ከተጠቀሱት የትምህርት ማስረጃዎች በተጨማሪ፣ የሙያ ዲፕሎማ ማስረጃ፣ COC አራተኛ እርከን ያለፋችሁበት ማስረጃ ይዛችሁ በመምጣት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በዩኒቨእሲቲው የቴአትር እና የፊልም ጥበባት ትምህርት ቤት አስታውቋል።

@TEMARI_Net1
ከዩኒቨርሲቲ ምደባ ጋር የተያያዘ ማንኛውም ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ላላቸው ተማሪዎች ምላሽ እየሰጠን ነው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡና በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ትናንት ይፋ መደረጉ ይታወቃል።

በርካታ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲ ምደባው ጋር ተያይዞ ያላቸውን ጥያቄ አድርሰውናል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቀናል፡፡

በዚህም በትምህርት ሚኒስቴር የተቋቋመ ኮሚቴ ከምደባው ጋር በተያያዘ ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ላላቸው ተማሪዎች ምላሽ እየሰጠ እንደሚገኝ የሚኒስቴሩ አመራር እና የኮሚቴው አባል ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል፡፡

በኦንላይን ብቻ 350 የሚሆኑ ቅሬታዎችን መቀበላቸውን የገለፁት የኮሚቴው አባል፤ በአካል ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ለሔዱ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ተገቢ ምላሽና ማብራሪያ እየተሰጣቸው መሆኑንም ገልፀዋል፡፡

ክፍተቶች ካሉ እያየን ነው ያሉት አመራሩ፤ ከምደባው ጋር የተያያዘ ማንኛውም ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች በቀጣይ ቀናትም በአካል ማቅረብ ይችላሉ ብለዋል፡፡

@TEMARI_Net1
1
Good News!

The CoBE Library will begin 24/7 service starting from ጥቅምት 1፣ 2018 E.C. (October 11, 2025).

Source: CoBE Students’ Council
@TEMARI_Net1
Forwarded from AAU NEWS
Addis_Ababa_University_Exam_Center_NGAT_Exam_Schedule_October_13.xlsx
254.8 KB
#NGAT
Addis Ababa University Exam Center NGAT Exam Schedule October 13, 2025

@AAUNEWS1
" በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።

ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው።

በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለፁት፤ በሚቀጥሉት ዓመታት የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ምደባ እንደሚያቆምና የማለፊያ ነጥብ የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች በሚፈልጓቸው ዩኒቨርሲቲዎችና የትምህርት መስኮች እንዲያመለክቱ ይደረጋል፡፡

" የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደከዚህ ቀደሙ በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ ሳይሆን በተማሪዎቹ ምርጫ ይሆናል " ብለዋል።

" ተማሪዎች የሚማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ሲመርጡም ምክንያታዊ በመሆን በዬትኛው ዩኒቨርሲቲ የተሻለ የትምህርት መስክ፣ እውቀትና የስራ እድል ላገኝ እችላለሁ በማለት ይመርዝታሉ " ሲሉ ገልጸዋል። #ኢፕድ

@TEMARI_Net1
6👍1
“ በተያዘው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሜዲያል ተፈታኞችን እቀበላላሁ ” - ኢንስቲትዩቱ

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2018 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሜዳል ተፈታኞችን እንደሚቀበልና አዲስ የተቀረጹ የስልጠና መርሃግብሮችንም ይፋ እንዳደረገ ገልጿል።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ተቀብሎ እስከ 3 ዲግሪ ባሉት ደረጃዎች እንደሚያሰለጥን ያስታወቀው ተቋሙ፣ በዚሁ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሚዳል ተፈታኞችን እንደሚቀበልም ጠቁሟል፡፡

በመደበኛው በቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በክረምት የስልጠና መርሃግብሮች ከደረጃ ስድስት እስከ 8 (ከመጀመሪያ እስከ 3ኛ ዲግሪ) የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አንደሚሰጥ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞችን የሚቀበልባቸው አራት መንገዶች ምን ምን ናቸው?

- ደረጃቸውን ለማሻሻል የቴክኒክና ሙያ አመራሮችና ሰልጣኞችን፣
- የኢንዱስትሪ ቴክኒሻኖችን በማታው፣ በቅዳሜና እሁድ ፕሮግራሞች፣
- የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያመጡትን፣ እንዲሁም የሪሜዳል ተፈታኞችን (ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ) እንደሚቀበል ነው የገለጸው፡፡

ተደራሽነቱ ምን ይመለስላል?

ኢንስቲትዩቱ በአዲስ አበባ ከሚገኘው ዋና ካምፓሱ በተጨማሪ የሀዋሳ ካምፓስና የብየዳ ስልጠና ልህቀት ማዕከል ካምፓሶች፣ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሚገኙ 16 የሳተላይት ተቋማት በደረጃ 6 ወይም በመጀመሪያ ዲግሪ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አስረድቷል፡፡

አዲስ የተቀረጹት አጫጭር የስልጠና መርሃግብሮች ምንድን ናቸው?

በዘንደሮው አመት 11 አዳዲስ የስልጠና ፕርግራሞች ከመታከላቸው በተጨማሪ አዳዲስ የተቀረጹ የአጭር ጊዜ የስልጠና መርሃ ግብሮችም ይፋ ተደርገዋል፡፡ በዚህም፦
- በሲቪል ቴክኖሎጂ፣
- በኤሌክትሪክ እና አይሲቲ፣
- በመካኒካል ቴክኖሎጂ፣
- በቴክስታይል እና አፓረል፣
- በአግሪካልቸራል እና አግሮፕሮሰሲንግ፣
- በሉባን ወርኪንግ የሚሰጡ ሲሆኑ፣ በእነዚህ ስር ያሉ ዝርዝሮችና ሌሎች የስልጠና ዝርዝሮች ከላይ ተያይዘዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
1
Forwarded from Alpha Market
💠Shop @AlphaMarket21 at a discount price

Airpods Pro(USA) white color 1899 birr
Airpods pro (USA) Black color 1899 birr

Calculator (Scientific) : 800 birr
P9 headset 1599 birr


u can check additional products @alphamarket21

contact us @ordernow21 or 0931463406
with free delivery

We Don’t Just Sell — We Guarantee!