Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
አጠቃላይ_40_60_ቤት_ፕሮግራም_አሸናፊዎች_ዝርዝር_xls_min_1.pdf
1.3 MB
እንኳን ደስ አላችሁ‼️
የ3ኛ ዙር የ40/60 የጋራ መኖርያ ቤት ዕድለኞችን ስም ዝርዝር
በአማራ ክልል ሁለት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ግንባታ ላይ ናቸው
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ሁለት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ግንባታ ላይ መሆናቸውን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ። በክልሉ በርካታ ባለሀብቶች በማዕድን ዘርፍ ላይ ገብተው የምርመራ ፍቃድ በመውሰድ ወደ ማምረት ስራ መግባታቸውም ተገልጿል።
የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ይታየው ተስፋሁን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የምርመራ ፍቃድ ከወሰዱ ሰባት ኩባንያዎች መካከል ሁለቱ ወደ ግንባታ ገብተዋል።
እንደ አቶ ይታየው ገለፃ፤ በክልሉ በሲሚንቶ ዘርፍ ገብተው ለመስራት ፍቃድ ከተሰጣቸው ሰባት ኩባንያዎች መካከል ናሽናል እና በረንታ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች የግንባታ ስራ ጀምረዋል።
የሲሚንቶ ፋብሪካዎቹ መገንባት እንደ ሀገር የተከሰተውን የሲሚንቶ እጥረት ችግር የመቅረፍ አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት ነው አቶ ይታየው የገለፁት።
ናሺናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በክልሉ ሰሜን ሸዋ እንሳሮ ወረዳ ለሜ እንዲሁም በረንታ ሲሚንቶ በክልሉ ምስራቅ ጎጃም ዞን በረንታ እንደሚገኙም አቶ ይታየው ተናግረዋል። ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ ስራውን በቀጣይ አንድ አመት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩነ ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85874
ክልሉ 321 ዋሻዎችን ለቱሪዝም አገልግሎት ለማዋል እየሰራ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
የቱሪዝም ሀብቶችን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች አገልግሎት በማዋል ከዘርፉ የሚጠበቀውን ገቢ ለማስገኘት 321 ዋሻዎችን ለቱሪዝም አገልግሎት ለማዋል በትኩረት እየሰራበት መሆኑን የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ ዋሻዎች ላይ የተደረገ ጥናት ክልሉ የዓለም ቱሪዝም ቀን በሚያከብርበት ቀን ይፋ ተደርጓል፡፡
በኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዋሻ ጥናት ባለሙያ ናስር አህመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ቢሮው በክልሉ ለቱሪዝም ሀብት የሚውሉ ዋሻዎች ለሚፈለገው አገልግሎት እንዲውሉ ለማድረግ በዋሻ ጥናት አድርጓል፡፡ ከውጪ ሀገራት ባለሙያ ጋር በመሆን በተደረገው ጥናት ለ321 ዋሻዎች አስፈላጊ መረጃ መሰባሰቡንም ገልጸዋል፡፡
ጥናት ከተደረገባቸው ውስጥ ለ200 ዋሻ ካርታና ፕላን የተሰራላቸው ሲሆን አብዛኞቹ በምስራቅና ምዕራብ ሀረርጌ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ሌሎቹ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ መልከ ቁንጡሬ አካባቢ ፣ ሰሜን ሸዋ ፣ ወለጋ ግምቢና ደምቢዶሎ እንደሚገኙ ጥናቱ አመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በዋሻ ሀብት ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገር ናት ያሉት አቶ ናስር፤ አሁን ጥናት ከተደረገባቸው አካባቢዎች በምስራቅ ሀረርጌ አንድ ወረዳ ብቻ 55 ዋሻዎች መኖራቸው ክልሉ በዋሻ ሀብት ቀዳሚ መሆኗን ያሳያል....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85862
(ፎቶ የሶፍዑመር ዋሻ ከኢንተርኔት የተገኘ)
በተያዘው ዓመት በማክሮ ኢኮኖሚው ሰባት ነጥብ አምስት በመቶ እድገት ይጠበቃል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በዘንድሮው ዓመት በማክሮ ኢኮኖሚው ዘርፍ ሰባት ነጥብ አምስት በመቶ እድገት ይመዘገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ከህዝብ እንደራሴዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለፉት ዓመታት፣ በተለይም ደግሞ ባለፈው ዓመት ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ፈተናዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ቢያስተናግድም፤ በቀላሉ የማይሰበርና በተያዘው የዕድገት መስመር የሚቀጥል በመሆኑ፤ ጫናን ተቋቁሞ 6 ነጥብ 16 ትሪሊየን ብር (127 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር) ደርሷል፡፡ የነፍስ ወከፍ ገቢ አንድ ሺህ 212 ዶላር ሆኗል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚው አምና ስድስት ነጥብ አራት በመቶ የተመዘገበ ሲሆን፤ በዘንድሮ ዓመት ሰባት ነጥብ አምስት በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዓለም ባንክን መረጃ ዋቢ አድርገው እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛው፣ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሃገራት ደግሞ ሶስተኛው ግዙፍ ኢኮኖሚ ሆኗል፡፡ በኢትዮጵያ መደበኛና መደበኛ ያልሆነ ኢኮኖሚያዊ እ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85846
የኢትዮቴሌኮምን 40 በመቶ ድርሻ ለመሸጥ ዓለም አቀፍ ጨረታ ከዛሬ ጀምሮ ይወጣል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የገንዘብ ሚኒስሩር አቶ አህመድ ሽዴ እና ሚኒስትር ደኤታው ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ኢትዮቴሌኮምን በከፊል ወደ ግል በሚዛወርበት (ፕራይቬታይዝ በሚደረግበት) ሁኔታ ዙሪያ መግለጫ እየሰጡ ነው።
መንግስት የኢትዮቴሌኮምን 40 በመቶ ድርሻ ወደ ግል ለማዛወር አውጥቶት የነበረው ዓለም አቀፍ ጨረታ በአለም አቀፍ የኢኮኖሚ መቀዛቀዝና በአገር አቀፍ ደረጃም ምቹ ሁኔታ ስላልነበረ መቋረጡን አስታውሰዋል።
ዓለም አቀፍ ኩባንያን ለማስገባት ከዛሬ ጀምሮ ጨረታው ለቀጣይ ሶስት ሳምንታት እስከ እአአ ዲሴምበር 19 ቀን 2022 ክፍት ተደርጓል።
አሁን በተፈጠረው ስምምነት መሰረትና አለም አቀፋዊ ሁኔታውን ግምት ውስጥ በማስገባት ከሳፋሪኮም ቀጥሎ አንድ ተጨማሪ ኩባንያ ለማስገባት ጨረታ ወጥቷል ብለዋል።
በዘላለም ግዛው
ከሁመራ -ወልቃይት እስከ ሽራሮ ያለው የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እየተጠገነ ነው
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከሁመራ – ወልቃይት እስከ ሽራሮ ያለው የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እየተጠገነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ጉዳት የደረሰባቸው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጥገና እንደቀጠለ ነው።
ከሁመራ እስክ ሽራሮ የተዘረጋውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ላይ በአማካይ በቀን እስከ 200 የሚደርሱ የኢትዮጵያ ኤለኬክትሪክ ኃይል ሰራተኞች እየተሳተፉበት ይገኛሉ ብለዋል። በከፍተኛ የኃይል መስመሩ ላይ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መስመሮች በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት እንደደረሰባቸውና ተበጣጥሰው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሞገስ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎችም መስመሮቹ ዳግም አገልግሎት እንዲሰጡ አስፈላጊውን ጥረት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከመስመር ጥገናው ባለፈ የወልቃይት አካባቢ የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያው ቀደም ብሎ በነበረው ጦርነት የተነሳ ጉዳት እንደደረሰበት አቶ ሞገስ አስታውሰዋል። የወልቃይት ኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የጥገና ስራም እየተከናወነ መሆኑንና ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85884
የውሃ አቅርቦት ከአንድ ወር በላይ በመቋረጡ ለችግር መጋለጣቸውን ነዋሪዎች ገለፁ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
👉የችግሩ መንስኤ በውሃ መስመር እና ኃይል አቅርቦት ላይ በተከሰተ ችግር መሆኑም ተጠቁሟል
ከአንድ ወር በላይ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በመቋረጡ ለችግር መጋለጣቸውን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ቅሬታቸውን ያቀረቡ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ ችግሩ በውሃ መስመር ላይ በተፈፀመ አሻጥርና በተወሰኑ አካባቢዎች ጉድጓዶች ላይ በደረሰ መጠነኛ የቴክኒክ ችግር የተከሰተ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ቅሬታቸውን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከገለፁት ነዋሪዎች መካከል በወይራ አካባቢ ለምለም በሚባል መንደር የሚገኙ ነዋሪዎች እንዳሉት፤ በአካባቢያቸው ከአንድ ወር በላይ የመጠጥ ውሃ ተቋርጦባቸው ቆይቷል፡፡ ይህም ለከፍተኛ እንግልት እንደዳረጋቸውና ከዚህም በተጨማሪ ለውሃ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከሚመለከታቸው አካላት በቅጡ እንዳልተነገራቸው እንዲሁም ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መልዕክት አለመተላለፉን አስገንዝበዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ ሃና ማርያም በሚባለው አካባቢ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ከተቋረጠ ከአንድ ወር በላይ መሆኑንና ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፈጣን ምላሽ ማግኘት አለመቻላቸው እንዳሳዘናቸው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ባለስልጣኑ ለደንበኞቹ የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲፈትሽ ጠይቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰርካለም ጌታቸው...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85873
የይርጋለም ኢንዱስትሪ ፓርክ በሊዝ የሚተላለፍ 97 ሄክታር መሬት ዝግጁ አድርጓል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በሲዳማ ክልል የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ የለማ 97 ሄክታር መሬት ለባለሀብቶች በሊዝ ለማስተላለፍ ዝግጁ ማድረጉን በክልሉ የኢንዱስትሪያል ፓርኮች ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኃይሉ የተራ ገለጹ።
በፓርኩ ከገቡ አምራቾች መካከል የግብርና ምርቶችን ከአርሶ አደሩ ተቀብለው በማቀነባበር ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማቅረብ የጀመሩ መኖራቸውን ገልጸዋል። የአቮካዶ ምርትን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ከጀመሩት የኢትዮጵያና የኔዘርላንድ ኩባንያዎች ባለፉት አራት ዓመታት አምስት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱንም ጠቁመዋል።
እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ 11 ሼዶች ተገንብተው ተከራይተዋል፡፡ በፓርኩ ለማልማት ውል ከፈጸሙ 20 የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች አራቱ ምርት ጀምረዋል፣ አንዱ በሙከራ ትግበራ ላይ ነው፤ ስድስቱ ደግሞ ከባንክ ጋር ውል ገብተው በሂደት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85864
ትኩረቱን በአባይ ግድብና በሌሎች ግዙፍ አገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ ያደረገ ውይይት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ ነው
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ትኩረቱን በአባይ ግድብና በሌሎች ግዙፍ አገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ ያደረገ ውይይት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ ነው።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፍ (ዶክተር) በመድረኩ ላይ እነደተናገሩት፤ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ባህሪው ውሃ አመንጭቶ ወደ ታችኛው የተፋሰስ አገራት የሚፈስ ቢሆንም ከዚህ እወነታ በተቃራኒ የሚደረገው ጫናው መሰረት የሌለው ነው።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ አንድ አንደ ምእራባውያን አገራትና ሚዲያዎቻቸው በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጫና ለማሳደር ጥረዋል፤ ኢትዮጵያ ግን እውንትን ይዛ በመጓዝ የአባይ ግድብን ሶስተኛ ዙር ሙሌት አጠናቃ ሁለት ተርባይኖች ሃይል እያመነጩ ነው።
የዓባይ ግድብ ኢትዮጵያውያን ከተባበርንና አንድ ከሆን ሌሎች ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በመገንባት እድገት ማስመዝገብ ማሳያ ነው ብለዋል።
የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ እያደረጉ ያሉት ጥናት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ለተከታታይ አመታት በኢትዮጵያ ላይ እየደረሰ ያለውን ጫና የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረስብ ላደረገው ፍትሃዊ ትግል ምስጋና አቅርበዋል።
የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሀብታሙ አበበ በውይይቱ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ጥቂት ምእራባውያን አገራትና ግብጽ ጨምሮ ኢትዮጵያ እየገነባችው ባለው የአባይ ግድብ ሀሰተኛ መረጃዎችንና ጥናት ላይ ያልተመሰረቱ ሀሰተኛ መረጃዎችን ሚዲያዎቻቸውን ጨምሮ በማሰራጨት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ሲያሳድሩ ቆይተዋል ብለዋል።
ለናይል ወንዝ 86 በመቶ የሚሆነውን ውሃ የምትለቀው ኢትዮጵያ በሚገባው ልክ ሳታለማ ቆይትለች። 65 በመቶ የሚሆነውም ህዝቧ በጨለማ ውስጥ የሚኖር ነው። ስለዚህ የሚገነባው ግድብ በጨለማ ውስጥ የሚኖረውን ህዝብ ብርሃን እንዲገኝ ለማድረግ ነው ብለዋል።
በውይይቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፍ(ዶክተር)፣ ዶክተር ያቆብ አርሳኖ፣ ኢንጂነር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ፣ በካናዳ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ጥምረት ተወካዮችና ሌሎች ምሁራን ተገኝተዋል።
ለሁለት ቀናት የሚቆየው ውይይት ኢትዮጵያ እየገነባችው ባላው የአባይ ግድብና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ በሚደርስባት ጫና የዳያስፖራው፣ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሚና፣ የሃይድሮ ዲፕሎማሲን የተመለከቱ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የወጣው መርሃግብር ያሳያል።
ሞገስ ተስፋ( ሆሳዕና)
ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ወደ ሽሬ የመጀመሪያውን በረራ ማድረጉን ገለጸ
****************
(ኢ ፕ ድ)
ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ከሁለት ዓመት በኋላ የመጀመሪያው የሆነው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አውሮፕላን የሙከራ በረራ ዛሬ ሽሬ አየር ማረፊያ አርፏል ሲል አስታውቋል።
ወደ ትግራይ የሚደረጉ የአየር በረራዎች እንደገና መጀመራቸው አስቸኳይ ሰብአዊ እርዳታን በፍጥነት ወደ ክልሉ ለማድረስ ያግዛል::
ይህም አፋጣኝ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን በርካታ ሰዎች ስቃይ ለመቅረፍ ይረዳል ብሏል፤ ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ::
ብሔራዊ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚቴ የሰብዓዊ ርዳታ አቅርቦትና ተደራሽት ጉዳይ ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫን አስቀመጠ
****
(ኢ.ፕ.ድ)

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሚመራዉ ብሔራዊ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚቴ ዛሬ ባካሄደዉ አስቸኳይ ስብሰባ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትና ተደራሽነት ጉዳይ ላይ በመምክር የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

ኮሚቴዉ በአገሪቱ በሰዉ ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት የሰብአዊ እርዳታ የሚሹ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ገምግሟል፡፡ በድርቅ፣ በጎርፍ እና በግጭት ምክንያት ከቤት ንብረታቸዉ የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት የሚፈልግና የሁሉንም ዜጋ ርብርብ እንደሚፈልግ ተጠቁሟል፡፡

በትግራይ፣ አፋር፣ አማራና በሌሎች አካባቢዎች በግጭት ምክንያት ከቤት ንብረታቸዉ ለተፈናቀሉና ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች መንግስት አስቾኳይ የሰብአዊ ርዳታ በማድረስ ላይ መሆኑንና ለችግር የተጋለጡ ተረጂዎችን በዘላቂነት ማቋቋም እንደሚያስፈልግ የኮሚቴዉ ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አሳስበዋል፡፡

በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት ለችግር ከተጋለጡት ዜጎች ጎን ለጎን ባለፉት ዓመታት በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎች የሚገኙ ተረጂዎችም ትኩረት እንደሚሹ ተናግረዋል፡፡

በግጭት ምክንያት ከትምህርት ገበታቸዉ ርቀው የቆዩ ተማሪዎችና በተለያየ ምክንያት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችም ከሰብዓዊ ርዳታ በተጨማሪ የስነ-ልቦና ድጋፍ ሊደረግላቸዉ እንደሚገባም አቶ ደመቀ አሳስበዋል፡፡

የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትን በተመለከተ በሃገሪቱ ካላት የተረጂዎች ቁጥር አንፃር መንግስት ላይ የሚፈጥረዉ ጫና ከፍተኛ መሆኑን ያነሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉም ሴክተሮች ሃብት ማሰባሰብና ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች ለመድረስ መቀናጀት አለባቸው ብለዋል፡፡

የሰብአዊ ርዳታ ሰጪ ድርጅቶችና የልማት አጋሮችም ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻችንን ለማገዝ ባላቸው አቅም ሁሉ መረባረብ እንዳለባቸዉ ጥሪ ቀርቧል፡፡

የግብርናና የከተማ ሴፍትኔት መርሃ ግብሮችም የተረጂዎችን ህይወት በዘላቂነት ለመቀየር በሚያሰችል መልኩ ሊሰራባቸው እንደሚገባም ነው ያነሱት።

የሚመለከታቸዉ ሴክተሮች፣ የፌዴራልና የክልሎች የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ተቋማት ልምዳቸዉንና ሃብታቸዉን በማቀናጀት በእለት ተእለት እቅዳቸዉ ዉስጥ በማካተት መረባረብ እንዳለባቸዉና ዜጎች በዘላቂነት ከተረጂነት በሚላቀቁበት መንገድ ላይ አተኩረዉ መስራት እንዳለባቸዉም በአስቸኳይ ስብሰባው አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

ብሔራዊ ኮሚቴዉም በየሳምንቱ በመገናኘት የሰብአዊ ርዳታ ፍላጎት፣ አቅርቦትና ተደራሽነት ሁኔታን እየገመገመ ይቀጥላል ተብሏል፡፡
የፀረ ሙስና ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋም

ሙስና ሀገርን የሚበላ ነቀዝ ነው፡፡ የሀገርን አንጡራ ሀብት እየቦረቦረ ጥሪቷን ባዶ ለማስቀረት ሌት ተቀን የሚማስን ተባይ ነው። ዋልጌ ባለሥልጣናት፣ በፍቅረ ነዋይ የታወሩ ደላሎች እና ባለሃብቶች አንድ ላይ ሲገጥሙ፤ ከነዚህ የሌብነት ፊታውራሪዎች ጀርባ ብዛት ያላቸው ዜጎች መሰለፍ ሲጀምሩ ሙስና የተባለው ነቀዝ ሀገርን እንደ ወረርሽኝ ያጠቃታል፡፡

ሙስና በየትኛው ቦታና በየትኛውም ዘመን ሊኖር ይችላል፡፡ ነገር ግን የሀገርን ልማት አጥንቱ ድረስ እስከ መጋጥ ከደረሰ ሙስና አንድ አደገኛ ወረርሽኝ ሆኗል ማለት ነው፡፡ ሙስና ሀገርን ሊያፈርስ የሚችል የደኅንነት ሥጋት መሆኑን ያስመሰከሩ ሀገሮችን በዘመናችን አይተናል፡፡ የአደንዛዥ ዕጽ፣ የኮንትሮባንድ፣ ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ንግድ፣ የንግድ ማጭበርበር ሙስናን ለዓላማቸው ማስፈጸሚያነት ይፈልጉታል፡፡

በዓለማችን የተጀመሩ ጦርነቶች እንዳይጠናቀቁ፤ ግጭቶች እንዳይበርዱ፣ ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲጋጩ፣ ከሚያደርጓቸው ምክንያቶች አንዱ ሙሰኞች ከዚህ አይነት ቀውሶች ስለሚያተርፉ ነው፡፡

ሙስና ዛሬ የሀገራችን የደኅንነት ሥጋት ሆኗል፡፡ ወደ ብልጽግና የምናደርገውን ጉዞ እጅ ተወርች አሥሮ ለመያዝ ከጠላቶቻች እኩል ሙሰኛው እየታገለን ነው፡፡

የተስተካከለ ቢሮክራሲ፣ የተቀናጀ መዋቅርና ዘመናዊ አሠራር ለሙስና ተጋላጭነትን ስለሚቀንሱ፣ እነዚህን ለማጥፋት ወይም ለማሰናከል ሙሰኛው ቀን ከሌት እየሠራ ነው፡፡ሕዝባችን በአገልግሎት አሰጣጥ፣ ከመሬት ጋር በተያያዙ አሠራሮች፣ በፋይናንስ ዘርፍ፣ በሽያጭና ግዥ ሂደቶች፣ በፍትሕ አደባባዮች፣ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት፣ የልማት ድርጅቶች፣ የህዝብ ተቋማት ወዘተ. በሚያጋጥመው ሙስና እየተማረረ ነው፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ከሕዝብ ጋር በተደረጉ ውይይቶች ከጸጥታ ሥጋቶች እኩል ሙስና የብልጽግና ጉዟችን ዋናው ዕንቅፋት መሆኑን አንሥቷል፡፡

መንግሥት በየደረጃው የሚገኘውን መዋቅር በመፈተሽ፣ አዳዲስ አሠራሮችን በመዘርጋት፣ በቴክኖሎጂ የታገዙ ሥራዎችን እያሳለጠ ሥራዎችን ከእጅ ንክኪ ነጻ በማድረግ፣ በሙስና ወንጀል የሚሳተፉ አመራሮችንና ሌሎች ተዋንያንን ለሕግ በማቅረብ፣ ሙስና ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠርለት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ሀገራችን ያጋጠማትን ጦርነትና ኮሮናን የመሳሰሉ ወረርሽኞች የመንግሥትን ትኩረት ወስደዋል ብለው ያሰቡ ሙሰኞች፣ በየቦታው ተሠግሥገውና ኔት ወርክ ዘርግተው፣ ኢትዮጵያን ለማጥፋት እየሠሩ መሆናቸውን በዝርዝር የቀረበው የጥናት ሪፖርት ያሳያል፡፡ መንግሥት በጸጥታው ዘርፍ እንዳደረገው ሁሉ በሙስና ላይ ጠንካራና የማያዳግም ኦፕሬሽን ማድረግ እንዳለበት የጥናቱ ውጤትና የሕዝብ ውይይቱ ግምገማ ያመለክታል፡፡ በአንድ በኩል የመንግሥት ሕጎች፣ደንቦች፣ መመሪያዎችና አሠራሮች ለሙስና ያላቸውን ተጋላጭነት የማጥፋት ሥራ ይሠራል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሙስና ተዋንያንን የማጋለጥና በሕግ የመጠየቅ ተግባር ይከናወናል፡፡

መንግሥት በጥናት በደረሰባቸው የመንግሥት ሹመኞች፣ የመንግስት ተቋማት ሰራተኞች፣ አቀባባዮችና ጉቦ ሰጪዎች ላይ ምርመራ እያደረገ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ሙስና በባሕርዩ በረቀቀ መንገድ፣ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ አንዳንድ ጊዜም በሕጋዊነት ሽፋን የሚካሄድ በመሆኑ በመንግሥት ጥናት የተደረሰባቸው አካላትን ብቻ ለሕግ በማቅረብ የሚፈታ አይደለም፡፡ ሙስናን ከሥር ከመሠረቱ ለመንቀል እንዲቻል ከሕግና ከአሠራር ማሻሻያዎች በተጨማሪ፣ የሙስና ተዋንያን ሁሉ ሙስናን እርም እንዲሉ የሚያደርግ ርምጃ ያስፈልጋል፡፡መንግሥት በሙስና ላይ የሚያደርገውን ዘመቻ የሚያስተባብር፣ በጥናት ተለይተው ከቀረቡት በተጨማሪ ሌሎችንም ተዋንያን የሚለይና ለሕግ እንዲቀርቡ የሚያደርግ ብሔራዊ ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡

ብሔራዊ ከሚቴው ሰባት አባላት ያሉት ሲሆን፣ እነርሱም፡-
1. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
2. ዶ/ር ጌዴዎን ጢሞቴዎስ
3. አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ
4. አቶ ሰሎሞን ሶቃ
5. አቶ ደበሌ ቃበታ
6. ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ
7. አቶ አብዱሃሚድ መሃመድ ናቸው፡፡

ይህ የፀረ ሙስና ብሔራዊ ኮሚቴ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣትና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት እንዲችል የኅብረተሰቡ ሙሉ ትብብር እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ኅብረተሰቡ በሙስና ላይ በሚደረገው ዘመቻ ሊሳተፍ እንደሚገባ በተለያዩ መድረኮች ሲያነሣ ቆይቷል፡፡ መንግሥትም ይሄንን የሕዝብ ተሳትፎ በእጅጉ ይፈልገዋል፤ ምክንያቱም ሙስና በዋናነት የሚጠፋው ሕዝብ አምርሮ ሲታገለው ነውና፡፡

በመሆኑም ኅብረተሰቡ የሙስና ተዋንያንን በተመለከተ ያለውን መረጃ፣ ከቂምና ከበቀል ነጻ በሆነ መንገድ፣ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት አድራሻዎች ለብሔራዊ ኮሚቴው በመላክ ሙስናን ለማጥፋት በሚደረገው ትግል ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን፡፡ የሚቀርቡ ጥቆማዎች የጠቋሚዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ ተገቢውን ጥንቃቄ እና ሚስጥራዊነት በጠበቀ መንገድ ተይዘው ይመረመራሉ። ብሄራዊ ኮሚቴው የሚወስዳቸው እርምጃዎች እና የእንቅስቃሴው ውጤት በየጊዜው ለህዝብ ይፋ ይደረጋል። የየክልሉ ርእሳነ መስተዳድሮች በየደረጃው የሚሠሩ ክልላዊ ኮሚቴዎችን በቅርቡ እንደሚያቋቁሙ በዚሁ አጋጣሚ እንገልጣለን።

ስልክ ፡ 9555
አጭር የፅሁፍ መልዕክት : 9555
ድረ ገፅ ፡ http://www.9555pmo.et/
ኢሜይል : http://9555pmo.et/
ቴሌግራም ፡ https://news.1rj.ru/str/PMOfeedback
በመጀመሪያው ሩብ አመቱ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች መቋቋማቸውን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አስታወቀ
*********************
(ኢ ፕ ድ )
በተያዘው የበጀት አመት የመጀመሪያው ሩብ አመቱ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች መቋቋማቸውን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት ከክልል ኢንተርፕራይዝ ቢሮዎች ጋር የሩብ አመቱን አፈጻጸም በአዳማ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኢንተርፔራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ የሩብ አመቱን የእቅድ አፈጻጸምን ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት
በበጀት አመቱ አራት ሽህ 62 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ለማቋቋም እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው።
እንደ አቶ አብዱልፈታ ገለጻ፤ በሩብ አመቱ 551 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ለማቋቋም ታልሞ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ማቋቋም ተችሏል።
በሩብ አመቱ 258 ሚሊዮን ብር የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች መሰራጨቱንም አቶ አብዱልፈታ የሱፍ ተናግረዋል።
በሙሐመድ ሁሴን (አዳማ)
ልማት ባንክ የሦስተኛ ደረጃ ሕክምና ለሚሰጡ ተቋማት ብድር ሊሰጥ ነው
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ ሀገራት የሚሰጡ የሦስተኛ ደረጃ የሕክምና አገልግሎቶችን በሀገር ውስጥ መስጠት ለሚችሉ የጤና ተቋማት ብድር መስጠት ሊጀምር መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው እንደገለጹት፤ ባንኩ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ የሚደረጉ የሕክምና አገልግሎቶች በሀገር ውስጥ እንዲጀመሩ ለማስቻል የሦስተኛ ደረጃ ሕክምና የሚሰጡ ተቋማትን ለመደገፍ ተዘጋጅቷል። በዘርፉ ድጋፍ ለማግኘት ጥያቄ ያቀረቡ የጤና ተቋማት መኖራቸውን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ የብድር ፕሮጀክቱን በቀጣዮቹ አራት ወራት ለማፅደቅና ወደ ሥራ ለመግባት መታቀዱን ተናግረዋል።
እንደ ዶክተር ዮሐንስ ገለጻ፤ የጤናው ዘርፍ የፋይናንስ ድጋፍ ያስፈልገዋል። ለዚህ ደግሞ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ የሚገኘው የልማት ባንክ የፋይናንስ አጋር ሆኖ ለመቅረብ...
https://www.press.et/?p=85938