Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ለመካከለኛና ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ሥልጠና እየሰጠ ነው
******
(ኢ.ፕ.ድ)

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ለመካከለኛና ከፍተኛ የአገሪቱ ዲፕሎማቶች በውጭ ግንኙነትና በብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ዙሪያ በአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል ሥልጠና እየሰጠ ነው።

ሥልጠናውን እየሰጡ ያሉ የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ እንደ በለጸጉት ሀገራት ሃያል ባትሆንም በሃያላን ውሳኔ የሚመራ አለም ውስጥ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ሚናዋን በውል ማሳየት ያስፈልጋል።

በሥልጠናውም የአገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር፣ የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚጋፋ የሌላውን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ መመከት የሚያስችል ግንዛቤ እየተሰጠ ነው።

በዋቅሹም ፍቃዱ (ሱሉልታ)
ጊዜ ያቀናት የጣና የአብራክ ክፋይ- ቁንዝላ
****
(ኢ.ፕ.ድ)
የውቢቷ ባህር ዳር ጀንበር የማለዳ ፈገግታዋን ጣና ላይ ጣል አድርጋለች። በሰፊው ሀይቅ ላይ የተጋደመው ባህርም ከሩቅ ሲያማትሩት አይንን ይስባል። ድንግል ውበትና ማራኪ የተፈጥሮ ሀብት አቅፋ የምትጠብቀን የጣና የአብራክ ክፋይ ቁንዝላ መደረሻችን ሆናለች።

ቁንዝላ በደቡብ ምዕራብ ጣና ሀይቅ ላይ የምትገኝ ትንሽ የወደብ ከተማ ናት። ምንም እንኳን ከክልሉ ዋና ከተማ ቅርብ ርቀት ላይ ብትሆንም የተፈጥሮ ሀብቷን ትጠቀምበት ዘንድ ትኩረት ሳይሰጣት ቆይታለች። በርካቶች ቀለብ ይሰፍርልናል ብለው ተስፋ የጣሉበት ጣና ለቁንዝላ ባዕድ ሆኖባት ቆይቷል።

ክንፈ ሳፋፊዎቹ ፍጡራን ካልሆኑ በቀር የቁንዝላውን ጣና ሰው አይን አይኑን ብቻ እየተመለከተ ትውልድ እያለፈ ዛሬ ላይ ደርሰዋል። የውሃና መሬት ሀብት ማእከል ከዛሬ ሁለት ዓመታት ተኩል በፊት በአካባቢው የተፈጥሮ ሀብትን ጥቅም ላይ ለማዋል የአካባቢውን ማህበረሰብ ያማከለ ፕሮጀክት ነድፎ ሥራ መጀመሩ ቁንዝላ አዲስ ተስፋ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=86077
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከአራት ሺ በላይ ዜጎች በትራፊክ አደጋ ሕይወታቸውን እያጡ ነው
**
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢትዮጵያ ከ2010 ዓ.ም እስከ 2014 ዓ.ም በየዓመቱ 4ሺ 396 ዜጎች በትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት አስታወቀ።

የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አብዱልበር ሸምሱ በኢትዮጵያ ለ15ኛና በዓለም ደግሞ ለ17ኛ ጊዜ “እናስታውስ፣ እንደግፍ፣ ለውጥ እናምጣ” በሚል መሪ ቃል ታስቦ በዋለው የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች ማስታወሻ ቀን ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት፤ በየዓመቱ 4 ሺ 396 ሰዎች በትራፊክ አደጋ በሚደርስ ጉዳት ሕይወታቸው እያለፈ ነው።

በአገር አቀፍ ደረጃ ባሳለፍነው አንድ ዓመት ብቻ በፌዴራል ፖሊስ በቀረበ ሪፖርት 3 ሺ 971 ሞት፣ 5ሺ 586 የከባድ የአካል ጉዳት፣ 4ሺ 739 የቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ተረጋግጧልም ብለዋል።

አቶ አብዱልበር አክለውም፣ በትራፊክ አደጋ በደረሰ ጉዳት ሳቢያም ከሕይወት ህልፈት በዘለለ በንብረት ላይ በደረሰ ጉዳት ከ13 ቢሊዮን ብር በላይ ውድመት ደርሷል።

በኢትዮጵያ በመንገድ ትራፊክ አደጋ በቀን የ12 ሰዎች ሕይወት በአማካኝ ያልፋል ያሉት አቶ አብዱልበር፤ በቀን...
https://www.press.et/?p=86076
«ስምምነቱ ለፓን-አፍሪካኒዝም መጠናከር ትልቅ ጥቅም አለው» - አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን
***
(ኢ.ፕ.ድ)
በፌዴራል መንግሥትና በሕወሓት መካከል በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተደረገው የሰላም ስምምነት ለፓን-አፍሪካኒዝም መጠናከር ትልቅ ጥቅም ያለው መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና የአሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር እሸቴ ጥላሁን አስታወቁ።

አምባሳደር እሸቴ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ በፌዴራል መንግሥትና በሕወሓት መካከል በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ የተደረገው የሰላም ስምምነት ለፓን-አፍሪካኒዝም መጠናከር ትልቅ ጥቅም ያለውና አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን በራሳቸው መፍታት እንደሚችሉ ማሳያ ነው። በተለይም የህብረቱ ዋና መቀመጫ እንዲሁም ለፓን- አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ ለሆነችውና ሌሎችን አነሳስታ ለዚህ አስተሳሰብ መሪ ሚና ለነበራት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ትርጉም አለው።

የፓን-አፍሪካኒዝም ዋናው መነሻው የአስተሳሰቡ ማዕቀፍ አፍሪካውያን የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን መምራት....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=86066
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ
👉በተጽዕኖዎች ውስጥ ዕድገት ማስመዝገቡ የማክሮ
ኢኮኖሚው ሥራ ውጤት ነው
👉ለተመዘገበው ዕድገት ግብርና ዋነኛው ሞተር ነው
👉የነፍስ ወከፍ ገቢው በተለያየ መንገድ ዜጎች ጋር
ይደርሳል
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት መንግሥት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ያከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ውጤት ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስቴርና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታወቁ።

የገንዘብ ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ እና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍፁም አሰፋ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ዶክተር ፍፁም አሰፋ፤ በሰሜኑ ጦርነት፣ በኮቪድ ወረርሽኝ በድርቅ እንዲሁም ምዕራባውያን በፈጠሩት ጫና የፋይናንስ እጥረት ኢኮኖሚው በተለያዩ ፈተናዎች ማለፉን ገልጸዋል።

በተለያዩ ተጽዕኖዎች አልፋ ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የስድስት ነጥብ አራት በመቶ ዕድገት በግብርናው፣ በአገልግሎት ዘርፉና በተለያዩ ዘርፎች ላይ በተከናወነው የማክሮ ኢኮኖሚ ሥራ ውጤት የመጣ መሆኑን ችግሮች ባሉበት ወቅት ከማዳበሪያ አቅርቦት እስከ ሜካናይዜሽን አቅርቦት ሰፊ ስራ ተከናውኗል፤ ዝናብን እና ወቅት ጠብቆ ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ አርሶ አደሩ እንዲያመርት ትልቅ ጥረት ተደርጓል። መንግሥት 50 ሺህ የውሃ ፓምፖችን በማከፋፈል ምርታማነትን ለማሳደግ ያደረገው ጥረት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=86068
የማክሮ ኢኮኖሚ ቡድን አባል የሆኑት የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶክተር ፍጹም አስፋ ይናገራሉ ‼️

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 126 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፤

👉 የኢትዮጵያውያን የነፍስ ወከፍ ገቢ አንድ ሺህ 212 ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል፤

👉 የነፍስ ወከፍ ገቢያችን አደገ ሲባል ግን እኩል በእያንዳንዳችን ኪስ የሚገባ አይደለም፤

👉 እንደየስራችንና ልፋታችን መጠን ባመረትነውና በተሳተፍንበት ልክ ይደርሰናል፤

👉 ብዙ የሰሩና ያመረቱ ከፍተኛ ገቢ ያገኛሉ፤

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት መንግሥት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ያከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ውጤት ነው፤

👉 በሰሜኑ ጦርነት፣ በኮቪድ ወረርሽኝ በድርቅ እንዲሁም ምዕራባውያን በፈጠሩት ጫና የፋይናንስ እጥረት ኢኮኖሚው በተለያዩ ፈተናዎች አልፏል፤

👉 በተለያዩ ተጽዕኖዎች አልፋ ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የስድስት ነጥብ አራት በመቶ ዕድገት በግብርናው፣ በአገልግሎት ዘርፉና በተለያዩ ዘርፎች ላይ በተከናወነው የማክሮ ኢኮኖሚ ሥራ ውጤት የመጣ ነው፤

👉 ችግሮች ባሉበት ወቅት ከማዳበሪያ አቅርቦት እስከ ሜካናይዜሽን አቅርቦት ሰፊ ስራ ተከናውኗል፤

👉 ዝናብን እና ወቅትን ጠብቆ ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ አርሶ አደሩ እንዲያመርት ትልቅ ጥረት ተደርጓል፤

👉 መንግሥት 50 ሺህ የውሃ ፓምፖችን በማከፋፈል ምርታማነትን ለማሳደግ ያደረገው ጥረት ለውጤቱ መመዝገብ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤

👉 በግብርና ዘርፍ በምግብ ራስን ለመቻል በተደረገ ጥረት ምርታማነት በማሳደግ የስንዴ ግዥ የውጭ ምንዛሬን ያስቀረ ስራ ተከናውኗል፤

👉 ከግብርናው ባለፈ የአገልግሎት ዘርፉም የኢኮኖሚ ዕድገቱ ወሳኝ ነበር፤

👉 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገኘው ገቢ ኢኮኖሚያችን በችግር ውስጥም ሆኖውጤታማ እንዲሆን ያገዘ ነው፤

👉 የማክሮ ኢኮኖሚው ውሳኔዎች ኢኮኖሚውን የሚገዳደሩ የዋጋ ግሽበትና ዘርፈ ብዙ ችግሮችን መቋቋም አስችሏል፤

👉 አንድ ኢኮኖሚ የዋጋ ግሽበቱን እስከ 40 በመቶ ከገታ ዕድገቱን ማቆየት ይችላል፤

👉 የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ያን ያህል ስላልደረሰ ዕድገቱ ማስቀጠል እንችላለን፤

👉 አካታችነት ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ስራ የስራ ዕድል ፈጠራ ኢንቨስትመንትና ልማትን አስተሳስሮ መሄድ ተችሏል፤

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 126 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፤

👉 የኢትዮጵያውያን የነፍስ ወከፍ ገቢ አንድ ሺህ 212 ዶላር ሆኖ ተመዝግቧል፤

👉 የነፍስ ወከፍ ገቢያችን አደገ ሲባል ግን ያን እኩል በእያንዳንዳችን ኪስ የሚገባ አይደለም፤

👉 እንደየስራችንና ልፋታችን መጠን ባመረትነውና በተሳተፍንበት ልክ ይደርሰናል፤

👉 ብዙ የሰሩና ያመረቱ ከፍተኛ ገቢ ያገኛሉ፤

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ‼️

https://youtu.be/RRUFwSUMDaU