አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 60ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ኤክስፖ ሊዘጋጅ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሜጋ ሰፕሊ ኢንጂነሪንግ ጋር በመተባበር አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ “አንድ አፍሪካ ኤክስፖ” በሚል መሪ ቃል ከግንቦት 17 እስከ 19 በሳይንስ ሙዚየም ኤክስፖ ሊያዘጋጅ ነው።
ኤክስፖውን አስመልክቶ ጋዜጣው መግለጫ የሰጡት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር አብዱ ያሲን እንደገለጹት፣ በነጮች ግንቦት 25 አፍሪካ ክብረት የተመሰረተበትን 60ኛ አመት ያከብራል። በኤክስፖው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ይበልጥ ታጸናለች ብለዋል።
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ከ60 አመት በፊት ሲመሰረት ዋና አላማው አፓርታይድን ማስወጣት ነው ያሉት አምባሳደሩ፣ ስሙን ወደ አፍሪካ ህብረት ከለወጠ ወዲህ ደግሞ አፍሪካውያን በኢኮኖሚ ጠንካራ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል። አፍሪካውያን እርስ በርስ በንግድና በገበያ እንዲተሳሰሩ በፖሊሲ የተደገፍ ስራ እየተሰራ ነው። የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ተግባራዊ እንዲሆን ኢትዮጵያ ጠንክራ እየሰራች ነው።
በኤክስፓውን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ዲፕሎማሲዋን የምታጠናክርበት ይሆናል ብለዋል።
የአንድ አፍሪካ ኤክስፖ አዘጋጅ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሳሙኤል መብራቱ በበኩላቸው፣ የሚዘጋጀው ኤክስፖ የአፍሪካን የ60 አመት ጉዞ የሚገመግም ነው። አፍሪካ ነጻ ከወጣች በኋላ በአለም መድረክ ያላትን ተቀባይነትና አፍሪካውያን ያላቸውን የባህል፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ግንኙነትም እንዲጠንክር ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል።
የሚዘጋጀው ኤክስፖ አዲስ አበባ የፖለቲካ ዲፕሎማ ማእከልነቷን እንድታጸና ያግዛል ያሉት የቦርድ ሰብሳቢው፣ ኤክስፖው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ፣ አፍሪካ ከአለም ጋር ያላቸውን ግንኙነት ያጠናክራል። የተጀመረውን ነጻ የንግድ ቀጠናን ያጠናክራል ብለዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሜጋ ሰፕሊ ኢንጂነሪንግ ጋር በመተባበር አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ “አንድ አፍሪካ ኤክስፖ” በሚል መሪ ቃል ከግንቦት 17 እስከ 19 በሳይንስ ሙዚየም ኤክስፖ ሊያዘጋጅ ነው።
ኤክስፖውን አስመልክቶ ጋዜጣው መግለጫ የሰጡት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር አብዱ ያሲን እንደገለጹት፣ በነጮች ግንቦት 25 አፍሪካ ክብረት የተመሰረተበትን 60ኛ አመት ያከብራል። በኤክስፖው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ይበልጥ ታጸናለች ብለዋል።
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ከ60 አመት በፊት ሲመሰረት ዋና አላማው አፓርታይድን ማስወጣት ነው ያሉት አምባሳደሩ፣ ስሙን ወደ አፍሪካ ህብረት ከለወጠ ወዲህ ደግሞ አፍሪካውያን በኢኮኖሚ ጠንካራ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል። አፍሪካውያን እርስ በርስ በንግድና በገበያ እንዲተሳሰሩ በፖሊሲ የተደገፍ ስራ እየተሰራ ነው። የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ተግባራዊ እንዲሆን ኢትዮጵያ ጠንክራ እየሰራች ነው።
በኤክስፓውን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ዲፕሎማሲዋን የምታጠናክርበት ይሆናል ብለዋል።
የአንድ አፍሪካ ኤክስፖ አዘጋጅ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሳሙኤል መብራቱ በበኩላቸው፣ የሚዘጋጀው ኤክስፖ የአፍሪካን የ60 አመት ጉዞ የሚገመግም ነው። አፍሪካ ነጻ ከወጣች በኋላ በአለም መድረክ ያላትን ተቀባይነትና አፍሪካውያን ያላቸውን የባህል፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ግንኙነትም እንዲጠንክር ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል።
የሚዘጋጀው ኤክስፖ አዲስ አበባ የፖለቲካ ዲፕሎማ ማእከልነቷን እንድታጸና ያግዛል ያሉት የቦርድ ሰብሳቢው፣ ኤክስፖው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ፣ አፍሪካ ከአለም ጋር ያላቸውን ግንኙነት ያጠናክራል። የተጀመረውን ነጻ የንግድ ቀጠናን ያጠናክራል ብለዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
አቶ ጥራቱ በየነ የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽንና የአርሶአደርና የከተማ ግብርና ውጤትን ጉበኙ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ ከቤተ ሙከራ እስከ አዝመራ" በሚል መሪ ሀሳብ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የተከፈተውን የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽንና "ምግባችን ከደጃችን" በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ የተጀመረውን የአርሶአደርና የከተማ ግብርና ውጤት ዛሬ ጎብኝተዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት፣ የተፈጥሮ ሀብትን በመጠቀም ዜጐችን በአግባቡ ወደ ስራ በማስገባት መበልጸግ እንደሚቻል በኤግዚቢሽኑ ላይ የታዩ ውጤቶች ማሳያ ናቸው።
ከ2014 አ.ም በወረዳዎችና ክፍለከተሞች በንቅናቄ መልክ መተግበር የጀመረው " ምግባችን ከዳጃችን" የከተማ ግብርና በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።
የከተማ ግብርና የዜጐችን ኑሮ በማሻሻልና የስራ እድልን በመፍጠር ተጨባጭ ውጤት እያሳየ እንዳለም ጥቅሰዋል።
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው፣ ግብርና የአገሪቱ የጀርባ አጥንት መሆኑንና ከእጅ ወደ አፍ የነበረው የግብርና ስራ በአሁን ወቅት ወደ ዘመናዊነት በመሸጋገር የከተማ ዜጐችን ጭምር ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በግብርና ሚኒስቴር አዘጋጅነት "ከቤተ ሙከራ እስከ አዝመራ" በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም ይፋ የሆነው የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽን ከሳምንት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ መከፈቱ ይታወሳል።
በአሁን ወቅትም ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ዜጐች እየጐበኙ ይገኛሉ።
በአዲሱ ገረመው
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥራቱ በየነ ከቤተ ሙከራ እስከ አዝመራ" በሚል መሪ ሀሳብ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የተከፈተውን የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽንና "ምግባችን ከደጃችን" በሚል መሪ ቃል በከተማ ደረጃ የተጀመረውን የአርሶአደርና የከተማ ግብርና ውጤት ዛሬ ጎብኝተዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ በጉብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት፣ የተፈጥሮ ሀብትን በመጠቀም ዜጐችን በአግባቡ ወደ ስራ በማስገባት መበልጸግ እንደሚቻል በኤግዚቢሽኑ ላይ የታዩ ውጤቶች ማሳያ ናቸው።
ከ2014 አ.ም በወረዳዎችና ክፍለከተሞች በንቅናቄ መልክ መተግበር የጀመረው " ምግባችን ከዳጃችን" የከተማ ግብርና በርካቶችን ተጠቃሚ ያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።
የከተማ ግብርና የዜጐችን ኑሮ በማሻሻልና የስራ እድልን በመፍጠር ተጨባጭ ውጤት እያሳየ እንዳለም ጥቅሰዋል።
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው፣ ግብርና የአገሪቱ የጀርባ አጥንት መሆኑንና ከእጅ ወደ አፍ የነበረው የግብርና ስራ በአሁን ወቅት ወደ ዘመናዊነት በመሸጋገር የከተማ ዜጐችን ጭምር ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በግብርና ሚኒስቴር አዘጋጅነት "ከቤተ ሙከራ እስከ አዝመራ" በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም ይፋ የሆነው የግብርና ሳይንስ ኤግዚቢሽን ከሳምንት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ መከፈቱ ይታወሳል።
በአሁን ወቅትም ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ዜጐች እየጐበኙ ይገኛሉ።
በአዲሱ ገረመው
አቶ ደመቀ መኮንን በቤላሩስ የኢትዮጵያ የክብር ቆንስል ከሆኑት ሚስተር ዲሚትሪ ሉካሼንኮ ጋር ተወያዩ
******************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በቤላሩስ የኢትዮጵያ የክብር ቆንስል የሆኑትን ሚስተር ዲሚትሪ ሉካሼንኮን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
የክብር ቆንስሉ በምስራቅ አውሮፓዊቷ ሀገር ኢትዮጵያንና ህዝቧን በመወከል እያበረከቱት ስላለው አስተዋጽኦ አቶ ደመቀ ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮያ እና ቤላሩስ በተለይ በኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ ግብርና ሜካናይዜሽን እና ማዕድን ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ይበልጥ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል። "ይህን ለማሳካት በእኛ በኩል የምንችለውን እናደርጋለን" ብለዋል።
ሚስተር ዲሚትሪ ሉካሼንኮ በበኩላቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቲዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
******************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በቤላሩስ የኢትዮጵያ የክብር ቆንስል የሆኑትን ሚስተር ዲሚትሪ ሉካሼንኮን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
የክብር ቆንስሉ በምስራቅ አውሮፓዊቷ ሀገር ኢትዮጵያንና ህዝቧን በመወከል እያበረከቱት ስላለው አስተዋጽኦ አቶ ደመቀ ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮያ እና ቤላሩስ በተለይ በኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ ግብርና ሜካናይዜሽን እና ማዕድን ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ይበልጥ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል። "ይህን ለማሳካት በእኛ በኩል የምንችለውን እናደርጋለን" ብለዋል።
ሚስተር ዲሚትሪ ሉካሼንኮ በበኩላቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቲዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ለሱዳን ስደተኞች ድጋፍ ለማድረግ የፌዴራል መንግስት ግብረ ኃይል አቋቁሞ እየሰራ ነው
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሱዳን ጦርነትን ተከትሎ ወደኢትዮጵያ ለሚመጡ ስደተኞች ድጋፍ ለማድረግ በፌዴራል መንግስት ደረጃ ግብረኃይል ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሱዳን የተከሰተውን የእርስ በርስ ግጭት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99673
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሱዳን ጦርነትን ተከትሎ ወደኢትዮጵያ ለሚመጡ ስደተኞች ድጋፍ ለማድረግ በፌዴራል መንግስት ደረጃ ግብረኃይል ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሱዳን የተከሰተውን የእርስ በርስ ግጭት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99673
“ወዳጅ እንዲኮራ፣ ጠላት እንዲፈራ መስራት ብቻ ሳይሆን የሰራነውን ማሳየት አለብን"
- አቶ ተመስገን ጥሩነህ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
************************
(ኢ ፕ ድ)
ወዳጅ እንዲኮራ፣ ጠላት እንዲፈራ፤ ወዳጅ እንዲተማመን፣ ጠላት እንዲመነምን መስራት ብቻ ሳይሆን የሰራነውን ማሳየት አለብን ሲሉ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ፡፡
በብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ባለቤትነት በእውነተኛ ታሪክ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99679
- አቶ ተመስገን ጥሩነህ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
************************
(ኢ ፕ ድ)
ወዳጅ እንዲኮራ፣ ጠላት እንዲፈራ፤ ወዳጅ እንዲተማመን፣ ጠላት እንዲመነምን መስራት ብቻ ሳይሆን የሰራነውን ማሳየት አለብን ሲሉ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ፡፡
በብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ባለቤትነት በእውነተኛ ታሪክ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99679
ከ59 ሺህ በላይ የመዲናዋ ነዋሪዎች በከተማ ግብርና ላይ እየተሳተፉ ነው
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና የሚሳተፉ ዜጎች ቁጥር ከ59 ሺህ በላይ መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አካሌ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመዲናዋ በከተማ ግብርናና ሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ዜጎች በስፋት እንዲሳተፉ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
በዘጠኝ ወራት በእንስሳት ዘርፍ 17 ሺህ 224፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ 42 ሺህ 374 በድምሩ 59 ሺህ 571 ዜጎች በከተማ ግብርና ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ሲሉ አስታውቀዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99689
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና የሚሳተፉ ዜጎች ቁጥር ከ59 ሺህ በላይ መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አካሌ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመዲናዋ በከተማ ግብርናና ሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ዜጎች በስፋት እንዲሳተፉ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
በዘጠኝ ወራት በእንስሳት ዘርፍ 17 ሺህ 224፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ 42 ሺህ 374 በድምሩ 59 ሺህ 571 ዜጎች በከተማ ግብርና ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ሲሉ አስታውቀዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99689
የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑክ በ ’ላፕሴት’ ፕሮጀክት ስብስባ ላይ ለመሳተፍ ጁባ ገባ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑክ በ ’ላፕሴት’ ፕሮጀክት ስብስባ ላይ ለመሳተፍ ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል።
ልዑኩ ጁባ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማሃዲ አቀባበል አድርገውለታል።
የኢትዮጵያ መንግስት ልዑክ በደቡብ ሱዳን በሚኖረው ቆይታ ኢትዮጵያ፣ኬንያና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት ለማስተሳሰር ያለመው ላፕሴት ፕሮጀክት አስመልክቶ በተዘጋጀው ውይይት ላይ እንደሚሳተፍ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በተጨማሪም ከደቡብ ሱዳን የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽና የጋራ ፍላጎት በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
የላፕሴት ፕሮጀክት እ.አ.አ በ2012 በኢትዮጵያ፣ኬንያና ደቡብ ሱዳን አገራት መሪዎች የጋራ ስምምነት ወደ ስራ እንዲገባ ውሳኔ መተላለፉ የሚታወስ ነው።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑክ በ ’ላፕሴት’ ፕሮጀክት ስብስባ ላይ ለመሳተፍ ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል።
ልዑኩ ጁባ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማሃዲ አቀባበል አድርገውለታል።
የኢትዮጵያ መንግስት ልዑክ በደቡብ ሱዳን በሚኖረው ቆይታ ኢትዮጵያ፣ኬንያና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት ለማስተሳሰር ያለመው ላፕሴት ፕሮጀክት አስመልክቶ በተዘጋጀው ውይይት ላይ እንደሚሳተፍ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በተጨማሪም ከደቡብ ሱዳን የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽና የጋራ ፍላጎት በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
የላፕሴት ፕሮጀክት እ.አ.አ በ2012 በኢትዮጵያ፣ኬንያና ደቡብ ሱዳን አገራት መሪዎች የጋራ ስምምነት ወደ ስራ እንዲገባ ውሳኔ መተላለፉ የሚታወስ ነው።