Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከካናዳ አለም አቀፍ የልማት ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ላይ እየተሰሩ ያሉና ውጤት የተመዘገበባቸውን የግብርና ልማት ስራዎችን ለካናዳ አለም አቀፍ የልማት ሚኒስትር እና ለልዑካን ቡድናቸው አብራርተዋል፡፡
https://www.facebook.com/ethiopianpressagency/posts/pfbid024WHX3cyhJwPwbQ3B6s3uftQ7kPBmpNhe3Tvavr3npLVD2yzu1wkzA5Lrd6vQFRsBl
የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ለማዛወር በወጣው ጨረታ ከ20 በላይ ድርጅቶች ለመሳተፍ ፍላጎት ማሳየታቸው የገንዘብ ሚኒስቴር አሰታወቀ
*******
(ኢ ፕ ድ)
መንግስት ስምንት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ለማዛወር ባወጣው ዓለም አቀፍ ጨረታ ከ20 በላይ ኩባንያዎች በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ማሳየታቸው የገንዘብ ሚኒስቴር አሰታወቀ።

በመንግስት የተያዙ 8 የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ለማዛወር መንግስት ዓለም አቀፍ ጨረታ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡

ፋብሪካዎቹም አርጆ ዴዴሳ፣ ከሰም፣ ኦሞ ኩራዝ 1፣ ኦሞ ኩራዝ 2፣ ኦሞ ኩራዝ 3፣ ኦሞ ኩራዝ 5፣ ጣና በለስና ተንዳሆ ናቸው።

ከ20 በላይ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መንግስት ባወጣው ጨረታ ላይ ለማሳተፍ ፍላጎት አሳይተዋል። በዚህም የጨረታ ማስረከቢያውን ሂደት የሚገልጽ አጠቃላይ የጨረታ ሰነድ መውጣቱ ተገልጿል።
“ግብጽ የአረብ ሊግ መሪነቷን በመጠቀም የዓባይ ግድብ ላይ ያላትን ኢፍትሃዊ ፍላጎት ለማሳካት እየሞከረች ነው‘
- ዶክተር ያዕቆብ አርሳኖ የውሃ ፖለቲካ ተመራማሪ
************************
(ኢ ፕ ድ)
ግብጽ የአረብ ሊግ መሪነቷን በመጠቀም በዓባይ ግድብ ላይ ያላትን ኢፍትሃዊ ፍላጎት ለማሳካት እየሞከረች መሆኑን የውሃ ፖለቲካ ተመራማሪና የዓባይ ግድብ ዓለም አቀፍ ተደራዳሪ ዶክተር ያዕቆብ አርሳኖ ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለአረብ ሊግ መግለጫ የሰጠው ምላሽ የዓለምአቀፍ ማህበረሰቡ እውነታውን....https://www.facebook.com/ethiopianpressagency/posts/pfbid02Jk8ggfZdKWPLZD6rXpv3SN9cGH3kfnHr993DQgsnAN36eXwpou9EQchVHBK2n849l
በአማራ ክልል 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል አምሥተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ መርሃ ግብር አንድ ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። እስካሁን ከ850 ሺህ በላይ ችግኞች ለተከላ ደርሰዋል።
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር አልማዝ ግዜው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመጪው.....https://www.facebook.com/ethiopianpressagency/posts/pfbid05QP2yzAZFed9NjER5mZggH72e8AgJk9NuaCHveQzrcxxZXwBcqnpijKoYXzybEgBl
የቀደምት አፍሪካውያን መሪዎችን ራዕይ እውን ለማድረግ ቁርጠኛ መሆን ይገባል
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ህብረትን 60ኛ ዓመት ስናከብር ቀደምት የአፍሪካ መሪዎች ጠንካራና አንድነቷ የተጠበቀ አህጉር ለመፍጠር የነበራቸውን ራዕይ እውን ለማድረግ መትጋት እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ።
ሚኒስትር ዴኤታው የአፍሪካ ህብረት የተመሠረተበትን 60ኛ ዓመት በማስመልከት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ባዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ ባደረጉት ንግግር እንዳሉት፤ ቀደምት የአፍሪካ ....https://www.facebook.com/ethiopianpressagency/posts/pfbid02zJkGnvJKHtLLFTFZXiSBfEgNu8N8d8yxgfrWwqri5Lwju1ZpyYqYtWvJ8neQdiKfl
የጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ9 ወራት ውስጥ ከሰባት መቶ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ውስጥ 701 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ንጉሴ እንደገለፁት ማመንጫ ጣቢያው በዘጠኝ ወራት ውስጥ ለማመንጨት ካቀደው....https://www.facebook.com/ethiopianpressagency/posts/pfbid02K5u9Y7XjWruPG38bLd4c9qnTNiq59bJCwPm8sutmaRw6F2XEJKawGLrHoK7PcvcAl
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
በዴንቨር በነበረን ቆይታ በጋራ ለመስራት የለየናቸው ዘርፎች ወደ ተግባር በሚለወጡባቸው መንገዶች ዙሪያ ከከንቲባ ማይክል ሃንኮክ፣ ከከተማው አመራሮች እና የንግድ ምክር ቤት ኃላፊዎች ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
ለዴንቨር ከተማ የንግድ ምክር ቤት ኃላፊዎችና አባላት ስለ ከተማችን ሰፋ ያለ ገለፃ አድርገንላቸዎል። ኃላፊዎቹ አዲስ አበባን ውብ ለማድረግ የጀመርናቸውን ስራዎችን አድንቀው ለከተማ እድገት የግሉን ዘርፍ ከመንግስት ጋር በቅንጅት መስራት ስላለው ትልቅ ፋይዳ ልምዳቸዉን አካፍለውናል።
በከተማችን አዲስ አበባ ብዛት ያለው የተማረ ወጣት እንደመኖሩ በዴንቨር ያሉ ተቋማትን በማስተባበር ለወጣቱ የስራ እድል የሚፈጥሩ አገልግሎቶቻቸውን ወደ አዲስ አበባ ማምጣትና ተደራሽ ማድረግ እንዲሁም በተለዩ ዘርፎች ላይ በቅርበት መስራት ለሁለቱም ከተሞች በሚያስገኘው ፋይዳ ዙሪያ በዝርዝር ተወያይተናል።
በዴንቨር ከተማ ከአቀባበል ጀምሮ ለቆይታችን ስኬታማነት፣ በተለይም ለተደረገልን ልዩ መስተንግዶ ሁሉ ከንቲባ ሃንኮክን እና ባልደረቦቻቸውን በድጋሚ ላመሰግን እወዳለሁ።
ጤፍን በዘመናዊ መንገድ በመዝራት ብክነትን የሚከላከል ቴክኖሎጂ እየለማ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ )
ጤፍን በማሽን በመዝራት በአበባ ወቅት የሚከሰተውን የምርት ብክነት ለመከላከል የሚያስችል ቴክኖሎጂ እየለማ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በግብርና ሚኒስቴር የአግሮኖሚስት ባለሙያው አቶ ምትኩ በጅጋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ እንደ አገር ጤፍ በባህላዊ መንገድ ሲዘራ በአበባ ወቅት መሬት ላይ ወድቆ የሚበሰብስበት ሁኔታ ይስተዋላል። የጤፍ ሰብል መሬት ላይ የሚወድቀው ዋናው ምክንያት የዘር መጠኑ በጣም ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ነው። በመሆኑም ይህንን ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100393