የሃስት ሰነዶችን ሲያዘጋጁ የነበሩ ወንጀል ፈጻሚዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ማህተሞችን በመጠቀም የሃስት ሰነዶች ሲያዘጋጁ የነበሩ ወንጀል ፈጻሚዎች የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ዘርፍና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ ባደረጉት ክትትል በቁጥጥር ሥር ዋሉ።
አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ የተባለው ግለሰብና ግብረአበሮቹ በአራዳ ክፍለ ከተማ 511 ማህተሞችን በመጠቀም የሃሰት የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሰነዶች ሲያዘጋጅ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ከ1500 እስከ 4500 ብር በማስከፈል የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት የወንጀል ተግባር ሲፈፅሙ እንደነበር ተገልጿል።
ወንጀል ፈጻሚው አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ እና ግብረአበሮቹ ሃስተኛ የሆኑ የመከላኪያ ሠራዊት የስንብት ወረቀት፣ የመከላከያ የፍቃድ ወረቀት፣ የብሔራዊ መረጃ መታወቂያ፣ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ፣ የመከላከያ ልዩ ዘመቻ ም/አዛዥ ሻ/ቃ፣ የመከላከያ ሠራዊት መታወቂያ አዘጋጅተው ተይዟል።
በተጨማሪም ግለሰቦቹ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የፌደራል አስተዳደር ፓሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዳይሬክቶሬት፣ የፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ማዕከላዊ፣ 31ኛ ክፍለ ጦር መምሪያ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሉ የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት ለወንጀል መፈጸሚያ እንዲውሉ ሲሰሩ እንደነበረ በኤግዚቢትነት የተያዙ ማስረጃዎች ያሳያሉ ሲል የአዲስ አበባ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ማህተሞችን በመጠቀም የሃስት ሰነዶች ሲያዘጋጁ የነበሩ ወንጀል ፈጻሚዎች የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ዘርፍና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ ባደረጉት ክትትል በቁጥጥር ሥር ዋሉ።
አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ የተባለው ግለሰብና ግብረአበሮቹ በአራዳ ክፍለ ከተማ 511 ማህተሞችን በመጠቀም የሃሰት የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሰነዶች ሲያዘጋጅ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ከ1500 እስከ 4500 ብር በማስከፈል የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት የወንጀል ተግባር ሲፈፅሙ እንደነበር ተገልጿል።
ወንጀል ፈጻሚው አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ እና ግብረአበሮቹ ሃስተኛ የሆኑ የመከላኪያ ሠራዊት የስንብት ወረቀት፣ የመከላከያ የፍቃድ ወረቀት፣ የብሔራዊ መረጃ መታወቂያ፣ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ፣ የመከላከያ ልዩ ዘመቻ ም/አዛዥ ሻ/ቃ፣ የመከላከያ ሠራዊት መታወቂያ አዘጋጅተው ተይዟል።
በተጨማሪም ግለሰቦቹ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የፌደራል አስተዳደር ፓሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዳይሬክቶሬት፣ የፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ማዕከላዊ፣ 31ኛ ክፍለ ጦር መምሪያ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሉ የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት ለወንጀል መፈጸሚያ እንዲውሉ ሲሰሩ እንደነበረ በኤግዚቢትነት የተያዙ ማስረጃዎች ያሳያሉ ሲል የአዲስ አበባ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
የአረብ ሊግ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የያዘው አቋም በወንድማማች የኢትዮጵያና የግብጽ ህዝቦች መካከል መጠራጠርን የሚፈጥር ነው-አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽ
******
(ኢ ፕ ድ)
የአረብ ሊግ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የያዘው አቋም በወንድማማች የኢትዮጵያና ግብጽ ህዝቦች መካከል ልዩነትና መጠራጠርን የሚፈጥር አካሄድ መሆኑን የውኃ ኃብት አስተዳደር አማካሪው አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽ ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ያለውን እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማስረዳት ከሌላ አቅጣጫ የሚሰነዘርባትን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ማክሸፍ ይኖርባታል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ያደረገ ጥናት በማከናወን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከጀመረች አስር ዓመታት አልፈዋል፡፡
ግድቡ ኢትዮጵያ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን በመከተል በተፋሰሱ ሀገራት ላይ ጉልህ ጉዳት በማያደርስ መልኩ ከላይኛውና ታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር በጋራ የመልማት አላማ እንዳላት የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው፡፡
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን በተፈጥሮ ሀብቷ መልማትና መጠቀም የማይፈልጉ አካላት፤ የግድቡን ግንባታ በሚመለከት ያልፈረመቻቸውን የአንድ ወገን የቅኝ ግዛት ስምምነቶች በማንሳት ይቃወማሉ።
የነዚህ አካላት ሚዛን የሌለውና እውነታ ላይ ያልተመሰረተ አካሄድ ኢትዮጵያ ዛሬም በድህነት እንድትማቅቅ ከመፈለግ የመነጨ መሆኑን ምሁራን ይገልጻሉ።
ከዚህም ባለፈ ከዓለም አቀፍ የወሰን ተሻጋሪ ወንዞች የውሃ አጠቃቀም ህግ ባፈነገጠ መልኩ በሶስተኛ ወገን አማካኝነት ተፅዕኖ ለመፍጠር ሲሞክሩ ይታያሉ፡፡
የውኃ ኃብት አስተዳደር አማካሪው አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በወሰን ተሻጋሪ ወንዞች መካከል የሚፈጠረውን ልዩነት በተመለከተ የሶስተኛ ወገን ጣልቃ ባይገባ ተመራጭ ነው፡፡
በወሰን ተሻጋሪ የውሃ አጠቃቀም ዙሪያ ያሉ ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሚፈልጉ ሶስተኛ ወገኖች ቢኖሩም አብዛኞቹ የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር የሚሞክሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የአረብ ሊግን ጨምሮ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ጣልቃ ለመግባት የሚሞክሩ አካላት የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ ዘላቂ ተጠቃሚነት ከማጎልበት ይልቅ ልዩነት የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡
በመሆኑም የተፋሰሱ ሀገራት በውሃ አጠቃቀም ላይ ያሏቸውን ልዩነቶች በራሳቸው ተመካክረው ከመፍታት የተሻለ አማራጭ እንደሌላቸው በመጠቆም።
የዓባይን ወንዝ ምክንያታዊና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት የሚወስነው የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ብቻ ነው ያሉት አቶ ፈቅአህመድ፤ መንግስት የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ የውሃ አጠቃቀም መርህ እንዲወጣ በማድረግ በጋራ የመልማት ፍላጎት እንዳለው ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡
የአረብ ሊግ የህዳሴውን ግድብ በተመለከተ የሚያሳልፋቸው ውሳኔዎች ወንድማማች በሆኑት የኢትዮጵያና ግብጽ ህዝቦች መካከል ልዩነትና መጠራጠርን ስለሚፈጥር የግብጽ ህዝብ ሊቀበለው አይገባም ብለዋል፡፡
የአረብ ሊግ "የአረብ የውኃ ካውንስል" በሚባለው ምክር ቤታቸው አማካኝነት በርካታ የውሃ አካላትን በስሩ አካቶ የአረብ ውኃ በሚል እየሰየመ "ከእኛ ውጭ ማንም መጠቀም አይችልም" የሚል ተቀባይነት የሌለውና አካሄድ እየተከተለ ነው ተናግረዋል።
ቱርክ የሚገኙ የኤፍራጠስና ጤግሮስ ወንዞችን፤ ዮርዳኖስን፣ የናይል ገባሮችን ከዛም አልፎ የዋቢ ሸበሌና ገናሌ ዳዋ ወንዞችን የአረብ ውኃ እንደሆኑ የተሳሳተ አስተሳሰብ እያራመደ መሆኑን በመጥቀስ ይህ ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለውና ኢፍትሐዊ አካሄድ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባው ፕሮጀክት ፍትሐዊና ምክንያታዊ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ፈቅ አህመድ፤ የግድቡ ግንባታ ሂደት ሉዓላዊ መብትንና ዓለም አቀፍ የውኃ ህግን የተከተለ መሆኑን ለዓለም በአግባቡ ማሳወቅ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡
ለዚህም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውዥንብር ውስጥ እንዳይገባና ትክክለኛውን መረጃ እንዲያውቅ በማድረግ የተሳሳተ መረጃ የሚነዙ አካላትን አካሄድ ማክሸፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
******
(ኢ ፕ ድ)
የአረብ ሊግ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የያዘው አቋም በወንድማማች የኢትዮጵያና ግብጽ ህዝቦች መካከል ልዩነትና መጠራጠርን የሚፈጥር አካሄድ መሆኑን የውኃ ኃብት አስተዳደር አማካሪው አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽ ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ያለውን እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማስረዳት ከሌላ አቅጣጫ የሚሰነዘርባትን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ማክሸፍ ይኖርባታል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ያደረገ ጥናት በማከናወን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከጀመረች አስር ዓመታት አልፈዋል፡፡
ግድቡ ኢትዮጵያ ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን በመከተል በተፋሰሱ ሀገራት ላይ ጉልህ ጉዳት በማያደርስ መልኩ ከላይኛውና ታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር በጋራ የመልማት አላማ እንዳላት የሚያሳይ ፕሮጀክት ነው፡፡
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን በተፈጥሮ ሀብቷ መልማትና መጠቀም የማይፈልጉ አካላት፤ የግድቡን ግንባታ በሚመለከት ያልፈረመቻቸውን የአንድ ወገን የቅኝ ግዛት ስምምነቶች በማንሳት ይቃወማሉ።
የነዚህ አካላት ሚዛን የሌለውና እውነታ ላይ ያልተመሰረተ አካሄድ ኢትዮጵያ ዛሬም በድህነት እንድትማቅቅ ከመፈለግ የመነጨ መሆኑን ምሁራን ይገልጻሉ።
ከዚህም ባለፈ ከዓለም አቀፍ የወሰን ተሻጋሪ ወንዞች የውሃ አጠቃቀም ህግ ባፈነገጠ መልኩ በሶስተኛ ወገን አማካኝነት ተፅዕኖ ለመፍጠር ሲሞክሩ ይታያሉ፡፡
የውኃ ኃብት አስተዳደር አማካሪው አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በወሰን ተሻጋሪ ወንዞች መካከል የሚፈጠረውን ልዩነት በተመለከተ የሶስተኛ ወገን ጣልቃ ባይገባ ተመራጭ ነው፡፡
በወሰን ተሻጋሪ የውሃ አጠቃቀም ዙሪያ ያሉ ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሚፈልጉ ሶስተኛ ወገኖች ቢኖሩም አብዛኞቹ የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር የሚሞክሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የአረብ ሊግን ጨምሮ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ጣልቃ ለመግባት የሚሞክሩ አካላት የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ ዘላቂ ተጠቃሚነት ከማጎልበት ይልቅ ልዩነት የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል፡፡
በመሆኑም የተፋሰሱ ሀገራት በውሃ አጠቃቀም ላይ ያሏቸውን ልዩነቶች በራሳቸው ተመካክረው ከመፍታት የተሻለ አማራጭ እንደሌላቸው በመጠቆም።
የዓባይን ወንዝ ምክንያታዊና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት የሚወስነው የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ብቻ ነው ያሉት አቶ ፈቅአህመድ፤ መንግስት የተፋሰሱን ሀገራት የጋራ የውሃ አጠቃቀም መርህ እንዲወጣ በማድረግ በጋራ የመልማት ፍላጎት እንዳለው ማሳየቱን ገልጸዋል፡፡
የአረብ ሊግ የህዳሴውን ግድብ በተመለከተ የሚያሳልፋቸው ውሳኔዎች ወንድማማች በሆኑት የኢትዮጵያና ግብጽ ህዝቦች መካከል ልዩነትና መጠራጠርን ስለሚፈጥር የግብጽ ህዝብ ሊቀበለው አይገባም ብለዋል፡፡
የአረብ ሊግ "የአረብ የውኃ ካውንስል" በሚባለው ምክር ቤታቸው አማካኝነት በርካታ የውሃ አካላትን በስሩ አካቶ የአረብ ውኃ በሚል እየሰየመ "ከእኛ ውጭ ማንም መጠቀም አይችልም" የሚል ተቀባይነት የሌለውና አካሄድ እየተከተለ ነው ተናግረዋል።
ቱርክ የሚገኙ የኤፍራጠስና ጤግሮስ ወንዞችን፤ ዮርዳኖስን፣ የናይል ገባሮችን ከዛም አልፎ የዋቢ ሸበሌና ገናሌ ዳዋ ወንዞችን የአረብ ውኃ እንደሆኑ የተሳሳተ አስተሳሰብ እያራመደ መሆኑን በመጥቀስ ይህ ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለውና ኢፍትሐዊ አካሄድ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባው ፕሮጀክት ፍትሐዊና ምክንያታዊ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ፈቅ አህመድ፤ የግድቡ ግንባታ ሂደት ሉዓላዊ መብትንና ዓለም አቀፍ የውኃ ህግን የተከተለ መሆኑን ለዓለም በአግባቡ ማሳወቅ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡
ለዚህም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውዥንብር ውስጥ እንዳይገባና ትክክለኛውን መረጃ እንዲያውቅ በማድረግ የተሳሳተ መረጃ የሚነዙ አካላትን አካሄድ ማክሸፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
ከዋሺንግተን ዲሲ ከንቲባ ሙሪዬል ቦውዘር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተገኝተን የሁለትዮሽ ግንኙነት በማጠናከር ዙሪያ ውይይት አድርገናል።
ከከንቲባ ሙሪዬል ቦውዘር እና አመራሮቻቸው ጋር በአዲስ አበባ እና የዋሺንግተን ዲሲ የእህትማማችነት ስምምነት ወደ ተግባር እንዲለወጡ ለማስቻል ሰፋ ያለ ውይይት አካሂደናል። በተለይ በመንግስትና የግል አጋርነት በሚገነቡ የተቀናጁ የልማት ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከተማን መልሶ በማልማት፣ የተሻለ ገቢ አሰባሰብ፣ የውሃ ማከም፣ በትራንስፖርት፣ በዙሪያ ካሉ ከተሞች ጋር የልማት ስራዎች በማቀናጀት ላይ ልምዶችን በመቀመርና በመለዋወጥ በትብብር ለመስራት ተግባብተናል።
በመንግስት እና የግል አጋርነት በሚገነቡ፣ ከተማን መልሶ የማልማትና መልሶ በመጠቀም ስራዎችንም ጎብኝተል።
ከዋሺንግተን ዲሲ ከንቲባ ሙሪዬል ቦውዘር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተገኝተን የሁለትዮሽ ግንኙነት በማጠናከር ዙሪያ ውይይት አድርገናል።
ከከንቲባ ሙሪዬል ቦውዘር እና አመራሮቻቸው ጋር በአዲስ አበባ እና የዋሺንግተን ዲሲ የእህትማማችነት ስምምነት ወደ ተግባር እንዲለወጡ ለማስቻል ሰፋ ያለ ውይይት አካሂደናል። በተለይ በመንግስትና የግል አጋርነት በሚገነቡ የተቀናጁ የልማት ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ከተማን መልሶ በማልማት፣ የተሻለ ገቢ አሰባሰብ፣ የውሃ ማከም፣ በትራንስፖርት፣ በዙሪያ ካሉ ከተሞች ጋር የልማት ስራዎች በማቀናጀት ላይ ልምዶችን በመቀመርና በመለዋወጥ በትብብር ለመስራት ተግባብተናል።
በመንግስት እና የግል አጋርነት በሚገነቡ፣ ከተማን መልሶ የማልማትና መልሶ በመጠቀም ስራዎችንም ጎብኝተል።
“ሽፍታው ዋሻ”‼️
የባሌ ሰንሰለታማ ተራራዎች አካል ነው። አቀበት የበዛው ጠመዝማዛው መንገድ። በተራራው አናት ዋሻዎች በኩራት ተጀቡነው ይገኛሉ። ከነዚህ ዋሻዎች ባንደኛው ታዛውን ያበጀ ሰብስቤ የተሰኘ ሽፍታ ነበር አሉ። ዋሻውም ከዚህ ሽፍታ ስያሜውን እንዳገኘ ይነገራል።
ይህ የሞት ዋሻ ለተጓዥ ምቹ አይደለም። የእናቶች ዋይታ የአባቶች ቁጭት በተደጋጋሚ ይደመጥበታል። እህህ አስብሎ የሚያስቃስት ከባድ ሕመም የሚያስታቅፍ ክፉ ነው። የሰው ደም እንደ ውሀ መጋት ለምዷል። የእልፎችን ሕይወት ያለ ርህራሄ ቀጥፏል።
ወላጅን ቀባሪ አሳጥቷል። ልጅን ያለ አሳዳጊ አስቀርቷል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ መገኛው ነው። ከባሌ ዞን አዲስ አበባም ይሁን ሻሸመኔ ለሚሄድ መንገደኛ....
https://www.press.et/?p=100712
የባሌ ሰንሰለታማ ተራራዎች አካል ነው። አቀበት የበዛው ጠመዝማዛው መንገድ። በተራራው አናት ዋሻዎች በኩራት ተጀቡነው ይገኛሉ። ከነዚህ ዋሻዎች ባንደኛው ታዛውን ያበጀ ሰብስቤ የተሰኘ ሽፍታ ነበር አሉ። ዋሻውም ከዚህ ሽፍታ ስያሜውን እንዳገኘ ይነገራል።
ይህ የሞት ዋሻ ለተጓዥ ምቹ አይደለም። የእናቶች ዋይታ የአባቶች ቁጭት በተደጋጋሚ ይደመጥበታል። እህህ አስብሎ የሚያስቃስት ከባድ ሕመም የሚያስታቅፍ ክፉ ነው። የሰው ደም እንደ ውሀ መጋት ለምዷል። የእልፎችን ሕይወት ያለ ርህራሄ ቀጥፏል።
ወላጅን ቀባሪ አሳጥቷል። ልጅን ያለ አሳዳጊ አስቀርቷል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ መገኛው ነው። ከባሌ ዞን አዲስ አበባም ይሁን ሻሸመኔ ለሚሄድ መንገደኛ....
https://www.press.et/?p=100712
ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሄደ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችና ከተሞች ተካሂዷል።
ሰልፈኞቹ በኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ላይ የሚፈፀመውን ስም ማጥፋት በፅኑ በመቃወም ድጋፋቸውን ገልጸዋል።
ለመከላከያ ሠራዊቱ ያላቸውን ፍቅር እና አክብሮት የገለጹት ሰልፈኞቹ “ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያዊያን ዋስትና በመሆኑ ሁሌም ከሠራዊታችን ጎን እንቆማለን” ሲሉ ድጋፋቸውን አሳይተዋል።
ጀግናው የመከላከያ ሠራዊትን የሚያጥላሉና የስም ማጥፋት የሚፈፅሙ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችና ከተሞች ተካሂዷል።
ሰልፈኞቹ በኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ላይ የሚፈፀመውን ስም ማጥፋት በፅኑ በመቃወም ድጋፋቸውን ገልጸዋል።
ለመከላከያ ሠራዊቱ ያላቸውን ፍቅር እና አክብሮት የገለጹት ሰልፈኞቹ “ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያዊያን ዋስትና በመሆኑ ሁሌም ከሠራዊታችን ጎን እንቆማለን” ሲሉ ድጋፋቸውን አሳይተዋል።
ጀግናው የመከላከያ ሠራዊትን የሚያጥላሉና የስም ማጥፋት የሚፈፅሙ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።