የከተማ አስተዳደሩ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሰራተኞች ችግኝ ተከሉ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሰራተኞች በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ከአካባቢ ነዋሪዎች ጋር በመተባበር 10ሺህ ችግኞች ተከሉ።
የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ዳኛው ገብሩ እንደገለፁት ችግኞችን መትከል የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ደህንነቱ በተረጋገጠ ሀገር ላይ ማኖር ነው።
ተቋሙ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር አገልግሎት ከተጀመረ ጀምሮ ሲተክልና ሲንከባከብ ቆይቷል። አሁንም መትከል ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ስራንም ይሰራሉ ብለዋል
ባለስልጣኑ ከአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በተጨማሪ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይም ተሳትፎ ያደርጋል።
በዳግማዊት ግርማ
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሰራተኞች በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ከአካባቢ ነዋሪዎች ጋር በመተባበር 10ሺህ ችግኞች ተከሉ።
የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ዳኛው ገብሩ እንደገለፁት ችግኞችን መትከል የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ደህንነቱ በተረጋገጠ ሀገር ላይ ማኖር ነው።
ተቋሙ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር አገልግሎት ከተጀመረ ጀምሮ ሲተክልና ሲንከባከብ ቆይቷል። አሁንም መትከል ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ስራንም ይሰራሉ ብለዋል
ባለስልጣኑ ከአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በተጨማሪ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይም ተሳትፎ ያደርጋል።
በዳግማዊት ግርማ
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
ኮሚሽኑ በ2015 በጀት ዓመት ለ2 ሺህ 904 ባለሀብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በ2015 በጀት ዓመት ለ2 ሺህ 904 አዲስ ባላሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከዘርፉ በ2015 ዓ.ም በጀት አመት ለባለሀብቶች ከሰጠው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች 27 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 26 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር አግኝቷል። የዕቅዱን 97 ነጥብ 7 በመቶ ማሳካቱንም አስታውቋል፡፡
ከዚሁ ጎን ለጎን የኮሚሹኑን አገልግሎት በዘመናዊ ቴክኖሎጄ በማዘመንና ተገልጋዮች ሀብትና ጊዜያቸውን በመቆጠብ ሳይንገላቱ ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠት ተጀምሯል፡፡
የተገልጋዮችን ፍላጎትም መሰረት በማድረግ ለ 2 ሺ 904 አዲስ ፍቃድ፤ ለ464 የኢንቨስትመንት ለውጥ ማሻሻያ ፣ለ1 ሺ 854 ኢንቨስትመንት እድሳት እና ለ 232 ኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ፈቃድ እንዲሁም 98 ምትክ ፈቃድ መስጠት መቻሉን ከኮኒሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በኢንቨስትመንት ሥራ ለመሰማራት የማምረቻው ፣ የአገልግሎት ፣ የቱሪዝም ልማት ዘርፎች እንዲሁም የባለኮከብ ሆቴል ፣ ሪል እስቴት ዘርፍና የከተማ ግብርና ዘርፍ ለባለሃብቶች ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች ናቸው።
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በ2015 በጀት ዓመት ለ2 ሺህ 904 አዲስ ባላሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከዘርፉ በ2015 ዓ.ም በጀት አመት ለባለሀብቶች ከሰጠው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች 27 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 26 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር አግኝቷል። የዕቅዱን 97 ነጥብ 7 በመቶ ማሳካቱንም አስታውቋል፡፡
ከዚሁ ጎን ለጎን የኮሚሹኑን አገልግሎት በዘመናዊ ቴክኖሎጄ በማዘመንና ተገልጋዮች ሀብትና ጊዜያቸውን በመቆጠብ ሳይንገላቱ ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠት ተጀምሯል፡፡
የተገልጋዮችን ፍላጎትም መሰረት በማድረግ ለ 2 ሺ 904 አዲስ ፍቃድ፤ ለ464 የኢንቨስትመንት ለውጥ ማሻሻያ ፣ለ1 ሺ 854 ኢንቨስትመንት እድሳት እና ለ 232 ኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ፈቃድ እንዲሁም 98 ምትክ ፈቃድ መስጠት መቻሉን ከኮኒሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በኢንቨስትመንት ሥራ ለመሰማራት የማምረቻው ፣ የአገልግሎት ፣ የቱሪዝም ልማት ዘርፎች እንዲሁም የባለኮከብ ሆቴል ፣ ሪል እስቴት ዘርፍና የከተማ ግብርና ዘርፍ ለባለሃብቶች ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች ናቸው።
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
በከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ማህበረሰብ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተከናወነ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ማህበረሰብ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በጨፌ ትምህርት ቤት ተከናውኗል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ፤ በከተማ አስተዳደር ደረጃ ባለፉት አራት አመታት 42 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል እንደተቻ አስታውሰው በተያዘው ዓመት 17 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዷል ብለዋል።
የዓለማችን ፈተና የሆነውን የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል ችግኝ መትከል አስፈላጊ ነው። እንዲሁም ዛሬ ላይ የሚንተክለው ችግኝ የነገው ትውልድ በተሻለና ምቹ በሆነ ምድር ላይ እንድኖር ያደርጋል ነው ያሉት።
አረንጓዴ አሻራ ከውበት ይልቅ ለትውልድ ትልቅ መሰረት የምንጥልበት እንደ መሆኑ መጠን መምህራን በተማሪዎች ላይ ከመለያየት ይልቅ ስለ አንድነት በማስተማር ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲያፈሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በበኩላቸው የዛሬው ቀን ሰኔ 30 መሆኑን አስታውሰው ቀኑ ሲታሰብ በአዕምሮአችን የሚመጣው ውጤት የምናይበትና ወደቀጣዩ ምዕራፍ የምንሻገርበት ነው ብለዋል።
ዛሬ ላይ ሆነን ነገን እንትከል ስንል ለነገው ሀገር ተረካቢው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ነው ሲለዚህም ነገን የሚትረከቡን እናንተ በመሆናችሁ ጠንክራችሁ ስሩ በማለት ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዛሬው እለት በተከናወነው በዚህ የማስጀመሪያ መርሀ ግብር ከ15 ሺ በላይ ችግኞች እንደሚተከሉ ተጠቁሟል።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ማህበረሰብ የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በጨፌ ትምህርት ቤት ተከናውኗል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ፤ በከተማ አስተዳደር ደረጃ ባለፉት አራት አመታት 42 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል እንደተቻ አስታውሰው በተያዘው ዓመት 17 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዷል ብለዋል።
የዓለማችን ፈተና የሆነውን የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል ችግኝ መትከል አስፈላጊ ነው። እንዲሁም ዛሬ ላይ የሚንተክለው ችግኝ የነገው ትውልድ በተሻለና ምቹ በሆነ ምድር ላይ እንድኖር ያደርጋል ነው ያሉት።
አረንጓዴ አሻራ ከውበት ይልቅ ለትውልድ ትልቅ መሰረት የምንጥልበት እንደ መሆኑ መጠን መምህራን በተማሪዎች ላይ ከመለያየት ይልቅ ስለ አንድነት በማስተማር ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲያፈሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በበኩላቸው የዛሬው ቀን ሰኔ 30 መሆኑን አስታውሰው ቀኑ ሲታሰብ በአዕምሮአችን የሚመጣው ውጤት የምናይበትና ወደቀጣዩ ምዕራፍ የምንሻገርበት ነው ብለዋል።
ዛሬ ላይ ሆነን ነገን እንትከል ስንል ለነገው ሀገር ተረካቢው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ነው ሲለዚህም ነገን የሚትረከቡን እናንተ በመሆናችሁ ጠንክራችሁ ስሩ በማለት ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዛሬው እለት በተከናወነው በዚህ የማስጀመሪያ መርሀ ግብር ከ15 ሺ በላይ ችግኞች እንደሚተከሉ ተጠቁሟል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።
ሁለቱ ተቋማት በሚዲያና ኮምንኬሽን ዘርፍ በጋራ ለመስራት ስምምነቱን የፈጸሙ ሲሆን፤ ኢፕድ በዚህ መስክ ያለውን የካበተ ልምድ ለተቋሙ ለማጋራት እንደሚሰራ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
ይህንኑ ስምምነት በኢፕድ በኩል የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ሄለን እስክንድር የፈረሙ ሲሆን፤ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ደግሞ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የትራንስፎርሜሽንና ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም ከተማ ፈርመዋል።
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
በሞገስ ተስፋ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።
ሁለቱ ተቋማት በሚዲያና ኮምንኬሽን ዘርፍ በጋራ ለመስራት ስምምነቱን የፈጸሙ ሲሆን፤ ኢፕድ በዚህ መስክ ያለውን የካበተ ልምድ ለተቋሙ ለማጋራት እንደሚሰራ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
ይህንኑ ስምምነት በኢፕድ በኩል የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ሄለን እስክንድር የፈረሙ ሲሆን፤ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ደግሞ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የትራንስፎርሜሽንና ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም ከተማ ፈርመዋል።
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
በሞገስ ተስፋ
ከነገ ጀምሮ ሁሉም ሚንስትሮችና ሚንስትር ዴኤታዎች ለስራ ግምገማ ወደክልሎች እንደሚሄዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስታወቁ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ከነገ ጀምሮ ሁሉም ሚንስትሮችና ሚንስትር ዴኤታዎች የስራ ግምገማ ለማድረግ ወደክልሎች እንደሚጓዙ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ እንደተናገሩት፤ ከነገ ሐምሌ አንድ ቀን 2015 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ሁሉም ሚንስትሮችና ሚንስትር ዴኤታዎች በየክልሉ የስራ ግምገማ ያደርጋሉ።
ሚኒስትሮችና ሚኒስትር ድኤታዎች ለስራ ግምገማው የሚሄዱባቸው ክልሎች ተመድቦ ማለቁን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚሁ ሚንስትሮች በሄዱባቸው ቦታዎች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉና ምን ክፍተት እንዳለ ይገመግማሉ ብለዋል።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገለጻም፤ ሚኒስትሮቹ ከመስክ ምልክታ ሲመለሱ ግምገማ ይካሄዳል።
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓም
በሀይማኖት ከበደ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ከነገ ጀምሮ ሁሉም ሚንስትሮችና ሚንስትር ዴኤታዎች የስራ ግምገማ ለማድረግ ወደክልሎች እንደሚጓዙ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ እንደተናገሩት፤ ከነገ ሐምሌ አንድ ቀን 2015 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ሁሉም ሚንስትሮችና ሚንስትር ዴኤታዎች በየክልሉ የስራ ግምገማ ያደርጋሉ።
ሚኒስትሮችና ሚኒስትር ድኤታዎች ለስራ ግምገማው የሚሄዱባቸው ክልሎች ተመድቦ ማለቁን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚሁ ሚንስትሮች በሄዱባቸው ቦታዎች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በምን ደረጃ ላይ እንዳሉና ምን ክፍተት እንዳለ ይገመግማሉ ብለዋል።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገለጻም፤ ሚኒስትሮቹ ከመስክ ምልክታ ሲመለሱ ግምገማ ይካሄዳል።
ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓም
በሀይማኖት ከበደ