የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
ዛሬ ማለዳ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙ የከተማችን ወጣቶች ጋር በመሆን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የደም ልገሳ አድርገናል። በአዕምሮ እና በአካል የበለፀገ ትውልድ ለማፍራት የጀመርናቸው ስራዎቻችን ፍሬ ማፍራት ጀምረዋል።
የከተማችን ወጣቶች “በጎነት አያጎድልም” ብለው የበጋ የበጎ ፍቃድ ስራዎቻችን ላይ ከፊት ሆነው በመምራት እና ከበጎ አስተሳሰብ እንዲሁም ከሁሉም መልካም ተግባሮች ጋር በመተባበር ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
በዚህ ክረምትም ከበጋው ወቅት በተሻለ መልኩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማችን እንዲስፋፋ አቅመ ደካሞችን እንዲደግፉ፣ የአረጋዊያንን ቤት እንዲያድሱ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራችን ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
ዛሬ ማለዳ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙ የከተማችን ወጣቶች ጋር በመሆን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የደም ልገሳ አድርገናል። በአዕምሮ እና በአካል የበለፀገ ትውልድ ለማፍራት የጀመርናቸው ስራዎቻችን ፍሬ ማፍራት ጀምረዋል።
የከተማችን ወጣቶች “በጎነት አያጎድልም” ብለው የበጋ የበጎ ፍቃድ ስራዎቻችን ላይ ከፊት ሆነው በመምራት እና ከበጎ አስተሳሰብ እንዲሁም ከሁሉም መልካም ተግባሮች ጋር በመተባበር ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
በዚህ ክረምትም ከበጋው ወቅት በተሻለ መልኩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማችን እንዲስፋፋ አቅመ ደካሞችን እንዲደግፉ፣ የአረጋዊያንን ቤት እንዲያድሱ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስራችን ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ ከተለያዩ አለም ሀገሮች ከተውጣጡ የሀረሪ ዳያስፖራዎች ጋር ተወያዩ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ ከተለያዩ አለም ሀገሮች ከተውጣጡ የሀረሪ ዳያስፖራዎች ጋር በካናዳ ቶሮንቶ ተወያይቶዋል።
በውይይቱ ላይም ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ኦርዲን በድሪ እንደተናገሩት ውይይቱ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራንበት እና በዋና ዋና ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት የተፈጠረበት ነው።
በተለይም ችግሮችን በዲያስፖራው ጋር በቅንጅት በመመፍታት በቀጣይም ዳያስፖራው በክልላዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
ለ25ኛው ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው አለም አቀፍ የሀረሪ ባህል እና ስፖርት ፌስቲቫል ስኬታማነት ድጋፍ ላደረጉላቸው አካላት ልባዊ ምስጋና ያቀረቡት ርዕሰ መስተዳደሩ በአሉን አስተባባሪ የሆኑት የካናዳ ሀረሪ ኮሙኒቲ እና የሀረሪ ሄሪቴጅ ሴንተር ላደረጉላቸው ደማቅ አቀባበልና መስተንግዶ የላቀ ምስጋና አቀርበዋል።
በውይይት መድረኩ ላይም የሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ፣ የክልሉ ምክር ቤት ም/አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድ ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማእከል ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ካሊድ አልዋ፣ በካናዳ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሐመድ እንድሪስን ጨምሮ በካናዳ እና በአካባቢው የሚኖሩ የሀረሪ ኮሚዩኒቲ ተዉካዮች ተገኝተዋል።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ ከተለያዩ አለም ሀገሮች ከተውጣጡ የሀረሪ ዳያስፖራዎች ጋር በካናዳ ቶሮንቶ ተወያይቶዋል።
በውይይቱ ላይም ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ኦርዲን በድሪ እንደተናገሩት ውይይቱ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራንበት እና በዋና ዋና ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት የተፈጠረበት ነው።
በተለይም ችግሮችን በዲያስፖራው ጋር በቅንጅት በመመፍታት በቀጣይም ዳያስፖራው በክልላዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
ለ25ኛው ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው አለም አቀፍ የሀረሪ ባህል እና ስፖርት ፌስቲቫል ስኬታማነት ድጋፍ ላደረጉላቸው አካላት ልባዊ ምስጋና ያቀረቡት ርዕሰ መስተዳደሩ በአሉን አስተባባሪ የሆኑት የካናዳ ሀረሪ ኮሙኒቲ እና የሀረሪ ሄሪቴጅ ሴንተር ላደረጉላቸው ደማቅ አቀባበልና መስተንግዶ የላቀ ምስጋና አቀርበዋል።
በውይይት መድረኩ ላይም የሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ፣ የክልሉ ምክር ቤት ም/አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድ ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማእከል ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ካሊድ አልዋ፣ በካናዳ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ፣የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሐመድ እንድሪስን ጨምሮ በካናዳ እና በአካባቢው የሚኖሩ የሀረሪ ኮሚዩኒቲ ተዉካዮች ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን የ2016 ዓ.ም በጀት 140 ነጥብ 29 ቢሊየን ብር አፀደቀ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን የ2016 ዓ.ም በጀት 140 ነጥብ 29 ቢሊየን ብር አፅድቋል።
የተበጀተው በጀት የከተማዋን የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄ ለመፍታት የሚያስችል መሆኑን ተገልጿል።
በታደሰ ብናልፈው
ሐምሌ 2ቀን 2015 ዓ.ም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን የ2016 ዓ.ም በጀት 140 ነጥብ 29 ቢሊየን ብር አፅድቋል።
የተበጀተው በጀት የከተማዋን የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄ ለመፍታት የሚያስችል መሆኑን ተገልጿል።
በታደሰ ብናልፈው
ሐምሌ 2ቀን 2015 ዓ.ም