አቶ ደመቀ መኮንን ከደቡብ አፍሪካ ፣ ከሞሮኮ እንዲሁም ከቻድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከደቡብ አፍሪካ የአለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር እና ከሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናስር ቡሪታ ጋር በኬንያ ናይሮቢ ተወያይተዋል።
አቶ ደመቀ ሚኒስትሮች ስለ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተስፋ ሰጪ አፈፃፀም እና ኢትዮጵያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽኖችን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እየሰራች መሆኑን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ፓንዶር ደቡብ አፍሪካ የሰላም ማስፈጸሚያ እቅዶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ተናግረዋል።
የሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡሪታ ሞሮኮ ለኢትዮጵያ ልዩ ቦታ እንደምትሰጥ እና እንደ ግብርና እና ትምህርት ባሉ ዘርፎች በትብብር መስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል ።
በተጨማሪም አቶ ደመቀ መኮንን ከቻድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህማት ሳሌህ አናዲፍ ጋር ተገናኝተው በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ሁለቱ ሚኒስትሮች ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል።
43ኛው የአፍሪካ ኀብር የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በኬንያ ናይሮቢ እየካሄደ ይገኛል ።
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከደቡብ አፍሪካ የአለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር እና ከሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናስር ቡሪታ ጋር በኬንያ ናይሮቢ ተወያይተዋል።
አቶ ደመቀ ሚኒስትሮች ስለ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተስፋ ሰጪ አፈፃፀም እና ኢትዮጵያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽኖችን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እየሰራች መሆኑን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ፓንዶር ደቡብ አፍሪካ የሰላም ማስፈጸሚያ እቅዶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ተናግረዋል።
የሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡሪታ ሞሮኮ ለኢትዮጵያ ልዩ ቦታ እንደምትሰጥ እና እንደ ግብርና እና ትምህርት ባሉ ዘርፎች በትብብር መስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል ።
በተጨማሪም አቶ ደመቀ መኮንን ከቻድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህማት ሳሌህ አናዲፍ ጋር ተገናኝተው በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ሁለቱ ሚኒስትሮች ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማምተዋል።
43ኛው የአፍሪካ ኀብር የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በኬንያ ናይሮቢ እየካሄደ ይገኛል ።
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
#ኢፕድ_ድንቃድንቅ‼️
ትልቁ የኩላሊት ጠጠር ከስሪላንካዊው በህክምና ተወግዷል
ኩንጌህ ይባላል፤ ሲሪላንካዊ የ62 ዓመት የዕድሜ ባላፀጋ ነው። በጉብዝናው ወራትም አገሩን በውትድርና ያገለገለ ጡረተኛ የቀድሞ ወታደር ነው።
ይህ ሲሪላንካዊ ጤንነቱ እንደቀድሞው አልሆን ቢለው ጊዜ ከእለታት በአንዱ ቀን ወደ ወታደሮች ሆስፒታል ያመራል።
አስፈላጊውን ምርመራ ካካሄደ በኋላም ሀኪሞቹ የኩላሊት ጠጠር እንዳለበት ይነግሩታል፤ በፍጥነትም በህክምና መወገድ አለበት ሲሉ አከሉለት።
ሲሪላንካዊው በሀኪሞቹ ምክረ ሃሳብ ተስማምቶም ለቀዶ ጥገና ዝግጁ ሆነ።
የሆስፒታሉ ሀኪሞችም በዶክተር ኩጋዳስ ሱታርሻን እየተመሩ እአአ ሰኔ 1 ቀን 2023 ከሲሪላንካዊው ኩላሊት እስካሁን ከሰው ልጆች ከተወገዱት ጠጠሮች ሁሉ በርዝመቱም፣ በስፋቱም ሆነ በክብደቱ ትልቅ የሆነውን የኩላሊት ጠጠር ማውጣት ቻሉ።
ይህ የኪላሊት ጠጠር ርዝመቱ 13.37 ሴ.ሜ (5.26 ኢንች) እና 10.55 ሴ.ሜ (4.15 ኢንች) ስፋት እና 800 ግራም (1.76 ፓውንድ) ክብደት ያለው መሆኑ በሀኪሞች ልኬት ተረጋገጠ።
እስካሁን ከተመዘገቡት የኩላሊት ጠጠሮች መካከልም ትልቁ የኩላሊት ጠጠር ተብሎ በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ሊመዘገብ ቻለ።
ከዚህ በፊት እአአ በ2008 ይህ የዓለም ሪከርድ ተይዞ የነበረው በፓኪስታናዊው ዋዚር መሀመድ ሲሆን በወቅቱም 620 ግራም የሚመዝን የኩላሊት ጠጠር ነበር የተወገደለት፡፡
ከኩንጌህ የተወገደው የኩላሊት ጠጠር ከቀኝ ኩላሊቱ ሲሆን ቀዶ ጥገናውን ያደረጉት ዶክተር የኩጋህ ኩላሊት አሁንም በመደበኛነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የኩንጌህ የውስጥ የሠውነት ክፍሎቹ በጥሩ ጤንነት ላይ የሚገኙ መሆኑንም ሀኪሙ ተናግረዋል።
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
በሀይማኖት ከበደ
ትልቁ የኩላሊት ጠጠር ከስሪላንካዊው በህክምና ተወግዷል
ኩንጌህ ይባላል፤ ሲሪላንካዊ የ62 ዓመት የዕድሜ ባላፀጋ ነው። በጉብዝናው ወራትም አገሩን በውትድርና ያገለገለ ጡረተኛ የቀድሞ ወታደር ነው።
ይህ ሲሪላንካዊ ጤንነቱ እንደቀድሞው አልሆን ቢለው ጊዜ ከእለታት በአንዱ ቀን ወደ ወታደሮች ሆስፒታል ያመራል።
አስፈላጊውን ምርመራ ካካሄደ በኋላም ሀኪሞቹ የኩላሊት ጠጠር እንዳለበት ይነግሩታል፤ በፍጥነትም በህክምና መወገድ አለበት ሲሉ አከሉለት።
ሲሪላንካዊው በሀኪሞቹ ምክረ ሃሳብ ተስማምቶም ለቀዶ ጥገና ዝግጁ ሆነ።
የሆስፒታሉ ሀኪሞችም በዶክተር ኩጋዳስ ሱታርሻን እየተመሩ እአአ ሰኔ 1 ቀን 2023 ከሲሪላንካዊው ኩላሊት እስካሁን ከሰው ልጆች ከተወገዱት ጠጠሮች ሁሉ በርዝመቱም፣ በስፋቱም ሆነ በክብደቱ ትልቅ የሆነውን የኩላሊት ጠጠር ማውጣት ቻሉ።
ይህ የኪላሊት ጠጠር ርዝመቱ 13.37 ሴ.ሜ (5.26 ኢንች) እና 10.55 ሴ.ሜ (4.15 ኢንች) ስፋት እና 800 ግራም (1.76 ፓውንድ) ክብደት ያለው መሆኑ በሀኪሞች ልኬት ተረጋገጠ።
እስካሁን ከተመዘገቡት የኩላሊት ጠጠሮች መካከልም ትልቁ የኩላሊት ጠጠር ተብሎ በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ሊመዘገብ ቻለ።
ከዚህ በፊት እአአ በ2008 ይህ የዓለም ሪከርድ ተይዞ የነበረው በፓኪስታናዊው ዋዚር መሀመድ ሲሆን በወቅቱም 620 ግራም የሚመዝን የኩላሊት ጠጠር ነበር የተወገደለት፡፡
ከኩንጌህ የተወገደው የኩላሊት ጠጠር ከቀኝ ኩላሊቱ ሲሆን ቀዶ ጥገናውን ያደረጉት ዶክተር የኩጋህ ኩላሊት አሁንም በመደበኛነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የኩንጌህ የውስጥ የሠውነት ክፍሎቹ በጥሩ ጤንነት ላይ የሚገኙ መሆኑንም ሀኪሙ ተናግረዋል።
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
በሀይማኖት ከበደ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የሩሲያ ፌደሬሽን አምባሳደር ጋር ተወያዩ
**********************************************
(ኢ ፕ ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የሩሲያ ፌደሬሽን አምባሳደር ከሆኑት ኤፍጌኒ ተረክህን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸው ወቅት የሩሲያ ከተሞች ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው የትብብር መንገዶች ዙሪያ መምክራቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
**********************************************
(ኢ ፕ ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የሩሲያ ፌደሬሽን አምባሳደር ከሆኑት ኤፍጌኒ ተረክህን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸው ወቅት የሩሲያ ከተሞች ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው የትብብር መንገዶች ዙሪያ መምክራቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያና ጀርመን የ25 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ
*****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ጀርመን ለምርትና ግብይት ሰንሰለት ማጠናከሪያ ፕሮጀክት የሚውል የ25 ሚሊዮን ዩሮ (የ1.5 ቢሊዮን ብር) የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በገንዘብ ሚኒስቴር በተካሄደ ስነስርአት ተፈራረሙ፡፡
የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቱን በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው ሲፈርሙ በጀርመን መንግስት በኩል የጀርመን የምስራቅ አፍሪካና የአፍሪካ ህብረት ቡድን ዳይሬክተር ሚስተር ክሪስቶፍ ቲስከንስ ፈርመዋል፡፡
የፋይናንስ ድጋፉ በአማራ ክልል በምስራቅ ጎጃምና በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በዝናብ ተጠቅመው ክፍተኛ ምርት ለሚያመርቱ አካባቢዎች ከአየር ንብረቱና ከስነምዳሩ ጋር የተጣጣመ ዘላቂ የምርት እድገትና የግብይት ሰንሰለት ለማጠናከር የሚውል ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በተለየ ትኩረት የሚያደርገው በአዝርእትና ጥራጥሬ ምርቶች ላይ ሲሆን አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር፣ የግብርና መሳሪያዎች፣ የመረጃና የዘመናዊ የግብርና አመራራ ስልት ድጋፍ እንዲያገኙ በማድረግ እንዲሁም በምርት ግብይቱ ሰንሰለት ተዋናይ የሆኑ ባለድርሻዎችን አቅም በማጎልበት ላይ ነው፡፡
በምርትና ግብይቱ አስተዋጽኦ ያላቸውን የግብርና ምርምር ተቋማት፣ የህብረት ስራ ማህበራት፣ የግብርና ልማት ተቋማት፣ ዩኒቨርስቲዎች፣ የምርጥ ዘር ተቋማትና የፕሮጀክት አስፈጻሚ አካትን አቅም ማጎልበትም የፕሮጀክቱ አላማ መሆኑ ታውቋል፡፡
በፊርማ ስነስርአቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ትብብር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው የኢትዮጵያና የጀርመን የሁለትዮሽ ትብብር ከአንድ ምዕተ አመት በላይ እድሜ ያስቆጠረ ጠንካራ ወዳጅነት መሆኑን አመለክተው የጀርመን መንግስት ኢትዮጵያ የነደፈችውን ሁለተኛውን የአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሸሻያ አጀንዳና የ10 አመቱን መሪ የልማት ዕቅድ እንደሚደግፍ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ጀርመን ለምርትና ግብይት ሰንሰለት ማጠናከሪያ ፕሮጀክት የሚውል የ25 ሚሊዮን ዩሮ (የ1.5 ቢሊዮን ብር) የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በገንዘብ ሚኒስቴር በተካሄደ ስነስርአት ተፈራረሙ፡፡
የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቱን በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው ሲፈርሙ በጀርመን መንግስት በኩል የጀርመን የምስራቅ አፍሪካና የአፍሪካ ህብረት ቡድን ዳይሬክተር ሚስተር ክሪስቶፍ ቲስከንስ ፈርመዋል፡፡
የፋይናንስ ድጋፉ በአማራ ክልል በምስራቅ ጎጃምና በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በዝናብ ተጠቅመው ክፍተኛ ምርት ለሚያመርቱ አካባቢዎች ከአየር ንብረቱና ከስነምዳሩ ጋር የተጣጣመ ዘላቂ የምርት እድገትና የግብይት ሰንሰለት ለማጠናከር የሚውል ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በተለየ ትኩረት የሚያደርገው በአዝርእትና ጥራጥሬ ምርቶች ላይ ሲሆን አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር፣ የግብርና መሳሪያዎች፣ የመረጃና የዘመናዊ የግብርና አመራራ ስልት ድጋፍ እንዲያገኙ በማድረግ እንዲሁም በምርት ግብይቱ ሰንሰለት ተዋናይ የሆኑ ባለድርሻዎችን አቅም በማጎልበት ላይ ነው፡፡
በምርትና ግብይቱ አስተዋጽኦ ያላቸውን የግብርና ምርምር ተቋማት፣ የህብረት ስራ ማህበራት፣ የግብርና ልማት ተቋማት፣ ዩኒቨርስቲዎች፣ የምርጥ ዘር ተቋማትና የፕሮጀክት አስፈጻሚ አካትን አቅም ማጎልበትም የፕሮጀክቱ አላማ መሆኑ ታውቋል፡፡
በፊርማ ስነስርአቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ትብብር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው የኢትዮጵያና የጀርመን የሁለትዮሽ ትብብር ከአንድ ምዕተ አመት በላይ እድሜ ያስቆጠረ ጠንካራ ወዳጅነት መሆኑን አመለክተው የጀርመን መንግስት ኢትዮጵያ የነደፈችውን ሁለተኛውን የአገር በቀል ኢኮኖሚ ማሸሻያ አጀንዳና የ10 አመቱን መሪ የልማት ዕቅድ እንደሚደግፍ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ክቡር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ሽልማት ተበረከተላቸው
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በ13ኛው ዓመታዊ የአፍሪካ አሸናፊዎች ሽልማት የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ እንግሊዝ ለንደን በተካሄደው የአፍሪካውያን የስኬታማዎች ሽልማት ትናንት ምሽት ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም በተካሄደ ስነ ስርዓት ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል ።
የአሸናፊነት ሽልማቱ ኢጋድ በአካባቢው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ላደረገው አስተዋፅኦ መሆኑን ተገልፆል ፤ ይህ ሽልማት ለስኬታማ ተግባር የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ሸላሚ ድርጀቱ አስታውቋል ። ከብዙ የኢጋድ ስኬቶች ውስጥ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲሳካ የተደረገው ጥረት የሚጠቀስ መሆኑ ተመላክቷል ።
የአፍሪካ አሸናፊዎች ሽልማቶች ለአህጉሪቱ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ለሚያደርጉ በአፍሪካ ውስጥ ታዋቂ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና በመስጠት እና በማክበር የአፍሪካን የላቀ ደረጃ የሚያከብር ዓመታዊ የሽልማት ሥነሥርዓት ነው።
ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በ13ኛው ዓመታዊ የአፍሪካ አሸናፊዎች ሽልማት የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ እንግሊዝ ለንደን በተካሄደው የአፍሪካውያን የስኬታማዎች ሽልማት ትናንት ምሽት ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም በተካሄደ ስነ ስርዓት ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል ።
የአሸናፊነት ሽልማቱ ኢጋድ በአካባቢው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ላደረገው አስተዋፅኦ መሆኑን ተገልፆል ፤ ይህ ሽልማት ለስኬታማ ተግባር የተሰጠ ዕውቅና መሆኑን ሸላሚ ድርጀቱ አስታውቋል ። ከብዙ የኢጋድ ስኬቶች ውስጥ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲሳካ የተደረገው ጥረት የሚጠቀስ መሆኑ ተመላክቷል ።
የአፍሪካ አሸናፊዎች ሽልማቶች ለአህጉሪቱ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ለሚያደርጉ በአፍሪካ ውስጥ ታዋቂ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን እውቅና በመስጠት እና በማክበር የአፍሪካን የላቀ ደረጃ የሚያከብር ዓመታዊ የሽልማት ሥነሥርዓት ነው።
ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም