Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
"እድል እና ትግል ሲገናኙ መከናወን ይሆናል፤ ኢትዮጵያዊነት የታደልነው ነው፤ ይህ መታሰቢያ ደግሞ ታግለን የሠራነው ነው"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****
(ኢ.ፕ.ድ)

የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የዓድዋ ድል መታሰቢያን በይፋ መርቀው ከፍተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በመርሃግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "እድል እና ትግል ሲገናኙ መከናወን ይሆናል። ኢትዮጵያዊነት የታደልነው ነው፤ ይህ መታሰቢያ ደግሞ ታግለን የሠራነው ነው ብለዋል።

መታሰቢያው ኢትዮጵያዊ በመሆናችን ታድለን የመስራት ጥረት ታክሎበት የተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ128 ዓመት በኋላ ተከውኖ ለልጆች ማለፍ በሚችልበት መልኩ ከነግርማ ሞገሱ ኢትዮጵያን መስሎ ኢትዮጵያን አክሎ የታየበት መሆኑንም ገልጸዋል።

የዓድዋን ድል ማርከስ ማለት የአባቶቻችንን አጥንትና ደም ማርከስ መሆኑንም ገልጸዋል።

አባቶቻችን ዋጋ የከፈሉበት ነጻነትና ክብር እሴት መሆኑን ገልጸው ነጻነትን ለማግኘት የሄዱበት መንገድ እሳት መሆኑን ገልጸዋል።

ከአባቶቻችን ልንወርስ የሚገባው ነጻነቱን ክብሩንና አንድነቱን እንጂ እሳቱን መሆን አይጠበቅብንም ብለዋል።

በምረቃ መርሃግብ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የሁለቱም ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ተገኝተዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሮች የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች የሀገር መከላከያና የፌድራል ፓሊስ አመራሮች የሃይማኖት አባቶች አባ ገዳዎች ታዋቂ ግለሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የዓድዋ ድል መታሰቢያ ለአሁኑ ትውልድ ኩራትና መማሪያ እንዲሆን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ አበባ አተማ አስተዳደር መገንባቱ ተገልጿል።

በማርቆስ በላይ
የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ.ም
"የዓድዋ ድል መታሰቢያ ታላቁ የዓድዋ ገድል የደመቀበት ተበታትነው የነበሩ የታሪክ ማስረጃዎች የተሰበሰቡበትና የተረሱት የታወሱበት ነው"
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ታላቁ የዓድዋ ገድል የደመቀበት ተበታትነው የነበሩ የታሪክ ማስረጃዎች የተሰበሰቡበትና የተረሱት የታወሱበት ነው ብለዋል።

በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያውያን ልዩነትን ወደ ጎን በመተው በአንድነት ወደ ዓውደ ውጊያው ተምመዋል ያሉት ከንቲባዋ በዚህም የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የነፃነት ቀንዲል የሆነውን የዓድዋ ድልን አስመዝግበዋል ብለዋል።

መታሰቢያው የታሪክና ትርክት ክፍተትን ከመሙላት ባለፈም ስብራትን የሚጠግን እንደሚሆን እናምናለን ብለዋል።

የዓደዋ ድል መታሰቢያ ጀግኖችን በሚገባቸው ከፍታ ያስቀመጠ መሆኑን ጠቅሰው ትውልዱ በአንድነት ሆኖ ማሸነፍንና የሀገር ፍቅርን የሚማርበት መሆኑንም ገልፀዋል።

የዓድዋ ድል መታሰቢያ መላ ኢትዮጵያውያን በአንድ ቋንቋ እንዲግባቡ የማድረግ ኃይል ያለው መሆኑን በመግለጽ ትናንትን ከዛሬ ዛሬን ከነገ የሚያስተሳስር ድልድያችን በመሆኑ የመጪው ትውልድ ስጦታችን ነው ብለዋል።

በማርቆስ በላይ
የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ.ም
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️

እንደ "አድዋው ዘማቾች" ከሰሜንም ፣ ከደቡብም ፣ ከምስራቅና ከምዕራቡም ጥሪያችንን አክብራችሁ በዚህ ታሪካዊ ፕሮግራም ላይ ለታደማችሁ እንዲሁም ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላደረጋችሁ አካላት ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ::

የረዳን ፈጣሪ ይመስገን

ኢትዮጵያ በልጆቿ ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር ።