በአማራ ክልል በሩዝ ሰብል ከለማው መሬት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተገኘ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራ ክልል በመኸር ወቅት በሩዝ ሰብል ከለማው መሬት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ አግደው ሞላ እንደገለጹት፤ ምርቱ የተገኘው በ2015/2016 የምርት ዘመን በሩዝ ሰብል ከለማ ከ82 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ነው።
ምርቱ የተሰበሰበው ለሩዝ ሰብል ልማት ተስማሚ በሆኑት ደቡብ፣ ማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ጃዊ ወረዳ በሩዝ ሰብል ከለማ መሬት መሆኑን ተናግረዋል።
የተሰበሰበው ምርት በቀዳሚው ዓመት ከተገኘው ጋር ሲነጻጸር ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ፤ በለማው መሬት ደግሞ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል።
በክልሉ የተሻሻሉ የሩዝ ምርጥ ዘሮችን ተደራሽ በማድረግ ልማቱ እንዲስፋፋ መደረጉ ከውጭ የሚገባን የሩዝ ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት የተያዘውን ግብ ለማሳካት እያገዘ መሆኑንም አቶ አግደው አስታውቀዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ ልማቱ አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን እንዲችል ከማድረግ ባለፈ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ በዘላቂነት እንዲያረጋገጥ የጎላ ሚና እንዳለው ነው ያስረዱት።
በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አርሶ አደር መልኬ መለሰ እንዳሉት፤ ባለፈው የመኸር ወቅት ''ሻጋ'' የተባለውን የሩዝ ምርጥ ዘር ተጠቅመው ካለሙት አንድ ሄክታር መሬት 60 ኩንታል ምርት አግኝተዋል።
የተሻሻሉና ምርታማ የሆኑ የሩዝ ዝርያዎች ተደራሽ መደረጋቸው የእሳቸውንና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርታማነት እያደገ እንዲመጣ ማገዙን ተናግረዋል።
በዚህም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ነው የገለጹት።
ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ተዋቸው ፈጠነ በበኩላቸው፤ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ ዕጥረት ቢያጋጥምም በሩዝ ሰብል ካለሙት አንድ ሄክታር ተኩል መሬት 65 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
‘‘ምርታማነትን ለማሳደግ በምናደርገው ጥረት ዋነኛ ችግራችን የማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦትና ጥራቱን የጠበቀ የሩዝ መፈልፈያ ማሽን አለመኖር ነው’’ ያሉት ደግሞ ሌላኛው የወረዳው አርሶ አደር ዘላለም አስፋው ናቸው።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ አርሶ አደሩ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት ገጥሟቸው የነበረ ቢሆንም በአንድ ሄክታር መሬት ካለሙት የሩዝ ሰብል ከ50 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ተናገረዋል።
በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በሩዝ ሰብል ከለማው 61 ሺህ ሄክታር መሬት 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራ ክልል በመኸር ወቅት በሩዝ ሰብል ከለማው መሬት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ አግደው ሞላ እንደገለጹት፤ ምርቱ የተገኘው በ2015/2016 የምርት ዘመን በሩዝ ሰብል ከለማ ከ82 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ነው።
ምርቱ የተሰበሰበው ለሩዝ ሰብል ልማት ተስማሚ በሆኑት ደቡብ፣ ማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ጃዊ ወረዳ በሩዝ ሰብል ከለማ መሬት መሆኑን ተናግረዋል።
የተሰበሰበው ምርት በቀዳሚው ዓመት ከተገኘው ጋር ሲነጻጸር ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ፤ በለማው መሬት ደግሞ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል።
በክልሉ የተሻሻሉ የሩዝ ምርጥ ዘሮችን ተደራሽ በማድረግ ልማቱ እንዲስፋፋ መደረጉ ከውጭ የሚገባን የሩዝ ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት የተያዘውን ግብ ለማሳካት እያገዘ መሆኑንም አቶ አግደው አስታውቀዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ ልማቱ አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን እንዲችል ከማድረግ ባለፈ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ በዘላቂነት እንዲያረጋገጥ የጎላ ሚና እንዳለው ነው ያስረዱት።
በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አርሶ አደር መልኬ መለሰ እንዳሉት፤ ባለፈው የመኸር ወቅት ''ሻጋ'' የተባለውን የሩዝ ምርጥ ዘር ተጠቅመው ካለሙት አንድ ሄክታር መሬት 60 ኩንታል ምርት አግኝተዋል።
የተሻሻሉና ምርታማ የሆኑ የሩዝ ዝርያዎች ተደራሽ መደረጋቸው የእሳቸውንና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርታማነት እያደገ እንዲመጣ ማገዙን ተናግረዋል።
በዚህም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ነው የገለጹት።
ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ተዋቸው ፈጠነ በበኩላቸው፤ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ ዕጥረት ቢያጋጥምም በሩዝ ሰብል ካለሙት አንድ ሄክታር ተኩል መሬት 65 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
‘‘ምርታማነትን ለማሳደግ በምናደርገው ጥረት ዋነኛ ችግራችን የማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦትና ጥራቱን የጠበቀ የሩዝ መፈልፈያ ማሽን አለመኖር ነው’’ ያሉት ደግሞ ሌላኛው የወረዳው አርሶ አደር ዘላለም አስፋው ናቸው።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ አርሶ አደሩ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት ገጥሟቸው የነበረ ቢሆንም በአንድ ሄክታር መሬት ካለሙት የሩዝ ሰብል ከ50 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ተናገረዋል።
በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በሩዝ ሰብል ከለማው 61 ሺህ ሄክታር መሬት 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
የጉጂ አባገዳዎች ህገ ደንቦችን አሳወቁ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የጉጂ አባገዳዎች ለሚቀጥሉት ስምንት ዓመታት በሥርዓቱ መሠረት መተግበር ያለባቸውን የተለያዩ ድንጋጌዎችን አሳለፉ።
በጉጂ ዞን አዶላ ከተማ በተካሄደው ድንጋጌዎችን የማሳወቅ መርሐ ግብር ከተላለፉ ህገ ደንቦች መካከል፤ የሴቶች መብት የተከበረ ስለመሆኑና ምድር ላይ ያሉ ፍጥረታት ሁሉ ክብር የሚገባቸው መሆኑ ይጠቀሳሉ።
በገዳ ሥርዓት ሰው መግደል፣ ሙስና መስጠትና መቀበል፣ ፍትህ ማዛባት፣ ሠላም ማደፍረስ፣ ነባር የገዳ ሥርዓትና ባህል መበረዝ፣ በማንኛውም ፍጥረት ላይ ወንጀል መፈፀምና ሌሎች ሀገራዊ እሴትን መፈፀም የተወገዘ ሆኑን በድንጋጌው ወቅት አስገንዝበል።
ከዚህም በተጨማሪ ለሠላምና ለአንድነት ሁሉም ሊታጋ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በአዶላ ከተማ አቅራቢያ አርዳ ጂላ በሚባለው ቦታ 75ኛ የጉጂ አባ ገዳዎች የ"ባሊ" ስልጣን ርክክብ መርሐ ግብር እየተከናወነ ሲሆን፤ የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ክፍለዮሐንስ አንበርብር
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የጉጂ አባገዳዎች ለሚቀጥሉት ስምንት ዓመታት በሥርዓቱ መሠረት መተግበር ያለባቸውን የተለያዩ ድንጋጌዎችን አሳለፉ።
በጉጂ ዞን አዶላ ከተማ በተካሄደው ድንጋጌዎችን የማሳወቅ መርሐ ግብር ከተላለፉ ህገ ደንቦች መካከል፤ የሴቶች መብት የተከበረ ስለመሆኑና ምድር ላይ ያሉ ፍጥረታት ሁሉ ክብር የሚገባቸው መሆኑ ይጠቀሳሉ።
በገዳ ሥርዓት ሰው መግደል፣ ሙስና መስጠትና መቀበል፣ ፍትህ ማዛባት፣ ሠላም ማደፍረስ፣ ነባር የገዳ ሥርዓትና ባህል መበረዝ፣ በማንኛውም ፍጥረት ላይ ወንጀል መፈፀምና ሌሎች ሀገራዊ እሴትን መፈፀም የተወገዘ ሆኑን በድንጋጌው ወቅት አስገንዝበል።
ከዚህም በተጨማሪ ለሠላምና ለአንድነት ሁሉም ሊታጋ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በአዶላ ከተማ አቅራቢያ አርዳ ጂላ በሚባለው ቦታ 75ኛ የጉጂ አባ ገዳዎች የ"ባሊ" ስልጣን ርክክብ መርሐ ግብር እየተከናወነ ሲሆን፤ የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ክፍለዮሐንስ አንበርብር
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
የኢትዮ-ቱርክ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ፕሮሞሽን መድረክ እየተካሄደ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ-ቱርክ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ፕሮሞሽን መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነርና የተርክየ ዛካርያ ከተማ 23 የንግድ ባለቤቶች ተገኝተዋል።
በፎረሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀና አርአያ ስላሴ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያና ተርክየ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው።
ከ100 በላይ የተርክየ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተሰማርተው ይገኛሉ። ውጤታማም ናቸው።
ተጨማሪ ኢንቨስተሮች ቢመጡ ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ኮሚሽነሯ፣ ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት አመታት የኢቨስትመንት ፖሊሲዋን አሻሽላለች። የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተካሄደ መሆኑንም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት አለት ያሉት ኮሚሽነር ሀና፣ የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የንግድ ልውውጥ ማደግ፣ የሰለጠነ ወጣት የሰው ሃይል መኖር፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለንግድና ኢንቨስትመንት የሰጠው ትኩረትና ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እንደ መግቢያ በር መሆኗ በኢትዮጵያ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ተጨማሪ እድሎች ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የተርክየ አምባሳደር እና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ በረክ ባራን በበኩላቸው፣ የተርክየ መርህ የጋራ ተጠቃሚነት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና ተርክየ የቆየና ትልቅ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው። የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት በንግድ ልውውጥ ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ጥንታዊ የዲፕሎማሲ መዲና ናት ያሉት አምባሳደሩ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የዲፕሎማሲ መዲና መሆኗን፤ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኤምባሲና አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ እ ንደሆነችም ገልጸዋል።
ይህም ተርክየ ከአፍሪካ ጋር ለመስራት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
***************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ-ቱርክ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ፕሮሞሽን መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነርና የተርክየ ዛካርያ ከተማ 23 የንግድ ባለቤቶች ተገኝተዋል።
በፎረሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀና አርአያ ስላሴ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያና ተርክየ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው።
ከ100 በላይ የተርክየ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተሰማርተው ይገኛሉ። ውጤታማም ናቸው።
ተጨማሪ ኢንቨስተሮች ቢመጡ ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ኮሚሽነሯ፣ ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት አመታት የኢቨስትመንት ፖሊሲዋን አሻሽላለች። የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተካሄደ መሆኑንም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት አለት ያሉት ኮሚሽነር ሀና፣ የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የንግድ ልውውጥ ማደግ፣ የሰለጠነ ወጣት የሰው ሃይል መኖር፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለንግድና ኢንቨስትመንት የሰጠው ትኩረትና ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እንደ መግቢያ በር መሆኗ በኢትዮጵያ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ተጨማሪ እድሎች ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የተርክየ አምባሳደር እና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ በረክ ባራን በበኩላቸው፣ የተርክየ መርህ የጋራ ተጠቃሚነት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና ተርክየ የቆየና ትልቅ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው። የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት በንግድ ልውውጥ ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ጥንታዊ የዲፕሎማሲ መዲና ናት ያሉት አምባሳደሩ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የዲፕሎማሲ መዲና መሆኗን፤ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኤምባሲና አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ እ ንደሆነችም ገልጸዋል።
ይህም ተርክየ ከአፍሪካ ጋር ለመስራት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
በዞኑ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ብር የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጥቷል
***************
(ኢ ፕ ድ)
በዞኑ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ብር የኢንቨስትመንት ፈቃድ ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሥራ የማይገቡ ኢንቨስተሮች ለልማት የተሰጣቸውን መሬት እንደሚነጠቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙዔል ፎላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ በዞኑ ከ3 ቢሊዮን 680 ሚሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል፡፡
እነዚህ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ እንዲያገኙ ከሚመለከተው አካል ጋር በጋራ ተሠርቷል፡፡
ፈቃድ የተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 53 የሚደርሱ መሆናቸውን የተናገሩት አስተዳዳሪው፤ ከኢንቨስትመንቶቹ ውስጥ ወደሥራ የገቡ እና በሂደት ላይ የሚገኙ ስለመኖራቸውም አብራርተዋል፡፡ ወደ ዞኑ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍላጎት ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ኢንቨስትመንቶቹ በገጠር እርሻ፤ በከተማ አገልግሎት ዘርፍ፣ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች እና በከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ ጭምር የተሠማሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የአካባቢው ተወላጅ ዲያስፖራዎች አብዛኛውን የኢንቨስትመንት ክፍል እንደሚሸፍኑም
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120887
***************
(ኢ ፕ ድ)
በዞኑ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ብር የኢንቨስትመንት ፈቃድ ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሥራ የማይገቡ ኢንቨስተሮች ለልማት የተሰጣቸውን መሬት እንደሚነጠቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙዔል ፎላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ በዞኑ ከ3 ቢሊዮን 680 ሚሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል፡፡
እነዚህ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ እንዲያገኙ ከሚመለከተው አካል ጋር በጋራ ተሠርቷል፡፡
ፈቃድ የተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 53 የሚደርሱ መሆናቸውን የተናገሩት አስተዳዳሪው፤ ከኢንቨስትመንቶቹ ውስጥ ወደሥራ የገቡ እና በሂደት ላይ የሚገኙ ስለመኖራቸውም አብራርተዋል፡፡ ወደ ዞኑ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍላጎት ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ኢንቨስትመንቶቹ በገጠር እርሻ፤ በከተማ አገልግሎት ዘርፍ፣ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች እና በከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ ጭምር የተሠማሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የአካባቢው ተወላጅ ዲያስፖራዎች አብዛኛውን የኢንቨስትመንት ክፍል እንደሚሸፍኑም
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120887
በአዲስ አበባ በስድስት ወራት ከሁለት ሺህ 800 በላይ የትዳር ፍቺ ተመዝግቧል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ሁለት ሺህ 813 ፍቺዎች እና 16 ሺህ 933 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ለኢፕድ በላኩት መግለጫ እንደገለጹት፤ ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ ከተመዘገበው ጠቅላላ ኩነት 181 ሺህ 983 ልደት፣ 16 ሺህ 933 ጋብቻ፣ 2 ሺህ 813 ፍቺ እና 8 ሺህ 761 ሞት ተመዝግቧል።
በሳሙኤል ወንድወሰን
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ሁለት ሺህ 813 ፍቺዎች እና 16 ሺህ 933 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ለኢፕድ በላኩት መግለጫ እንደገለጹት፤ ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ ከተመዘገበው ጠቅላላ ኩነት 181 ሺህ 983 ልደት፣ 16 ሺህ 933 ጋብቻ፣ 2 ሺህ 813 ፍቺ እና 8 ሺህ 761 ሞት ተመዝግቧል።
በሳሙኤል ወንድወሰን
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ያልተፈቀደ አገልገሎት ሲሰጡ በተገኙ 125 ማሳጅ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ
******
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት በመዲናዋ ከተቀመጠው የአገልግሎት ደረጃ ዉጪ አገልግሎት ሲሰጡ በተገኙ 125 ማሳጅ ቤቶች ላይ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን የማሳጅ ቤቶችን ህጋዊነት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሰፋ ተሬሳ እንደተናገሩት፤ ማሳጅ ቤቶች ለማህበረሰቡ መጤ ባህል ከማውረስ ባሻገር አምራቹን ዜጋ ወዳልተፈለገ መንገድ እንዲገባ እያደረጉ ናቸው።
በማሳጅ ቤቶች ላይ የሚደረገው የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ እደሚቀጥል ገልጸዋል።
በባለስልጣኑ የምግብና ጤንነት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ሚሬሳ ሚዴቅሳ በወቅቱ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ161 ማሳጅ ቤቶች ላይ ቁጥጥርና የክትትል ስራ ተሰርቷል።
በቁጥጥር ስራው 125 ማሳጅ ቤቶች ከተቀመጠው የአገልግሎት ደረጃ ዉጪ አገልግሎት ሲሰጡ የተገኙ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 76 የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም 49 ማሳጅ ቤቶች እንዲታሸጉ ተደርጓል ብለዋል።
በአማን ረሺድ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት በመዲናዋ ከተቀመጠው የአገልግሎት ደረጃ ዉጪ አገልግሎት ሲሰጡ በተገኙ 125 ማሳጅ ቤቶች ላይ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን የማሳጅ ቤቶችን ህጋዊነት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሰፋ ተሬሳ እንደተናገሩት፤ ማሳጅ ቤቶች ለማህበረሰቡ መጤ ባህል ከማውረስ ባሻገር አምራቹን ዜጋ ወዳልተፈለገ መንገድ እንዲገባ እያደረጉ ናቸው።
በማሳጅ ቤቶች ላይ የሚደረገው የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ እደሚቀጥል ገልጸዋል።
በባለስልጣኑ የምግብና ጤንነት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ሚሬሳ ሚዴቅሳ በወቅቱ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ161 ማሳጅ ቤቶች ላይ ቁጥጥርና የክትትል ስራ ተሰርቷል።
በቁጥጥር ስራው 125 ማሳጅ ቤቶች ከተቀመጠው የአገልግሎት ደረጃ ዉጪ አገልግሎት ሲሰጡ የተገኙ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 76 የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም 49 ማሳጅ ቤቶች እንዲታሸጉ ተደርጓል ብለዋል።
በአማን ረሺድ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
የአፍሪካ አባቶችን ይተዋወቁ‼️
#ቀዳማዊ_ኃይለሥላሴ
የግንቦት 1955 ዓ.ም.32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆንም ኢትዮጵያ በመሪዋ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የመሪነት ሚና ተጫውታለች።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱ አማረኛ ነበር።
#ቀዳማዊ_ኃይለሥላሴ
የግንቦት 1955 ዓ.ም.32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆንም ኢትዮጵያ በመሪዋ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የመሪነት ሚና ተጫውታለች።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱ አማረኛ ነበር።
ኢትዮጵያና አንጎላ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
***
(ኢ.ፕ.ድ)
ከ44ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን ኢትዮጵያና አንጎላ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ እና የአንጎላው አቻቸው ቴት አንቶኒዮ ተፈራርመዋል።
በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ፍሰሀ ሻውል እንደገለፁት፤ በሀገራቱ መካከል የተፈረመው ስምምነት ሁለት አይነት ይዘት አለው።
የመጀመሪያው ለተቋማት ህጋዊ ማዕቀፍ የሚሰጥ አጠቃላይ የትብብር ስምምነት መሆኑን ጠቅሰው ሁለተኛው የፓለቲካ ምክክር ስምምነት መፈራረማቸውን ገልጸዋል።
ሁለቱ ሀገራት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ መስኮች ለመተባበር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር በማድረግ ወደ ፊት ተጨማሪ ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸውም ተገልጿል።
በተጨማሪም አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከዝምባብዌ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ፌድሪክ ሻቫ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው ሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን መድረክን ተባብሮ ለማዘጋጀት መመካከራቸውን ጠቅሰው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን አምባሳደር ታዬ ገልጸዋል።
ሁለቱ ሀገራት በግብርና ቱሪዝም በሌሎች ዘርፎችም ለመስራት መነጋገራቸውም ተገልጿል።
44ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።
በማርቆስ በላይ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
***
(ኢ.ፕ.ድ)
ከ44ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን ኢትዮጵያና አንጎላ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ እና የአንጎላው አቻቸው ቴት አንቶኒዮ ተፈራርመዋል።
በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ፍሰሀ ሻውል እንደገለፁት፤ በሀገራቱ መካከል የተፈረመው ስምምነት ሁለት አይነት ይዘት አለው።
የመጀመሪያው ለተቋማት ህጋዊ ማዕቀፍ የሚሰጥ አጠቃላይ የትብብር ስምምነት መሆኑን ጠቅሰው ሁለተኛው የፓለቲካ ምክክር ስምምነት መፈራረማቸውን ገልጸዋል።
ሁለቱ ሀገራት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለያዩ መስኮች ለመተባበር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር በማድረግ ወደ ፊት ተጨማሪ ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸውም ተገልጿል።
በተጨማሪም አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከዝምባብዌ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ፌድሪክ ሻቫ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው ሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን መድረክን ተባብሮ ለማዘጋጀት መመካከራቸውን ጠቅሰው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን አምባሳደር ታዬ ገልጸዋል።
ሁለቱ ሀገራት በግብርና ቱሪዝም በሌሎች ዘርፎችም ለመስራት መነጋገራቸውም ተገልጿል።
44ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።
በማርቆስ በላይ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
የአፍሪካ አባቶችን ይተዋወቁ‼️
#አህመድ_አሂድጆ
ኢትዮጵያ “የሞኖሮቪያ” እና “የካዛብላንካ” ቡድን በሚል ተከፍለው የነበሩትን የአፍሪካ አገሮች አዲስ አበባ ላይ በማገናኘትና ልዩነቶችን በማለዘብ ወደ አንድ የጋራ አቋም እንዲመጡ አድርጋለች።
በዚሁ መሰረት ግንቦት 1955 ዓ.ም. 32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆን ፊርማቸውን ካኖሩ አገራት መካከል የካሜሮን የቀድሞ ፕሬዝዳንት አህመድ አሂድጆ አንዱ ናቸው።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱም አማረኛ ነበር።
#አህመድ_አሂድጆ
ኢትዮጵያ “የሞኖሮቪያ” እና “የካዛብላንካ” ቡድን በሚል ተከፍለው የነበሩትን የአፍሪካ አገሮች አዲስ አበባ ላይ በማገናኘትና ልዩነቶችን በማለዘብ ወደ አንድ የጋራ አቋም እንዲመጡ አድርጋለች።
በዚሁ መሰረት ግንቦት 1955 ዓ.ም. 32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆን ፊርማቸውን ካኖሩ አገራት መካከል የካሜሮን የቀድሞ ፕሬዝዳንት አህመድ አሂድጆ አንዱ ናቸው።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱም አማረኛ ነበር።
የሐሮማያ ሐይቅ ተስፋና ስጋት
**************
(ኢ ፕ ድ)
አካባቢው ማራኪ ነው፡፡ በሐሮማያ ሀይቅ ዙሪያ ያሉ እርሻዎች አካባቢውን አረንጓዴ ስጋጃ የተነጠፈ አስመስለውታል፡፡
የአዕዋፋት ድምፅ፣ የጀልባዎች ቀዘፋና የአካባቢው ሥነ ምሕዳር የጎብኝዎችን ቀልብ ይስባል፡፡
በ1996 ዓ.ም ሐይቁ በዓይናችን እያየነው ደረቀ የሚለው ሐሮማያ ሐይቅ አጠገብ በምትገኘው ማያ ከተማ ተወልዶ ያደገው አቶ ረመዳን አሊ፤ በወቅቱ ሐይቁ ሲደርቅ እናትና አባታችንን እንዳጣን ሁላችንም የአካባቢው ነዋሪዎች አዘንን፣ ተከፋን፣ ዳግመኛም ሐይቁ ይመለሳል ብለንም አላሰብንም ይላል፡፡
የአምላክ ሥራ አይታወቅም፤ ያልገመትነው ነገር ተከሰተ፡፡
ሐሮማያ ሐይቅ ከ17 ዓመታት በኋላ ተመልሶ መጣ፡፡ እኛም ዳግም እንደተወለደ ሰው ተደሰትን፣ ጨፍርን፣ እንደ ዓይናችን ብሌን የምናየውን ሐይቅ በደስታ እንባ ተቀበልነው ብሏል፡፡
2012 ዓ.ም ኃይለኛ ዝናብ በመዝነቡ ሐይቁ ተመልሶ እንደመጣ የሚያስታውሰው አቶ ረመዳን፤ በአሁኑ ጊዜም 360 ወጣቶች ተደራጅተው ሐይቁን በማስጎብኘትና ዓሳ በማጥመድ ሥራ ላይ ተሠማርተው እንደሚገኙ ነግሮናል።
ሐይቁ በመመለሱ ደስተኞች ነን። እኛም ሆነ ልጆቻችን ከ17 ዓመታት በኋላ ወደ ቀድሞ ሥራችን ተመልሰናል
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120863
**************
(ኢ ፕ ድ)
አካባቢው ማራኪ ነው፡፡ በሐሮማያ ሀይቅ ዙሪያ ያሉ እርሻዎች አካባቢውን አረንጓዴ ስጋጃ የተነጠፈ አስመስለውታል፡፡
የአዕዋፋት ድምፅ፣ የጀልባዎች ቀዘፋና የአካባቢው ሥነ ምሕዳር የጎብኝዎችን ቀልብ ይስባል፡፡
በ1996 ዓ.ም ሐይቁ በዓይናችን እያየነው ደረቀ የሚለው ሐሮማያ ሐይቅ አጠገብ በምትገኘው ማያ ከተማ ተወልዶ ያደገው አቶ ረመዳን አሊ፤ በወቅቱ ሐይቁ ሲደርቅ እናትና አባታችንን እንዳጣን ሁላችንም የአካባቢው ነዋሪዎች አዘንን፣ ተከፋን፣ ዳግመኛም ሐይቁ ይመለሳል ብለንም አላሰብንም ይላል፡፡
የአምላክ ሥራ አይታወቅም፤ ያልገመትነው ነገር ተከሰተ፡፡
ሐሮማያ ሐይቅ ከ17 ዓመታት በኋላ ተመልሶ መጣ፡፡ እኛም ዳግም እንደተወለደ ሰው ተደሰትን፣ ጨፍርን፣ እንደ ዓይናችን ብሌን የምናየውን ሐይቅ በደስታ እንባ ተቀበልነው ብሏል፡፡
2012 ዓ.ም ኃይለኛ ዝናብ በመዝነቡ ሐይቁ ተመልሶ እንደመጣ የሚያስታውሰው አቶ ረመዳን፤ በአሁኑ ጊዜም 360 ወጣቶች ተደራጅተው ሐይቁን በማስጎብኘትና ዓሳ በማጥመድ ሥራ ላይ ተሠማርተው እንደሚገኙ ነግሮናል።
ሐይቁ በመመለሱ ደስተኞች ነን። እኛም ሆነ ልጆቻችን ከ17 ዓመታት በኋላ ወደ ቀድሞ ሥራችን ተመልሰናል
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120863
መንግሥታዊ ያለሆኑ ድርጅቶች ለ28 አቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤት አበረከቱ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ሀቢታት ፎር ሂውማኒቲ ኢትዮጵያና ኤልጂ ኤሌክትሮኒክስ በትብብር በየካና ጉለሌ ክፍለከተሞች ለሚገኙ 28 አቅመ ደካሞች የመኖሪያቤቶችና ልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫዎችን አበረከቱ።
በመርሀግብሩ የተገኙት በኢትዮጵያ የኮሪያ አምባሳደር ሚስተር ጃንግ ካንግ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለኮሪያ የዋለችውን ነፍስ እስከመስጠት የደረሰ ውለታ አትረሳም።
አሁን ኮሪያ በተራዋ ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖራትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ድጋፎች የምትቀጥል ይሆናል።
የሀቢታት ፎር ሂውማኒቲ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ዳይሬክተርና የተቋሙ የአፍሪካ ህብረት ተወካይ አቶ ይጥና ተካልኝ እንዳሉት፤ ተቋሙ የኮሪያ ዘማች ቤተሰቦችን ጨምሮ ብዙዎችን ከጉስቁልና እንዲላቀቁ ያስቻለ ነው።
ተቋሙ ባለፉት 29 ዓመታት 165ሺህ ቤተሰቦችን ወይም 826ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ ሲሆን በዛሬው ፕሮጀክትም 28 ቤቶችን ሰርቶ አስረክቧል።
በዳግማዊት ግርማ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ሀቢታት ፎር ሂውማኒቲ ኢትዮጵያና ኤልጂ ኤሌክትሮኒክስ በትብብር በየካና ጉለሌ ክፍለከተሞች ለሚገኙ 28 አቅመ ደካሞች የመኖሪያቤቶችና ልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫዎችን አበረከቱ።
በመርሀግብሩ የተገኙት በኢትዮጵያ የኮሪያ አምባሳደር ሚስተር ጃንግ ካንግ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለኮሪያ የዋለችውን ነፍስ እስከመስጠት የደረሰ ውለታ አትረሳም።
አሁን ኮሪያ በተራዋ ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖራትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ድጋፎች የምትቀጥል ይሆናል።
የሀቢታት ፎር ሂውማኒቲ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ዳይሬክተርና የተቋሙ የአፍሪካ ህብረት ተወካይ አቶ ይጥና ተካልኝ እንዳሉት፤ ተቋሙ የኮሪያ ዘማች ቤተሰቦችን ጨምሮ ብዙዎችን ከጉስቁልና እንዲላቀቁ ያስቻለ ነው።
ተቋሙ ባለፉት 29 ዓመታት 165ሺህ ቤተሰቦችን ወይም 826ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ ሲሆን በዛሬው ፕሮጀክትም 28 ቤቶችን ሰርቶ አስረክቧል።
በዳግማዊት ግርማ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
የአፍሪካ አባቶችን ይተዋወቁ
#ማውረሥ_ያመጎ
ኢትዮጵያ “የሞኖሮቪያ” እና “የካዛብላንካ” ቡድን በሚል ተከፍለው የነበሩትን የአፍሪካ አገሮች አዲስ አበባ ላይ በማገናኘትና ልዩነቶችን በማለዘብ ወደ አንድ የጋራ አቋም እንዲመጡ አድርጋለች።
በዚሁ መሰረት ግንቦት 1955 ዓ.ም 32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆን ፊርማቸውን ካኖሩ አገራት መካከል የቀድሞ የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ማውረሥ ያመጎ አንዱ ናቸው።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱም አማረኛ ነበር።
#ማውረሥ_ያመጎ
ኢትዮጵያ “የሞኖሮቪያ” እና “የካዛብላንካ” ቡድን በሚል ተከፍለው የነበሩትን የአፍሪካ አገሮች አዲስ አበባ ላይ በማገናኘትና ልዩነቶችን በማለዘብ ወደ አንድ የጋራ አቋም እንዲመጡ አድርጋለች።
በዚሁ መሰረት ግንቦት 1955 ዓ.ም 32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆን ፊርማቸውን ካኖሩ አገራት መካከል የቀድሞ የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ማውረሥ ያመጎ አንዱ ናቸው።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱም አማረኛ ነበር።