Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ኖርዌይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ጠንካራ ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለፀች
******
(ኢ ፕ ድ)

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ከኖር የልማት ሚኒስትር አኔ ቤዝ ቲቭነሪም ጋር በሁለትዮሽና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ።

በውይይታቸውም በአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ በደን ልማት፣ በትምህርት፣ በግብርና ዘርፍና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።

አምባሳደር ታዬ ኖርዌይ በሁኔታዎች የማትቀየር የኢትዮጵያ ጠንካራ ወዳጅ አገር መሆኗን ገልፀዋል።

ኖርዌይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ጠንካራ ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥልም ሚኒስትሯ ገልፀዋል።

ሁሉቱ ሚኒስትሮች ሁለቱ አገራት በትብብር በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መክረዋል።

የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"ወደ አፍሪካ ኅብረት መዲና እንኳን ደኅና መጣችሁ" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
ኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ የስትራቴጂያዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ
*****
(ኢ ፕ ድ)

ኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የስትራቴጂያዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ እና የደቡብ አፍሪካ አቻቸው ናሌዲ ፓንዶር ስምምነቱን ዛሬ ከ44ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ ጎን ለጎን በተካሄደ ስነ ስርዓት ላይ ፈርመዋል።

ስትራቴጂያዊ አጋርነቱ በፀረ-አፓርታይድ ትግል ወቅት የተፈጠረውን ጠንካራ ወዳጅነት መሰረት ያደረገ ፖለቲካዊ ትብብርን ለማሳደግና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶችን ለማስፋት ያለመ ነው።

ስምምነቱ በተለያዩ መስኮች ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማስፋትና ለማጠናከር ያለመ ነውም ተብሏል።

በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ በጋራ ጥቅም ጉዳዮች ላይ ትብብር ማድረግ ከስምምነቱ ዋና ዓላማዎች አንዱ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
አምባሳደር ታዬአጽቀሥላሴ ከቤኒን አቻቸው ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል
***
(ኢ ፕ ድ)

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከቤኒን አቻቸው ኦሉሸጉን ባካሪ ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

በውይይቱ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ቤኒን በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

ኦሉሼጉን ባካሪ በበኩላቸው ቤኒን በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ መቅሰም ትፈልጋለች ብለዋል።

የፖለቲካ ግንኙነቶችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ለማሳደግ ትክክለኛው ጊዜ አሁን እንደሆነም ተስማምተዋል።

የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
ለአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የሀገራት መሪዎች አዲሰ አበባ እየገቡ ነው‼️

በ37ኛው የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ የስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ዲላሚኒ፤  የሴራሊዮን ምክትል ፕሬዝዳንት መሀመድ ዡሌ ዣሎህ፤ የቻድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱክሴ ማስራ፤ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ቦላ አህመድ ቲኑቡ፤ የቶጎ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ቶሜጋህ ዶግቤ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል።

የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
የብራዚል ፕሬዝዳንት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
***

(ኢ ፕ ድ)

የብራዚል ፕሬዝዳንት ሊዊዝ ኢናሲዬ ሉላ ዳ ሲልቫ ማምሻውን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፕሬዝዳንት ሉላ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ስላሴ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።

የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
«አፍሪካ የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት በዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ያላትን ድርሻ ልታሳድግ ይገባል»
– አልበርት ሙቻንጋ
የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የአፍሪካ ድርሻ 2 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ በመሆኑ ሀገራት የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት ድርሻቸውን ለማሳደግ ሊሠሩ ይገባል ሲሉ የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር አልበርት ሙቻንጋ ገለጹ።

ኮሚሽነር አልበርት ሙቻንጋ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የዓለም ኢኮኖሚ ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ ቢመጣም ከዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የአፍሪካ ድርሻ 2 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ ነው።

በመሆኑ ሀገራት ይህንን በመገንዘብ የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት ድርሻቸውን ለማሳደግ ሊሠሩ ይገባል።

ይህም የሚያሳየው የአፍሪካ ሀገራት ምርትን በበቂ መጠን እያመረቱ ላለመሆኑ ማሳያ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በመሆኑም የግብርና ምርትን ማሳደግ፣ የተቀነባበሩና እሴት የተጨመረባቸው...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120946
«ዓድዋ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አፍሪካውያንን አንድ ያደረገ ድል ነው» አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ
– የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓድዋ ድል በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አፍሪካውያንን ቀጣይነት ባለው መልኩ አንድ በማድረግ በኩል ትልቁን ድርሻ መውሰዱን አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ።

በ37ኛው አፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔና በ44ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ለመታደም አዲስ አበባ የገቡ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከጉብኝቱ በኋላ ለእንግዶቹ ባደረጉት የእራት ግብዣ ላይ እንደተናገሩት፤ በዓድዋ ድል የተስተዋለው ታሪክ የአፍሪካን ፅናትና ጥንካሬ የሚያመለክት እንደሆነ አብራርተዋል።

ድሉ ለቅኝ ግዛት ተቃውሞ ትልቅ ሚና የተጫወተና የፓን አፍሪካኒዝምን ዕድገት ያሳየ ነው ብለውም፤ በዚህም በዓለም...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120955