የብራዚል ፕሬዝዳንት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
***
(ኢ ፕ ድ)
የብራዚል ፕሬዝዳንት ሊዊዝ ኢናሲዬ ሉላ ዳ ሲልቫ ማምሻውን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንት ሉላ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ስላሴ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
***
(ኢ ፕ ድ)
የብራዚል ፕሬዝዳንት ሊዊዝ ኢናሲዬ ሉላ ዳ ሲልቫ ማምሻውን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንት ሉላ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ስላሴ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
«አፍሪካ የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት በዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ያላትን ድርሻ ልታሳድግ ይገባል»
– አልበርት ሙቻንጋ
የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የአፍሪካ ድርሻ 2 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ በመሆኑ ሀገራት የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት ድርሻቸውን ለማሳደግ ሊሠሩ ይገባል ሲሉ የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር አልበርት ሙቻንጋ ገለጹ።
ኮሚሽነር አልበርት ሙቻንጋ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የዓለም ኢኮኖሚ ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ ቢመጣም ከዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የአፍሪካ ድርሻ 2 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ ነው።
በመሆኑ ሀገራት ይህንን በመገንዘብ የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት ድርሻቸውን ለማሳደግ ሊሠሩ ይገባል።
ይህም የሚያሳየው የአፍሪካ ሀገራት ምርትን በበቂ መጠን እያመረቱ ላለመሆኑ ማሳያ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በመሆኑም የግብርና ምርትን ማሳደግ፣ የተቀነባበሩና እሴት የተጨመረባቸው...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120946
– አልበርት ሙቻንጋ
የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የአፍሪካ ድርሻ 2 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ በመሆኑ ሀገራት የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት ድርሻቸውን ለማሳደግ ሊሠሩ ይገባል ሲሉ የአፍሪካ ኅብረት የኢኮኖሚ ልማት፣ ቱሪዝም፣ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ማዕድን ኮሚሽነር አልበርት ሙቻንጋ ገለጹ።
ኮሚሽነር አልበርት ሙቻንጋ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ የዓለም ኢኮኖሚ ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ ቢመጣም ከዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ የአፍሪካ ድርሻ 2 ነጥብ 8 በመቶ ብቻ ነው።
በመሆኑ ሀገራት ይህንን በመገንዘብ የቴክኖሎጂ ሽግግር በማምጣት ድርሻቸውን ለማሳደግ ሊሠሩ ይገባል።
ይህም የሚያሳየው የአፍሪካ ሀገራት ምርትን በበቂ መጠን እያመረቱ ላለመሆኑ ማሳያ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በመሆኑም የግብርና ምርትን ማሳደግ፣ የተቀነባበሩና እሴት የተጨመረባቸው...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120946
«ዓድዋ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አፍሪካውያንን አንድ ያደረገ ድል ነው» አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ
– የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓድዋ ድል በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አፍሪካውያንን ቀጣይነት ባለው መልኩ አንድ በማድረግ በኩል ትልቁን ድርሻ መውሰዱን አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ።
በ37ኛው አፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔና በ44ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ለመታደም አዲስ አበባ የገቡ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከጉብኝቱ በኋላ ለእንግዶቹ ባደረጉት የእራት ግብዣ ላይ እንደተናገሩት፤ በዓድዋ ድል የተስተዋለው ታሪክ የአፍሪካን ፅናትና ጥንካሬ የሚያመለክት እንደሆነ አብራርተዋል።
ድሉ ለቅኝ ግዛት ተቃውሞ ትልቅ ሚና የተጫወተና የፓን አፍሪካኒዝምን ዕድገት ያሳየ ነው ብለውም፤ በዚህም በዓለም...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120955
– የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓድዋ ድል በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አፍሪካውያንን ቀጣይነት ባለው መልኩ አንድ በማድረግ በኩል ትልቁን ድርሻ መውሰዱን አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ።
በ37ኛው አፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔና በ44ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ለመታደም አዲስ አበባ የገቡ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከጉብኝቱ በኋላ ለእንግዶቹ ባደረጉት የእራት ግብዣ ላይ እንደተናገሩት፤ በዓድዋ ድል የተስተዋለው ታሪክ የአፍሪካን ፅናትና ጥንካሬ የሚያመለክት እንደሆነ አብራርተዋል።
ድሉ ለቅኝ ግዛት ተቃውሞ ትልቅ ሚና የተጫወተና የፓን አፍሪካኒዝምን ዕድገት ያሳየ ነው ብለውም፤ በዚህም በዓለም...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120955
በክልሉ አንድ ሚሊዮን የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መጽሀፍ ተሰራጭቷል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከአሥር ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ መምህራን ሥልጠና ተሰጥቷል
በ2016 የትምህርት ዘመን አንድ ሚሊዮን የሁለተኛ ደረጃ የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመማሪያ መጽሀፍ ለትምህርት ቤቶች ማሰራጨት መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ከአሥር ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ የትምህርት ቤት አመራሮችና መምህራን ሥልጠና ተሰጥቷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ በክልሉ አንድ ሚሊዮን የሁለተኛ ደረጃ የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመማሪያ መጽሐፍት ተሰራጭቷል።
አሁን ባለው ሁኔታ አንድ መጽሐፍ ለአራት ተማሪዎች ይዳረሳል ያሉት አቶ አንተነህ፤ በክልሉ የትምህርት ጥራት ለማሻሻልና የመማሪያ ግብዓት ማሟላት እንዲቻል በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
አቶ አንተነህ አክለውም፤ በክልሉ 50 መምህራን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከዋና መጽሐፍ አዘጋጆች ሥልጠና በመውሰድ ከአስር ሺህ 500 በላይ ለሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች በሦስት ምዕራፍ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥተዋል ብለዋል።
በተጨማሪም የመምህራን የአቅም ውስንነት ለመሙላት በየደረጃው ይዘትን መሠረት ያደረገ ሥልጠና መሰጠቱን አቶ አንተነህ …….
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120975
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከአሥር ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ መምህራን ሥልጠና ተሰጥቷል
በ2016 የትምህርት ዘመን አንድ ሚሊዮን የሁለተኛ ደረጃ የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመማሪያ መጽሀፍ ለትምህርት ቤቶች ማሰራጨት መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ከአሥር ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ የትምህርት ቤት አመራሮችና መምህራን ሥልጠና ተሰጥቷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ በክልሉ አንድ ሚሊዮን የሁለተኛ ደረጃ የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመማሪያ መጽሐፍት ተሰራጭቷል።
አሁን ባለው ሁኔታ አንድ መጽሐፍ ለአራት ተማሪዎች ይዳረሳል ያሉት አቶ አንተነህ፤ በክልሉ የትምህርት ጥራት ለማሻሻልና የመማሪያ ግብዓት ማሟላት እንዲቻል በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
አቶ አንተነህ አክለውም፤ በክልሉ 50 መምህራን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከዋና መጽሐፍ አዘጋጆች ሥልጠና በመውሰድ ከአስር ሺህ 500 በላይ ለሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች በሦስት ምዕራፍ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥተዋል ብለዋል።
በተጨማሪም የመምህራን የአቅም ውስንነት ለመሙላት በየደረጃው ይዘትን መሠረት ያደረገ ሥልጠና መሰጠቱን አቶ አንተነህ …….
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120975
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
ዛሬ ማለዳ የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ከቀዳማዊት እመቤት ጃንጃ ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር በመሆን በዓድዋ ድል ሃውልት ስር የአበባ ጉንጉን በማኖር የዓድዋ ድል መታሰቢያን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የካቲት 8 ቀን 2016 ዓ.ም
ዛሬ ማለዳ የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ከቀዳማዊት እመቤት ጃንጃ ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር በመሆን በዓድዋ ድል ሃውልት ስር የአበባ ጉንጉን በማኖር የዓድዋ ድል መታሰቢያን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የካቲት 8 ቀን 2016 ዓ.ም
«ኩባ ባለፉት ሦስት ዓመታት የቆየውን የኢትዮጵያን ወዳጅነትና አጋርነት በተግባር አጠናክራ አሳይታለች»
- አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) በኩባ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
ኩባና ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት የዘለቀውን ወዳጅነትና አጋርነት አጠናክረው መቀጠላቸውን በኩባ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) አስታወቁ።
በኩባ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኩባ የኢትዮጵያ ጥንታዊና ታሪካዊ ወዳጅ ናት። በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት ወቅት 17 ሺህ ወታደሮችን አሰልፋ ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መስዋዕትነት እስከመክፈል የደረሰ ድጋፍ አድርጋለች ያሉት አምባሳደሩ፤ ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የራሷን አስተዋፅዖ ስታደርግ የቆየች ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።
ኩባ በአንድ ሀገር ውስጥ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት አያስፈልግም የሚል ጽኑ አቋም አላት ያሉት አምባሳደሩ፤ በኩባ አቋም ኢትዮጵያ የውጭ ጫና ሳያስፈልጋት የራሷን ችግር በራሷ መፍታት የምትችል ሀገር ናት የሚል አቋም በማራመድ የቆየውን ግንኙነት አጠናክራለች ብለዋል። በተለይ ኩባ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር የነበራትን ወዳጅነትና አጋርነት አጠናክራ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120970
- አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) በኩባ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
ኩባና ኢትዮጵያ ለብዙ ዓመታት የዘለቀውን ወዳጅነትና አጋርነት አጠናክረው መቀጠላቸውን በኩባ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) አስታወቁ።
በኩባ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኩባ የኢትዮጵያ ጥንታዊና ታሪካዊ ወዳጅ ናት። በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት ወቅት 17 ሺህ ወታደሮችን አሰልፋ ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መስዋዕትነት እስከመክፈል የደረሰ ድጋፍ አድርጋለች ያሉት አምባሳደሩ፤ ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የራሷን አስተዋፅዖ ስታደርግ የቆየች ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።
ኩባ በአንድ ሀገር ውስጥ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት አያስፈልግም የሚል ጽኑ አቋም አላት ያሉት አምባሳደሩ፤ በኩባ አቋም ኢትዮጵያ የውጭ ጫና ሳያስፈልጋት የራሷን ችግር በራሷ መፍታት የምትችል ሀገር ናት የሚል አቋም በማራመድ የቆየውን ግንኙነት አጠናክራለች ብለዋል። በተለይ ኩባ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከኢትዮጵያ ጋር የነበራትን ወዳጅነትና አጋርነት አጠናክራ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120970
44ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ተጠናቀቀ
**
(ኢ.ፕ.ድ)
44ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ዛሬ ማለዳ ተጠናቋል።
ስብሰባው "ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣የሕይወት ዘመን፣ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“ በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2024 መሪ ቃል ሲካሄድ ቆይቷል።
በስብሰባው የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ዲፕሎማቶችና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል ።
ምክር ቤቱ ከጥር 6 እስከ 17 ቀን 2016 ዓ.ም 47ኛው የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ በተወያየባቸው አጀንዳዎች ላይ ምክክር አድርጓል።
ሌሊቱን በዘለቀው የምክር ቤቱ ስብሰባ የአፍሪካ ሕብረት ተቋማትና አደረጃጀቶች፣በምክር ቤቱ ስር የሚገኙ ኮሚቴዎችና ንዑሳን ኮሚቴዎች እንዲሁም የአጀንዳ 2063 የ10 ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጧል።
ሰላምና ደህንነት፣ ንግድና ትስስር፣ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣ትምህርት፣ግብርናና የአየር ንብረት ለውጥ፣ሰብዓዊ መብቶች፣ ስርዓተ ጾታና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም የተቋማትና አደረጃጀቶች ምርጫ ውይይት ከተደረገባቸው ዋንኛ አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም ለሚከናወነው 37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችንም አፅድቋል።
የአፍሪካ ሕብረት ተቋማትና አደረጃጀቶች መግለጫዎችን ጨምሮ የተለያዩ ሁነቶች ዛሬ እንደሚካሄዱ ከሕብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል።
የካቲት 8 ቀን 2016 ዓ.ም
**
(ኢ.ፕ.ድ)
44ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ዛሬ ማለዳ ተጠናቋል።
ስብሰባው "ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣የሕይወት ዘመን፣ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“ በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2024 መሪ ቃል ሲካሄድ ቆይቷል።
በስብሰባው የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ዲፕሎማቶችና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል ።
ምክር ቤቱ ከጥር 6 እስከ 17 ቀን 2016 ዓ.ም 47ኛው የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ በተወያየባቸው አጀንዳዎች ላይ ምክክር አድርጓል።
ሌሊቱን በዘለቀው የምክር ቤቱ ስብሰባ የአፍሪካ ሕብረት ተቋማትና አደረጃጀቶች፣በምክር ቤቱ ስር የሚገኙ ኮሚቴዎችና ንዑሳን ኮሚቴዎች እንዲሁም የአጀንዳ 2063 የ10 ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጧል።
ሰላምና ደህንነት፣ ንግድና ትስስር፣ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣ትምህርት፣ግብርናና የአየር ንብረት ለውጥ፣ሰብዓዊ መብቶች፣ ስርዓተ ጾታና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም የተቋማትና አደረጃጀቶች ምርጫ ውይይት ከተደረገባቸው ዋንኛ አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም ለሚከናወነው 37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችንም አፅድቋል።
የአፍሪካ ሕብረት ተቋማትና አደረጃጀቶች መግለጫዎችን ጨምሮ የተለያዩ ሁነቶች ዛሬ እንደሚካሄዱ ከሕብረቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል።
የካቲት 8 ቀን 2016 ዓ.ም
የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎትን ለማሻሻል ነጻ የቪድዮ ትምህርቶች እየተሰጡ ነው
***
(ኢ.ፕ.ድ)
በተማሪዎች ላይ የሚታየውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎትን ለማሻሻል ነጻ የቪድዮ ትምህርቶች እየተሰጠ መሆኑን ትምህርት ሚንስቴር አስታወቀ።
ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የስድስት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ እንደ ሀገር ለተፈጠረው የትምህርት ጥራት ስብራት አንዱ ምክንያት ተማሪዎች ትምህርቱ የሚሰጥበት ቋንቋ በቂ እውቀት አለመኖር ነው። በመሆኑም የቋንቋ ችግር በተለይ ከሁለተኛ ደረጃ ጀምሮ ተማሪዎች ያላቸው እውቀት የተገደበ እንዲሆን አደርጓል።
ይህንንም ለመቅረፍ ከአዲሱ ስርዓተ-ትምህርት ጋር የሚስማሙ፤ የተለያዩ ይዘት ያላቸው 305 አጫጭር ትምህርታዊ ቪድዮዎች በፖርታል ዌብ ላይ ተጭነው በነጻ (ያለ ዳታ) ተደራሽ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ቪዲዮዎቹ እንግሊዝኛ ቋንቋ አፍ መፍቻቸው በሆኑ ባለሙያዎች የተዘጋጁ ሲሆን ስለ ፖርታል ዌቡ አጠቃቀምም ለ4 ሺ 630 የእንግሊዝኛ መምህራን ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ተከናውኗል።
በዘላቂነት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችግርን ለመቅረፍ እንደ እቅድ ተቀምጦ የነበረው በርካታ የውጪ መምህራንን በድጋፍና በተለያዩ መንገዶቸ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት እንዲያስተምሩ ማድረግ ነበር። ለዚህም ከአምስት የእንግሊዝኛ ቋንቋ አፍ መፍቻቸው ከሆኑ ሀገራት ጋር ውይይቶች እየተደረጉ ቢሆንም በዚህ ወቅት መድረስ አልቻሉም ብለዋል።
በተጨማሪ ሁለተኛ ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አምጥቶ እንዲያስተምሩ ለማድረግ የተጀመሩ እንቅስቀሴዎች ቢኖሩም ግዜ የሚፈልጉ ሆነዋል። በመሆኑም እንደ አማራጭ የተዘጋጁ ቪዲዮችን ተደራሽ ማድረጉ ተመራጭ ሆኗል ነው ያሉት።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍ መፍቻ ቋንቋ ከመማር ጋር የተያያዙ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍም የትምህርት ሚንስቴር በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ለ2 ሺ 287 መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና በወሰዱ መምህራን ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡
በቀጣይም ትምህርት ሚንስቴር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ የሚፈጠሩ ተግዳሮቶችን ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ሚንስትሩ ጠቁመዋል።
በራስወርቅ ሙሉጌታ
***
(ኢ.ፕ.ድ)
በተማሪዎች ላይ የሚታየውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎትን ለማሻሻል ነጻ የቪድዮ ትምህርቶች እየተሰጠ መሆኑን ትምህርት ሚንስቴር አስታወቀ።
ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የስድስት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ እንደ ሀገር ለተፈጠረው የትምህርት ጥራት ስብራት አንዱ ምክንያት ተማሪዎች ትምህርቱ የሚሰጥበት ቋንቋ በቂ እውቀት አለመኖር ነው። በመሆኑም የቋንቋ ችግር በተለይ ከሁለተኛ ደረጃ ጀምሮ ተማሪዎች ያላቸው እውቀት የተገደበ እንዲሆን አደርጓል።
ይህንንም ለመቅረፍ ከአዲሱ ስርዓተ-ትምህርት ጋር የሚስማሙ፤ የተለያዩ ይዘት ያላቸው 305 አጫጭር ትምህርታዊ ቪድዮዎች በፖርታል ዌብ ላይ ተጭነው በነጻ (ያለ ዳታ) ተደራሽ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ቪዲዮዎቹ እንግሊዝኛ ቋንቋ አፍ መፍቻቸው በሆኑ ባለሙያዎች የተዘጋጁ ሲሆን ስለ ፖርታል ዌቡ አጠቃቀምም ለ4 ሺ 630 የእንግሊዝኛ መምህራን ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ተከናውኗል።
በዘላቂነት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችግርን ለመቅረፍ እንደ እቅድ ተቀምጦ የነበረው በርካታ የውጪ መምህራንን በድጋፍና በተለያዩ መንገዶቸ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት እንዲያስተምሩ ማድረግ ነበር። ለዚህም ከአምስት የእንግሊዝኛ ቋንቋ አፍ መፍቻቸው ከሆኑ ሀገራት ጋር ውይይቶች እየተደረጉ ቢሆንም በዚህ ወቅት መድረስ አልቻሉም ብለዋል።
በተጨማሪ ሁለተኛ ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አምጥቶ እንዲያስተምሩ ለማድረግ የተጀመሩ እንቅስቀሴዎች ቢኖሩም ግዜ የሚፈልጉ ሆነዋል። በመሆኑም እንደ አማራጭ የተዘጋጁ ቪዲዮችን ተደራሽ ማድረጉ ተመራጭ ሆኗል ነው ያሉት።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአፍ መፍቻ ቋንቋ ከመማር ጋር የተያያዙ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍም የትምህርት ሚንስቴር በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ለ2 ሺ 287 መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና በወሰዱ መምህራን ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡
በቀጣይም ትምህርት ሚንስቴር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ የሚፈጠሩ ተግዳሮቶችን ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ሚንስትሩ ጠቁመዋል።
በራስወርቅ ሙሉጌታ
ዘጠነኛውን ሀገር አቀፍ የከተሞች ፎረም ነገ ይጀመራል
******
(ኢ.ፕ.ድ)
ዘጠነኛውን ሀገር አቀፍ የከተሞች ፎረም “የዘመኑ ከተሞች ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በነገው እለት በወላይታ ሶዶ ከተማ ይካሄዳል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ኮሙንኬሽን ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ብላቴና ብርሃኑ ፎረሙን አስመልክተው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት ፤ በፎረሙ ከተሞች እርስ በርስ ልምድ የሚለዋወጡበትና የሚተዋወቁበት ነው ፡፡
የወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶችን ለመቀበል በቂ ዝግጅት መደረጉንም አስታውቀዋል፡፡
በፎረሙ ከ200 በላይ ከተሞች የሚሳተፉ ሲሆን ከ20 ሺህ በላይ ጎብኚዎችም ወደ ከተማዋ ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃልም ሲሉ ተናግረዋል ፡፡
ፎረሙ ከነገው ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል፡፡
በዳግማዊት አበበ
የካቲት 8/2016 ዓ.ም
******
(ኢ.ፕ.ድ)
ዘጠነኛውን ሀገር አቀፍ የከተሞች ፎረም “የዘመኑ ከተሞች ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በነገው እለት በወላይታ ሶዶ ከተማ ይካሄዳል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ኮሙንኬሽን ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ብላቴና ብርሃኑ ፎረሙን አስመልክተው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት ፤ በፎረሙ ከተሞች እርስ በርስ ልምድ የሚለዋወጡበትና የሚተዋወቁበት ነው ፡፡
የወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶችን ለመቀበል በቂ ዝግጅት መደረጉንም አስታውቀዋል፡፡
በፎረሙ ከ200 በላይ ከተሞች የሚሳተፉ ሲሆን ከ20 ሺህ በላይ ጎብኚዎችም ወደ ከተማዋ ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃልም ሲሉ ተናግረዋል ፡፡
ፎረሙ ከነገው ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ቀናት የሚካሄድ ይሆናል፡፡
በዳግማዊት አበበ
የካቲት 8/2016 ዓ.ም