የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
ዛሬ ጠዋት ከቦሌ ካርጎ እስከ አቃቂ ድልድይ በመሰራት ላይ የሚገኘውን የአረንጓዴ ልማት ስራ ተዘዋውረን ጎብኝተናል።
ከተማችንን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ ለማድረግ የጀመርነው የኮሪደር ልማት አካል የሆነው የአረንጓዴ ልማት ስራ የህጻናት መጫዎቻዎችን፣ መናፈሻዎችን እንዲሁም የተለያዩ ለአካባቢው ነዋሪዎች ግልጋሎት የሚሰጡ ስራዎችን የሚያካትት፣ ከ200 ሺሕ ካሬ በላይ ሽፋን ያለው እና ከቦሌ ካርጎ እስከ አቃቂ ድልድይ ድረስ 9.5 ኪ ሜ የሚረዝም ሲሆን ስራውን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለህዝብ ክፍት እናደርጋለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
ዛሬ ጠዋት ከቦሌ ካርጎ እስከ አቃቂ ድልድይ በመሰራት ላይ የሚገኘውን የአረንጓዴ ልማት ስራ ተዘዋውረን ጎብኝተናል።
ከተማችንን ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ ለማድረግ የጀመርነው የኮሪደር ልማት አካል የሆነው የአረንጓዴ ልማት ስራ የህጻናት መጫዎቻዎችን፣ መናፈሻዎችን እንዲሁም የተለያዩ ለአካባቢው ነዋሪዎች ግልጋሎት የሚሰጡ ስራዎችን የሚያካትት፣ ከ200 ሺሕ ካሬ በላይ ሽፋን ያለው እና ከቦሌ ካርጎ እስከ አቃቂ ድልድይ ድረስ 9.5 ኪ ሜ የሚረዝም ሲሆን ስራውን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለህዝብ ክፍት እናደርጋለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
"በመዲናዋ የቅርስ መስፈርት የማያሟሉ ቤቶችንና አካባቢዎችን በመልሶ ማልማት የቀደመ ስያሜያቸው እንዲቀጥል ይደረጋል"
- የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን
****
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት የቅርስ መስፈርት የማያሟሉ ቤቶችንና አካባቢዎችን በመልሶ ማልማት የቀደመ ስያሜና አገልግሎታቸው እንዲቀጥል እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አሰታወቀ።
የሀገር ሃብትና ቅርሶችን የመጠበቅ የመንከባከብና የመጠገን ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጿል።
በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ሥራ ቅርሶችና መሰረተ ልማቶችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማደስ ሥራ በማከናወን በነበሩበት እንዲቀጥሉ መደረጉን የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መግለፃቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት የኢትዮጵያን ሃብትና ቅርሶች በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በመጠገን ለትውልድ እንዲተላለፉ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።
የቅርስ ጥበቃና መስህቦችን የማስፋት ስራ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተከናወነ ሲሆን በአዲስ አበባም ቅርሶችን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የመጠገን ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በመዲናዋ የአራዳ፣ ጉለሌ፣ ቂርቆስ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች የአዲስ አበባ ቀደምት የምስረታ አካል በመሆናቸው የኪነ-ሕንፃና መልክዓ ከተማነትን የሚያሳዩ መታሰቢያዎች መኖራቸውን አንስተዋል።
ከዚህ ቀደም በመዲናዋ የቅርስ መስፈርቶችን ያላሟሉ ሁሉ የተመዘገቡ መኖራቸውን አስታውሰው ዓለም አቀፍ የቅርስ ምዝገባ ተሞክሮን መነሻ በማድረግ በተዘጋጀ መመሪያ መሰረት በአዲስ መልክ የቅርስ ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚሁ መሰረት ከዚህ በፊት የተመዘገቡ በቅርስነት የሚቀጥሉ ሲኖሩ በመመሪያው መሰረት መስፈርቱን የማያሟሉ ደግሞ አይቀጥሉም ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም በአዲስ አበባ የመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት መጠበቅ ያለባቸው ቅርሶች እንዲጠበቁ መደረጉን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተለያዩ አካባቢዎች ከማህበራዊ ትውስታ፣ ዘመናዊነትና መዝናኛነት ጋር በተገናኘ የቆዩ ቤቶች ሁሉ ቅርስ ሊሆኑ አይችሉም ብለዋል።
ከዚህ ቀደም መርካቶ የቃኘው ሻለቃ ሆቴል፣ ቤላ የነጋድራስ ገብረህይወት ባይከዳኝ ቤትና ፒያሳ የአድዋ ሆቴል የቅርስነት መስፈርት ሳያሟሉ ተመዝግበው እንደነበርም አስታውሰዋል።
በመሆኑም በመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት ቅርሶች ተለይተው በቅርስ ምዝገባ መስፈርት ተመዝግበው እንዲጠበቁ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በየትኛውም ዓለም ልማትና ቅርስ ጥበቃ ሚዛኑን ጠብቆ እንደሚጓዝ ጠቁመው ቅርስ ጥበቃና ልማትን ማጣጣም ግዴታ ነው ሲሉም ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አስረድተዋል።
በመሆኑም የቅርስ ጥበቃና የልማት ስራዎች ተመጋግበው እንዲሄዱ በማድረግ የቅርስ መስፈርት የማያሟሉ ቤቶችንና አካባቢዎችን በመልሶ ልማት የቀደመ ስያሜና አገልግሎታቸው እንዲቀጥል ይደረጋል።
በኮሪደር ልማት ሥራው ቅርሶችና መሰረተ ልማቶችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማደስ ሥራ በማከናወን በነበሩበት እንዲቀጥሉ መደረጉን ከንቲባዋ መናገራቸው ይታወሳል።
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
- የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን
****
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት የቅርስ መስፈርት የማያሟሉ ቤቶችንና አካባቢዎችን በመልሶ ማልማት የቀደመ ስያሜና አገልግሎታቸው እንዲቀጥል እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አሰታወቀ።
የሀገር ሃብትና ቅርሶችን የመጠበቅ የመንከባከብና የመጠገን ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጿል።
በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ሥራ ቅርሶችና መሰረተ ልማቶችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማደስ ሥራ በማከናወን በነበሩበት እንዲቀጥሉ መደረጉን የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መግለፃቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት የኢትዮጵያን ሃብትና ቅርሶች በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በመጠገን ለትውልድ እንዲተላለፉ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።
የቅርስ ጥበቃና መስህቦችን የማስፋት ስራ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች እየተከናወነ ሲሆን በአዲስ አበባም ቅርሶችን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የመጠገን ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በመዲናዋ የአራዳ፣ ጉለሌ፣ ቂርቆስ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች የአዲስ አበባ ቀደምት የምስረታ አካል በመሆናቸው የኪነ-ሕንፃና መልክዓ ከተማነትን የሚያሳዩ መታሰቢያዎች መኖራቸውን አንስተዋል።
ከዚህ ቀደም በመዲናዋ የቅርስ መስፈርቶችን ያላሟሉ ሁሉ የተመዘገቡ መኖራቸውን አስታውሰው ዓለም አቀፍ የቅርስ ምዝገባ ተሞክሮን መነሻ በማድረግ በተዘጋጀ መመሪያ መሰረት በአዲስ መልክ የቅርስ ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚሁ መሰረት ከዚህ በፊት የተመዘገቡ በቅርስነት የሚቀጥሉ ሲኖሩ በመመሪያው መሰረት መስፈርቱን የማያሟሉ ደግሞ አይቀጥሉም ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም በአዲስ አበባ የመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት መጠበቅ ያለባቸው ቅርሶች እንዲጠበቁ መደረጉን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተለያዩ አካባቢዎች ከማህበራዊ ትውስታ፣ ዘመናዊነትና መዝናኛነት ጋር በተገናኘ የቆዩ ቤቶች ሁሉ ቅርስ ሊሆኑ አይችሉም ብለዋል።
ከዚህ ቀደም መርካቶ የቃኘው ሻለቃ ሆቴል፣ ቤላ የነጋድራስ ገብረህይወት ባይከዳኝ ቤትና ፒያሳ የአድዋ ሆቴል የቅርስነት መስፈርት ሳያሟሉ ተመዝግበው እንደነበርም አስታውሰዋል።
በመሆኑም በመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት ቅርሶች ተለይተው በቅርስ ምዝገባ መስፈርት ተመዝግበው እንዲጠበቁ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በየትኛውም ዓለም ልማትና ቅርስ ጥበቃ ሚዛኑን ጠብቆ እንደሚጓዝ ጠቁመው ቅርስ ጥበቃና ልማትን ማጣጣም ግዴታ ነው ሲሉም ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አስረድተዋል።
በመሆኑም የቅርስ ጥበቃና የልማት ስራዎች ተመጋግበው እንዲሄዱ በማድረግ የቅርስ መስፈርት የማያሟሉ ቤቶችንና አካባቢዎችን በመልሶ ልማት የቀደመ ስያሜና አገልግሎታቸው እንዲቀጥል ይደረጋል።
በኮሪደር ልማት ሥራው ቅርሶችና መሰረተ ልማቶችን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና የማደስ ሥራ በማከናወን በነበሩበት እንዲቀጥሉ መደረጉን ከንቲባዋ መናገራቸው ይታወሳል።
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮ ቴሌኮም ኩባንያን ጎበኙ
******
(ኢ ፕ ድ)
በቅርቡ የኢትዮ ቴሌኮም የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተሰየሙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከቦርዱ አባላት ጋር በኩባንያው የተለያዩ የቦታዎች ላይ ጉብኝት አድርገዋል።
ጉብኝታቸውም በአድዋ የድል መታሰቢያ በሚገኘው የኩባንያው ኤክስፒሪየንስ ማዕከል በመጀመር በፕሪሚየም አገልግሎት ማዕከል፣ ሞጁላር ዳታ ሴንተር እና የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የኮኔክቲቪቲ ተደራሽነትና ጥራት ከማሻሻል ባሻገር የዲጂታል ሶሉሽኖችንና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ የህዝቡን ህይወት ለማቅለል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ በጉብኝቱ ተገልጿል፡፡
በቴሌኮም እና በዲጂታል መሠረተ ልማት አቅም የተፈጠረውን አስቻይ ሁኔታ በመጠቀም የመንግስት ተቋማት አሰራሮቻቸውን በማዘመን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት ማቅረብ እንዲችሉ የተገነቡ የዲጂታል አቅሞችን እንዲያውቁትና እንዲጠቀሙበት ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ ዕውን ለማድረግ እያደረገ ያለውን ጥረት እና አስተዋጽኦ በማድነቅ ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቦርዱ ተገቢውን ድጋፍ እና አመራር እንደሚሰጥ መገለፁን ከኢትዮ ቴሌኮም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
******
(ኢ ፕ ድ)
በቅርቡ የኢትዮ ቴሌኮም የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተሰየሙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከቦርዱ አባላት ጋር በኩባንያው የተለያዩ የቦታዎች ላይ ጉብኝት አድርገዋል።
ጉብኝታቸውም በአድዋ የድል መታሰቢያ በሚገኘው የኩባንያው ኤክስፒሪየንስ ማዕከል በመጀመር በፕሪሚየም አገልግሎት ማዕከል፣ ሞጁላር ዳታ ሴንተር እና የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ተመልክተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የኮኔክቲቪቲ ተደራሽነትና ጥራት ከማሻሻል ባሻገር የዲጂታል ሶሉሽኖችንና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ የህዝቡን ህይወት ለማቅለል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ በጉብኝቱ ተገልጿል፡፡
በቴሌኮም እና በዲጂታል መሠረተ ልማት አቅም የተፈጠረውን አስቻይ ሁኔታ በመጠቀም የመንግስት ተቋማት አሰራሮቻቸውን በማዘመን ፈጣን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት ማቅረብ እንዲችሉ የተገነቡ የዲጂታል አቅሞችን እንዲያውቁትና እንዲጠቀሙበት ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ ዕውን ለማድረግ እያደረገ ያለውን ጥረት እና አስተዋጽኦ በማድነቅ ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቦርዱ ተገቢውን ድጋፍ እና አመራር እንደሚሰጥ መገለፁን ከኢትዮ ቴሌኮም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም
ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ
*****
(ኢ ፕ ድ)
ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
በአዲስ አበባ የተጀመረው የልማት ኮሪደር አላማና አሁን ያለበት ደረጃ ለተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮቹ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ ለቀጣይ ትውልድ ቋሚ ቅርስ በሚሆን መልኩ መገንባቱ እንዳስደሰታቸው በጉብኝቱ ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ የጋራ ታሪካችንን በልኩ ሰንዶ የያዘ፣ አንድነታችንን የሚያጸና ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንና የልማት ኮሪደር አላማ ከተማዋን ማስዋብ መሆኑን መረዳታቸውን ተናግረዋል።
ከልማት ተነሺዎች የሚነሳ ቅሬታ ከፍተኛ አመራሩ አዳምጦ መመለሱን አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል።
በጉብኝቱ ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ገዢው ፓርቲ የሰራቸውን የልማት ስራዎች በማየት እውነታውን መመስከር በፖለቲካ ስርዓታችን ውስጥ አዲስ ባህል በመሆኑ ይህ አዲስ አስተሳሰብና ተግባር ሊዳብር መግለፃቸውን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።
በአዲስ አበባ የተጀመረው የልማት ኮሪደር አላማና አሁን ያለበት ደረጃ ለተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮቹ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ ለቀጣይ ትውልድ ቋሚ ቅርስ በሚሆን መልኩ መገንባቱ እንዳስደሰታቸው በጉብኝቱ ገልጸዋል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ የጋራ ታሪካችንን በልኩ ሰንዶ የያዘ፣ አንድነታችንን የሚያጸና ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንና የልማት ኮሪደር አላማ ከተማዋን ማስዋብ መሆኑን መረዳታቸውን ተናግረዋል።
ከልማት ተነሺዎች የሚነሳ ቅሬታ ከፍተኛ አመራሩ አዳምጦ መመለሱን አሁንም አጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል።
በጉብኝቱ ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ገዢው ፓርቲ የሰራቸውን የልማት ስራዎች በማየት እውነታውን መመስከር በፖለቲካ ስርዓታችን ውስጥ አዲስ ባህል በመሆኑ ይህ አዲስ አስተሳሰብና ተግባር ሊዳብር መግለፃቸውን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓም