Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሲንጋፖር ሪፐብሊክ በኢስታና ቤተመንግስት በነበራቸው ቆይታ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በሁለትዮሽ ምክክር ላይ የመግባቢያ ስምምነት ብሎም በኢፌዲሪ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሲንጋፖር የትራንስፖርት ሚኒስቴር መካከል የፍላጎት ስምምነት ተፈርሟል።

ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
በውኃ ሀብት ተጠቃሚዎች የሚነሱ ግጭቶችንና የውኃ ብክነትን ለማስቀረት እየተሰራ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
በውሀ ሀብት ተጠቃሚዎች የሚነሱ ግጭቶችንና የውሀ ብክነትን ለማስቀረት እየተሰራ እንደሚገኝ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የዋቢ ሸበሌ፣ የገናሌ ዳዋና የኦሞ ግቢ ተፋሰሶች እቅድ የማጽደቅና የተፋሰስ ተጋሪ ክልሎች ፎረም ምስረታ መርሐግብር እየተካሄደ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዴኤታ አብርሃ አዱኛ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የውሃ ሀብት አስተዳደርን በማስፈን ተፋሰሶችን ከጉዳትና ብክለት ተጠብቀው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላይ እንዲውሉ በእቅድ መመራት እንዳለባቸው በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በውሀ ሀብት የሚነሱ ግጭቶችን ለመፍታትና የውሀ በክነትንና ብክለትን ለማስቀረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ የውሀ ሀብትን ከብክለትና ከአደጋ መከላከል የሚያስችል ቴክኒካል ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ኢትዮጽያ በቂ የዝናብ መጠን፣ በርካታ ወንዞች፣ ሀይቆች እና የተለያዩ የውሃ ሀብት ቢኖራትም ከህዝብ ብዛት መጨመርና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ማድረግ አልተቻለም ሲሉ ተናግረዋል።

ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የውሃ ሀብትን በፍትሀዊነት ተጠቃሚ መሆን እንዲችሉ የተናበበና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ እቅድ ሊኖር ይገባል ያሉት ዶክተር አብርሀም፤ በዚህም መሰረት የዋቢ ሸበሌ፣ የገናሌ ዳዋና የኦሞ ግቢ ተፋሰሶችን እቅድ በማውጣት ለማስጸደቅ መድረክ ተዘጋጅቷል ብለዋል።

የአባይ፣ የአዋሽ፣ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች እና ዛሬ የሚመሰረተውን የዋቢ ሸበሌ፣ የገናሌ ዳዋና የኦሞ ግቢ የተፋሰስ ተጋሪ ፎረም ጨምሮ በሀገሪቱ ስድስት የውሃ ሀብት ፎረሞች ይኖራሉ ብለዋል።

በመርሐግብሩ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፌደራል ተቋማት፣ ከስድቱ ክልሎች የተውጣጡ አመራሮች ተገኝተዋል።

በሄለን ወንድምነው
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
በልማት ኮርደር ስራ ከለሙ አካባቢዎች ከቴዎድሮስ አደባባይ እስከ መሃሙድ ሙዚቃ ቤት ያለው አሁናዊ ገጽታ‼️
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሲንጋፖር በብሔራዊው የእፅዋት ማዕከል ባህላዊውን እፅዋት የመሰየም ሥነሥርዓት ተካፍለዋል፤ 'አራንዳ ዐቢይ አሕመድ ዝናሽ ታያቸው' የተሰኘ የኦርኪድ አበባ በስማቸው ተሰይሞላቸዋል። ይህንን ስነስርዓት በፎት‼️

ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም