Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ ጥገናው ተጠናቆ ዛሬ መደበኛ ሥራውን ይጀምራል
******
(ኢ ፕ ድ )

ለአራት ዓመታት አገልግሎቱ ተቋርጦ የቆየው የአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ (ኤርፖርት) ጥገናው ተጠናቆ ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ.ም መደበኛ ሥራውን እንደሚጀምር የአክሱም ከተማ ከንቲባ አቶ አበበ ብርሃነ አስታወቁ፡፡

የከተማዋ ከንቲባ አቶ አበበ ብርሃነ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳሉት፤ የአፄ ዮሐንስ አራተኛ የአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ በሰሜኑ ጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ደርሶበታል ፡፡ ይህን ጉዳት ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት በፌዴራል መንግሥት እና በአጋር አካላት ዕቅድ ተይዞ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡

የአክሱም ኤርፖርት ለከተማዋ ገቢ፣ ቱሪዝምና ንግድ እንቅስቃሴ የጀርባ አጥንት መሆኑን ገልጸው፤ ኤርፖርቱ ለአራት ዓመታት ሥራውን በማቆሙ ምክንያት ለከተማዋ ከባድ ማህበራዊ ቀውስ ፈጥሮ እንደቆየ አውስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ማረፊያው ታህሳስ ወር 2016 ዓ.ም የጀመረው የጥገና ሥራ በፍጥነት ተጠግኖ ወደ ሥራ እንዲገባ ባደረገው ጥረት በተያዘለት ጊዜ ሥራው ተጠናቆ ዛሬ ሰኔ 02 ቀን.....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129557
በሜዲካል ኮሌጁ ለ400 ታካሚዎች የሥነ ልሳን ህክምና ተሰጠ
***
(ኢ ፕ ድ)

ለ400 ታካዎች የሥነ ልሳን ህክምና መስጠቱን የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አስታወቀ፡፡

በሆስፒታሉ የሥነ ልሳን ህክምና ባለሙያ ዶ/ር አካሉ አሰፋ፣ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት ሆስፒታሉ ባለፉት 11 ወራት ለ400 ህጻናትና አዋቂ ታካሚዎች የሥነ ልሳን ህክምና (Speech Therapy) ሰጥቷል፡፡

ህክምና ያገኙ ታካሚዎች ቁጥር ካለው የባለሙያ ቁጥር አንጻር ትንሽ የሚባል ባይሆንም፣ ህክምናውን ማግኘት ካለባቸው ታካሚዎች አንጻር ግን አነስተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

ህክምናው አጭር በሆነ የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚሰጥ አለመሆኑ ከሌሎች የህክምና ሂደቶች የተለየ እንደሚያደርገው ያነሱት ዶ/ር አካሉ፤ የሥነ ልሳን ህክምና ለውጡ በጊዜ ሂደት ውስጥ የሚገኝ በመሆኑ ታካሚዎች ረዘም ላለ ጊዜ ህክምናቸውን እንደሚከታተሉ ገልጸዋል፡፡

በሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት ውጤታማ ነው በማለት የገለጹት ዶ/ሩ፣ ታካሚዎች በተሻለ ፍጥነት ለውጥ ለውጥ ማምጣት እንዲችሉ የቤተሰብ ክትትል ወሳኝ መሆኑን......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129558
በአቪዬሽን ሳይንስና በኤሮስፔስ ኢንጅነሪግ ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ
*******
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ፣የኢትዮጵያ አየር ሃይል ፣የጅማ ዩኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በአቪዬሽን ሳይንስና በኤሮስፔስ ኢንጅነሪግ ዘርፍ አብረው በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል ።

ስምምነቱ የቴክኖሎጅ ልህቀት ማሳደግ በሚችሉ የአቪዬሽን ሳይንስና የኤሮስፔስ ኢንጅነሪግ ዘርፍ የሚጠይቀውን የሰለጠነ የሰው ሃይል በጋራ ለማፍራት ያለመ ነው።

ብቁና የሰለጠነ የሰው ሃይል ይዞ እየሰራ የሚገኘው የጅማ ዩኒቨርሲቲ እንደሆነም በስምምነቱ ላይ ተጠቅሷል።

ከሁሉም ተቋሞች የተወጣጣ አስራ ሁለት አባላትን ያካተተ ቴክኒካል ኮሚቴ ተመርጧል። ስምምነቱን ተግባራዊነት እየመራና የአፈፃፀም ሂደቱን እየተከታተለ ለተቋማቱ የበላይ ጠባቂዎች የሚያሳውቅ እንደሆነ ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ተቋምን የሚያሻግርና ትውልድን የሚጠቅም መሠረት ያለው የቴክኖሎጅ ልህቀት የሚሸጋገርበት ተቋም ለመገንባት በስምምነቱ ኃላፊነት የተጣለባቸው አካላት ዘመኑን የዋጄ ታሪክ ሰርተው ለትውልድ እንዲያስረክቡ ተጠይቋል።

ሰኔ 02 ቀን 2016 ዓ.ም 
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️

ዛሬ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ አቡነ ማትያስ ጋር በመሆን በኮሪደር ልማት ምክንያት በፈረሱ ቤቶች ምትክ በቤተክርስቲያኒቱ የሚገነባ ህንፃ የመሠረተ ድንጋይ አስቀምጠናል።

ቤተ ክህነት የከተማውን ልማት ሥራ በላቀ ሁኔታ በመደገፍ እና ለኮሪደር ልማት ስራዎች መጀመር፤ በማፍረስ ሂደትም ሆነ መልሶ በመገንባት ሂደት እንዲሁም ህንፃዎችን በማደስ ላደረገችው ተሳትፎ እና ተግባራዊ የሆነ ምላሽ ከልቤ ለማመስገን እወዳለሁ።
በዚህ አጋጣሚ ከቤተክርስቲያንቱ ለቀረበልኝ ምስጋናም እጅግ በጣም አድርጌ አመሰግናለሁ ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿን ይባርክ

ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ካላቸው የእስያ ሀገራት ምን ትቀስማለች?
***
(ኢ ፕ ድ)

ሀገራት እንደሚከተሉት ፖሊሲ እና ስተራቴጂ የኢኮኖሚ እድገት ደረጃቸው ይለያያል፡፡ የሀገራት የማያቋርጥ ተከታታይ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ሀገራቱ በኢኮኖሚ ራሳቸውን የቻሉ እንዲሆኑ ከማድረጉም በላይ ለዜጎች ምቹ ሀገር ከመፍጠር አኳያ ትልቅ ድርሻ እንዳለው የዘርፉ ምሁራን ይገልጻሉ፡፡

ከእስያ ሀገራት መካከል በተለይ አራት ሀገራት ተከታታይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በማስመዝገብ “እስያ ታይገርስ” የሚል ስያሜ በማግኘት ይታወቃሉ፡፡ ሀገራቱ ሆንግ ኮንግ፣ ሲንጋፖር (ቻይና) ፣ታይዋን እና ደቡብ ኮሪያ ናቸው፡፡

ሀገራቱ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ የጀመሩት እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ከ1960 ጀምሮ ሲሆን ከዚያ በፊት ኋላቀርና ኢኮኖሚያቸውም እዚህ ግባ የሚባል እንዳልሆነ ታሪካቸው ያስረዳል፡፡

እነዚህ ሀገራት በፖሊሲያቸው ያላቸውን እና የሌላቸውን ሀብት በመለየት የወጪ ንግድን መሠረት ያደረገ የኢንዱስትሪ አብዮት አካሂደዋል፡፡ የትምህርት ጥራት ላይ እንዲሁም ለቴክኖሎጂ እድገት ትኩረት ሰጥተው ሠርተዋል፡፡ በዚህም የማያቋርጥ እድገት እያስመዘገቡ በመቀጠል እንደ ኢትዮጵያ ላሉ በማደግ ላሉ ሀገራት ጥሩ አርአያ መሆን መቻላቸውን.....

https://press.et/?p=129624
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️

የቀደሙትን የኮሪደር ልማት ስራዎች ግምገማ ስናጠናቅቅ ቀጣዩን ግምገማችንን በስራው ስፍራ ተገኝተን እንደምናካሂድ ቃል ገብተን ነበር። የፒያሳ እና የአራት ኪሎ መስመር ስራ በተያዘው የሶስት ወር መርሃግብር ማጠናቀቃችንን ስገልፅ ደስታ ይሰማኛል።

በቀጣይ ስራ ሀብት ቁጠባ ቀዳሚ ትኩረት ሆኖ በቀሪ ኮሪደሮች ስራዎቻችን ፈጣን እና ፈጠራ መር ልንሆን ይገባል። ጥራትን ማስጠበቅ እና ለዜጎቻችን ሁሉ የተመቸ ከባቢን መፍጠር ቅድሚያ የምንሰጣቸው ተግባራት ናቸው።

ይህ ፕሮጀክት የሚራመደው በብዙሃን ትብብር ነው። ከጅማሮው በስራችን ባገኘነው በጎፈቃድ ምስጋና አቀርባለሁ። ይህም በእቅድ እና አፈፃፀም ላይ የታየውን ጥረታችንን እና መልካም ፈቃዳችንን የመጠነ ሆኖ ታይቷል።

በዚህ ከተማችንን ለተሻለ ለውጥ ለማብቃት በተደከመበት ታላቅ ስራ ሂደት ውስጥ በዜጎቻችን ላይ ፈጥረነው ሊሆን ለሚችል አለመመቸት ይቅርታ እንጠይቃለን። ኢትዮጵያችን እንድትለወጥ በፅናት እንደምንሰራ በዚህ የኮሪደር ልማት ስራ ሂደትም ያሉ የዲዛይን እና የጥራት ክፍተቶችም ካሉ ማስተካከል እንደምንቀጥል እንድትተማመኑ ለመግለፅ እፈልጋለሁ።

በግሉ ዘርፍ ያሉ አጋሮቻችንን ጨምሮ ትናንት ምሽት በጎዳናዎች ፍቅራችሁን ለገለፃችሁልን፤ በአጠቃላይም በዚህ ስራ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓም