“ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና”
#ጽዱኢትዮጵያ #CleanEthiopia
ለ #ጽዱኢትዮጵያ ንቅናቄ ጥሪ ስናቀርብ ዜጎቻችን በከፍተኛ ተነሳሽነት በሥራው ተሳትፈዋል። ዋናው አላማችን አካባቢያችንን ሳቢ በማድረግ መፀዳጃ ቤት የመጠቀም ባህላችንን ከመሠረቱ ማዳበር ነበር።
ዛሬ በዜጎቻችን በዋጋ የማይተመን የልብ መዋጮና እምነት የተገነቡትን ሥራዎች በቦታው በመገኘት ገምግመናል።
ከፍተኛ ጥራት ባላቸው ጠንካራና ዘመን ተሻጋሪ በሆኑ ቁሶች በመጠቀም ደረጃቸውን የጠበቁ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ለመገንባት ቁርጠኝነት ይዘናል።
ይህ የሥራው መጀመሪያ ነው። በእናንተ ያላሰለሰ ድጋፍ የጀመርናቸውን ሥራዎች እናስፋፋለን።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ጽዱኢትዮጵያ #CleanEthiopia
ለ #ጽዱኢትዮጵያ ንቅናቄ ጥሪ ስናቀርብ ዜጎቻችን በከፍተኛ ተነሳሽነት በሥራው ተሳትፈዋል። ዋናው አላማችን አካባቢያችንን ሳቢ በማድረግ መፀዳጃ ቤት የመጠቀም ባህላችንን ከመሠረቱ ማዳበር ነበር።
ዛሬ በዜጎቻችን በዋጋ የማይተመን የልብ መዋጮና እምነት የተገነቡትን ሥራዎች በቦታው በመገኘት ገምግመናል።
ከፍተኛ ጥራት ባላቸው ጠንካራና ዘመን ተሻጋሪ በሆኑ ቁሶች በመጠቀም ደረጃቸውን የጠበቁ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ለመገንባት ቁርጠኝነት ይዘናል።
ይህ የሥራው መጀመሪያ ነው። በእናንተ ያላሰለሰ ድጋፍ የጀመርናቸውን ሥራዎች እናስፋፋለን።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት በቴሌኮም ዘርፍ‼️
👉 4G አገልግሎት ተጠቃሚ ከተሞች 424 ደርሰዋል
👉 462 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች ተገንብተዋል
👉 132 የገጠር የሞባይል ጣቢያዎች ከ2G ወደ 3G አገልግሎት አድገዋል፣
👉 4G አገልግሎት 34 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል፣
👉 በአምስት ከተሞች 5G አገልግሎት ተደራሽ ተደርጓል፣
👉 የሞባይል ኔትወርክ ያልነበራቸውን 216 የገጠር ቀበሌዎች በኔትወርክ ተሳስረዋል፣
👉 የሞባይል ኔትወርክ ተደራሽነት 85 ነጥብ 4፤ በተጠቃሚዎች ከ99 በመቶ በላይ ደርሷል፣
👉 93 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስቧል፣
👉 21 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ አግኝቷል፣
👉 የደንበኞቹን ቁጥር ከ78 ሚሊዮን በላይ አድርሷል
👉 በቴሌ ብር ከአንድ ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር በላይ አገበያይቷል
👉 የቴሌብር ደንበኞት ቁጥርም 47 ነጥብ 55 ሚሊዮን፣
👉 86 ሚሊዮን ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል የሞባይል ኔትወርክ ተገንብቷል፣
👉 በዓለም አቀፍ ከሚገኙ 778 የቴሌኮም ኦፕሬተሮች 17ኛ፣ በአፍሪካ ከ195 የቴሌኮም ኦፕሬተሮች 2ኛ ደረጃን ይዟል፣
ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131808
👉 4G አገልግሎት ተጠቃሚ ከተሞች 424 ደርሰዋል
👉 462 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች ተገንብተዋል
👉 132 የገጠር የሞባይል ጣቢያዎች ከ2G ወደ 3G አገልግሎት አድገዋል፣
👉 4G አገልግሎት 34 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል፣
👉 በአምስት ከተሞች 5G አገልግሎት ተደራሽ ተደርጓል፣
👉 የሞባይል ኔትወርክ ያልነበራቸውን 216 የገጠር ቀበሌዎች በኔትወርክ ተሳስረዋል፣
👉 የሞባይል ኔትወርክ ተደራሽነት 85 ነጥብ 4፤ በተጠቃሚዎች ከ99 በመቶ በላይ ደርሷል፣
👉 93 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስቧል፣
👉 21 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ አግኝቷል፣
👉 የደንበኞቹን ቁጥር ከ78 ሚሊዮን በላይ አድርሷል
👉 በቴሌ ብር ከአንድ ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር በላይ አገበያይቷል
👉 የቴሌብር ደንበኞት ቁጥርም 47 ነጥብ 55 ሚሊዮን፣
👉 86 ሚሊዮን ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል የሞባይል ኔትወርክ ተገንብቷል፣
👉 በዓለም አቀፍ ከሚገኙ 778 የቴሌኮም ኦፕሬተሮች 17ኛ፣ በአፍሪካ ከ195 የቴሌኮም ኦፕሬተሮች 2ኛ ደረጃን ይዟል፣
ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131808
ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር ሆና የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጸደቀች
******
(ኢ ፕ ድ)
ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በፓርላማ በማጽደቅ ስድስተኛ ሀገር ሆናለች፡፡ ከ11 የናይል ተፋሰስ ሀገራት መካከል ስድስት ሀገራት በፓርላማ ካጸደቁ ቋሚ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ኮሚሽን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ይችላል፡፡
በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ነቢል ማህዲ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በአባይ ተፋሰስ ሀገራት መካከል ከተፈረመ ቆይቷል፡፡ አምስት ሀገራት በፓርላማቸው አጽድቀው ነበር፡፡
የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን ለመመስረት የሚጠበቀው ስድስተኛ ሀገር በፓርላማ እስኪያጸድቅ ድረስ ነበር፤ ደቡብ ሱዳን አጸድቃለች ብለዋል፡፡
ስድስት ሀገራት የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ማጽደቃቸው ፋይዳው ከፍተኛ ነው ያሉት አምባሳደሩ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት በሙሉ በሰነዱ ይገዛሉ፡፡ በሐምሌ አንድ ቀን 2016 ዓ.ም የደቡብ ሱዳን በፓርላማ የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በማጽደቅ ስድስተኛ ሀገር ሆናለች፡፡
የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ለማጸደቅ ሂደቱ በጣም ከባድ ነበር ያሉት አምባሳደር ነቢል፤ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለፉት ሶስት አመታት ብዙ ትግል አድርጓል፡፡ የደቡብ ሱዳን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከአምስት አመት በፊት ያጸደቀው ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች መዘግየቱን ገልጸዋል፡፡
በፓርላማ ውስጥ የሚመለከታቸውን አካላት በማነጋገር የተገኘ ውጤት ነው፡፡ የደቡብ ሱዳን የሽግግር መንግስት በመሆኑ የሰላም ስምምነቱን የፈረሙ ፓርቲዎችን በሙሉ በማነጋገር የመጣ ነው ብለዋል፡፡ መፈረማቸው ለደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ገልጸዋል፡፡
ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር ሆና የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጽድቃለች ያሉት አምባሰደሩ፤ በቅርቡ የሀገሪቷ ፕሬዚዳንት ይፈርማሉ፡፡ በመቀጠልም ሰነዱን ለአፍሪካ ህብረት በመላክ ሕጋዊ ሰነድነቱ ይረጋገጣል፡፡
ከደቡብ ሱዳን በፊት የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ፈርመዋል፤ይሁንና ወሳኙ ስድስተኛ ሀገር መፈረም በመሆኑ ደቡብ ሱዳን መፈረሟ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ ጉዳዩን የኢትዮጵያ መንግስት የቅርብ ክትትል ያደረገበት በመሆኑ የተሳካ መሆን ችሏል፡፡
ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን መፈረሟ ለኢትዮጵያ ያላትን አጋርነት ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ነጻነት ከፍተኛ መስዋትነት ከፍላለች፡፡ ደቡብ ሱዳንም አጠቃላይ ለተፋሰሱ ሀገር በተለይ ለላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ያላትን አጋርነት ያረጋገጠችበት ነበር ብለዋል፡፡
ማእቀፉን ያጸደቁ ኢትዮጵያ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ዩጋዳንዳ፣ ብሩንዲና ደቡብ ሱዳን ናቸው፡፡
የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት እአአ 2006 የተዘጋጀ ሲሆን የናይል ተፋሰስ አገራት የውሃ ሀብቶችን በትብብር ማልማትና ማስተዳደር የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ያስቀመጠ ነው፡፡ የናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ (NBI) የሽግግር ማእቀፍ ሆኖ በዘጠኝ መስራች አባል ሀገራት የጋራ ራእይ የተመሰረተና ቋሚ የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን እስከሚመሰረት የሽሽግር ማእቀፍ ሆኖ እንዲያገልገል ታስቦ መቋቋሙ ይታወቃል።
በሞገስ ጸጋዬ
ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በፓርላማ በማጽደቅ ስድስተኛ ሀገር ሆናለች፡፡ ከ11 የናይል ተፋሰስ ሀገራት መካከል ስድስት ሀገራት በፓርላማ ካጸደቁ ቋሚ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ኮሚሽን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ይችላል፡፡
በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ነቢል ማህዲ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በአባይ ተፋሰስ ሀገራት መካከል ከተፈረመ ቆይቷል፡፡ አምስት ሀገራት በፓርላማቸው አጽድቀው ነበር፡፡
የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን ለመመስረት የሚጠበቀው ስድስተኛ ሀገር በፓርላማ እስኪያጸድቅ ድረስ ነበር፤ ደቡብ ሱዳን አጸድቃለች ብለዋል፡፡
ስድስት ሀገራት የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ማጽደቃቸው ፋይዳው ከፍተኛ ነው ያሉት አምባሳደሩ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት በሙሉ በሰነዱ ይገዛሉ፡፡ በሐምሌ አንድ ቀን 2016 ዓ.ም የደቡብ ሱዳን በፓርላማ የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በማጽደቅ ስድስተኛ ሀገር ሆናለች፡፡
የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ለማጸደቅ ሂደቱ በጣም ከባድ ነበር ያሉት አምባሳደር ነቢል፤ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለፉት ሶስት አመታት ብዙ ትግል አድርጓል፡፡ የደቡብ ሱዳን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከአምስት አመት በፊት ያጸደቀው ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች መዘግየቱን ገልጸዋል፡፡
በፓርላማ ውስጥ የሚመለከታቸውን አካላት በማነጋገር የተገኘ ውጤት ነው፡፡ የደቡብ ሱዳን የሽግግር መንግስት በመሆኑ የሰላም ስምምነቱን የፈረሙ ፓርቲዎችን በሙሉ በማነጋገር የመጣ ነው ብለዋል፡፡ መፈረማቸው ለደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ገልጸዋል፡፡
ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር ሆና የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጽድቃለች ያሉት አምባሰደሩ፤ በቅርቡ የሀገሪቷ ፕሬዚዳንት ይፈርማሉ፡፡ በመቀጠልም ሰነዱን ለአፍሪካ ህብረት በመላክ ሕጋዊ ሰነድነቱ ይረጋገጣል፡፡
ከደቡብ ሱዳን በፊት የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ፈርመዋል፤ይሁንና ወሳኙ ስድስተኛ ሀገር መፈረም በመሆኑ ደቡብ ሱዳን መፈረሟ ትልቅ ትርጉም አለው፡፡ ጉዳዩን የኢትዮጵያ መንግስት የቅርብ ክትትል ያደረገበት በመሆኑ የተሳካ መሆን ችሏል፡፡
ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን መፈረሟ ለኢትዮጵያ ያላትን አጋርነት ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ነጻነት ከፍተኛ መስዋትነት ከፍላለች፡፡ ደቡብ ሱዳንም አጠቃላይ ለተፋሰሱ ሀገር በተለይ ለላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ያላትን አጋርነት ያረጋገጠችበት ነበር ብለዋል፡፡
ማእቀፉን ያጸደቁ ኢትዮጵያ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ዩጋዳንዳ፣ ብሩንዲና ደቡብ ሱዳን ናቸው፡፡
የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት እአአ 2006 የተዘጋጀ ሲሆን የናይል ተፋሰስ አገራት የውሃ ሀብቶችን በትብብር ማልማትና ማስተዳደር የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ያስቀመጠ ነው፡፡ የናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ (NBI) የሽግግር ማእቀፍ ሆኖ በዘጠኝ መስራች አባል ሀገራት የጋራ ራእይ የተመሰረተና ቋሚ የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን እስከሚመሰረት የሽሽግር ማእቀፍ ሆኖ እንዲያገልገል ታስቦ መቋቋሙ ይታወቃል።
በሞገስ ጸጋዬ
ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቦሌ የኮሪደር ልማት ስራ አፈፃፀም ክትትል እና ድጋፍ እያደረጉ ያሉ አካላትን አመሰገኑ
****
(ኢ ፕ ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቦሌ የኮሪደር ልማት ስራ አፈፃፀም ክትትል እና ድጋፍ እያደረጉ ያሉ አካላትን አመሰገኑ።
የኮሪደር ልማት ስራዎቻችን ለከተማዋ ነዋሪ ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር የሚያስችሉ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ከዘመናዊነት ጋር የተቃኘ አሰራርን በመዘርጋትና በማሳለጥ የኢኮኖሚ እድገት ወሳኙን ሚና እንድንወጣ ያስቻለ መሆኑን ከንቲባዋ ገልጸዋል።
በሂደቱ በምታደርጉት ተሳትፎ በአዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ ውስጥ ታሪካዊ አሻራችሁን እያሳረፋችሁ መሆናችሁን ተረድታችሁ ስራውን በፍጥነት ብቻ ሳይሆን በጥራት እንድትሰሩ አበረታታችኋለሁ ብለዋል።
በታሪክ ሂደት የከተማዋን የሥራ ባህል በቀየርንበት ፤ ቀንና ለሊት በስራችሁበት ጎን ለሥራ ጥራት የምትሰጡት ትኩረት ባህል ሆኖ መቀጠል እንዲችል መስራት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በቦሌ ሳይት በምሽት በሥራ ላይ ለነበሩ ሰራተኞችን የእራት ግብዣ እያደረጉ ያሉትን የአካባቢውን ነዋሪዎች ምስጋናና ክብር ይገባቸዋል ማለታቸውን የከተማዋ ኮሙዩኒኬሽን ዘግቧል።
ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቦሌ የኮሪደር ልማት ስራ አፈፃፀም ክትትል እና ድጋፍ እያደረጉ ያሉ አካላትን አመሰገኑ።
የኮሪደር ልማት ስራዎቻችን ለከተማዋ ነዋሪ ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር የሚያስችሉ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ከዘመናዊነት ጋር የተቃኘ አሰራርን በመዘርጋትና በማሳለጥ የኢኮኖሚ እድገት ወሳኙን ሚና እንድንወጣ ያስቻለ መሆኑን ከንቲባዋ ገልጸዋል።
በሂደቱ በምታደርጉት ተሳትፎ በአዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ ውስጥ ታሪካዊ አሻራችሁን እያሳረፋችሁ መሆናችሁን ተረድታችሁ ስራውን በፍጥነት ብቻ ሳይሆን በጥራት እንድትሰሩ አበረታታችኋለሁ ብለዋል።
በታሪክ ሂደት የከተማዋን የሥራ ባህል በቀየርንበት ፤ ቀንና ለሊት በስራችሁበት ጎን ለሥራ ጥራት የምትሰጡት ትኩረት ባህል ሆኖ መቀጠል እንዲችል መስራት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በቦሌ ሳይት በምሽት በሥራ ላይ ለነበሩ ሰራተኞችን የእራት ግብዣ እያደረጉ ያሉትን የአካባቢውን ነዋሪዎች ምስጋናና ክብር ይገባቸዋል ማለታቸውን የከተማዋ ኮሙዩኒኬሽን ዘግቧል።
ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም
ሩሲያ በብሪክስ የትብብር ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ታጠናክራለች
*******
(ኢ ፕ ድ)
ሩሲያ በብሪክስ የትብብር ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ይበልጥ አጠናክራ ለመቀጠል እንደምትሰራ በኢትዮጵያ የሀገሪቱ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን ተናገሩ።
አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ ብሪክስን ከተቀላቀለች ጀምሮ በሚደረጉ ሁነቶች እያደረገች ያለው የነቃ ተሳትፎ የሚደነቅ ነው።
ሩሲያ የተያዘው የፈረንጆች ዓመት የብሪክስ ሊቀመንበር መሆኗን አስታውሰው፤ ጥምረቱን ማጠናከር የሚያስችሉ የተለያዩ ሁነቶችን እያካሄደች መሆኗን ጠቁመዋል።
ለአብነትም በቅርቡ የብሪክስ አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን ጨምሮ የሌሎች ተቋማት ተወካዮች በሩሲያ ሞስኮ ከተማ ስብሰባ መካሄዱን ገልፀዋል። በዚህም ስብሰባ ኢትዮጵያ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጓን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በሙያተኞችና ሚኒስትሮች ደረጃ የምታደርገው ተሳትፎ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ እንዲሁም ብሪክስን የሚያጠናክር መሆኑን ነው ያስረዱት።
ኢትዮጵያ በብሪክስ እያደረገች ያለው ተሳትፎ በትብብር ማዕቀፉ ለጋራ እድገት መረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ አምባሳደሩ ገለፃ፤ አባል ሀገራቱ በሚቀይሱት የትብብር አቅጣጫ መሠረት ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ የትብብር መስኮች አጋርነቷን ታጠናክራለች።
ኢትዮጵያ የብሪክስ የልማት ባንክ አባል ለመሆን የምታደርገውን ጥረት ሩሲያ እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2006 ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ሕንድና ቻይና "ብሪክ" ቡድን የፈጠሩ ሲሆን በ2010 ደቡብ አፍሪካ ቡድኑን በመቀላቀሏ "ብሪክስ" ወደሚለው ስያሜ መጥቷል።
ከዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት ጀምሮ ኢትዮጵያን ጨምሮ ግብጽ፣ ኢራን፣ ሳዑዲ አረቢያና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ይህንን በመስፋፋት ላይ ያለውን ጥምረት በይፋ ተቀላቅለዋል።
የብሪክስ አባል ሀገራት አሁን ላይ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን የሚሆነውን የዓለም ሕዝብ የሚይዙ ሲሆን፤ ይህም ከአጠቃላይ የዓለም ሕዝብ ቁጥር አንጻር 45 በመቶ ማለት ነው።
የሀገራቱ ምጣኔ ኃብት 28 ነጥብ 5 ትሪሊየን ዶላር የሚገመት ሲሆን፤ ይህም ከወቅታዊው የዓለም ምጣኔ ኃብት አንጻር ሲታይ 28 በመቶ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
ሩሲያ በብሪክስ የትብብር ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ይበልጥ አጠናክራ ለመቀጠል እንደምትሰራ በኢትዮጵያ የሀገሪቱ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን ተናገሩ።
አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ ብሪክስን ከተቀላቀለች ጀምሮ በሚደረጉ ሁነቶች እያደረገች ያለው የነቃ ተሳትፎ የሚደነቅ ነው።
ሩሲያ የተያዘው የፈረንጆች ዓመት የብሪክስ ሊቀመንበር መሆኗን አስታውሰው፤ ጥምረቱን ማጠናከር የሚያስችሉ የተለያዩ ሁነቶችን እያካሄደች መሆኗን ጠቁመዋል።
ለአብነትም በቅርቡ የብሪክስ አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን ጨምሮ የሌሎች ተቋማት ተወካዮች በሩሲያ ሞስኮ ከተማ ስብሰባ መካሄዱን ገልፀዋል። በዚህም ስብሰባ ኢትዮጵያ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጓን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በሙያተኞችና ሚኒስትሮች ደረጃ የምታደርገው ተሳትፎ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ እንዲሁም ብሪክስን የሚያጠናክር መሆኑን ነው ያስረዱት።
ኢትዮጵያ በብሪክስ እያደረገች ያለው ተሳትፎ በትብብር ማዕቀፉ ለጋራ እድገት መረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ አምባሳደሩ ገለፃ፤ አባል ሀገራቱ በሚቀይሱት የትብብር አቅጣጫ መሠረት ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ የትብብር መስኮች አጋርነቷን ታጠናክራለች።
ኢትዮጵያ የብሪክስ የልማት ባንክ አባል ለመሆን የምታደርገውን ጥረት ሩሲያ እንደምትደግፍም አረጋግጠዋል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2006 ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ሕንድና ቻይና "ብሪክ" ቡድን የፈጠሩ ሲሆን በ2010 ደቡብ አፍሪካ ቡድኑን በመቀላቀሏ "ብሪክስ" ወደሚለው ስያሜ መጥቷል።
ከዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት ጀምሮ ኢትዮጵያን ጨምሮ ግብጽ፣ ኢራን፣ ሳዑዲ አረቢያና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ይህንን በመስፋፋት ላይ ያለውን ጥምረት በይፋ ተቀላቅለዋል።
የብሪክስ አባል ሀገራት አሁን ላይ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን የሚሆነውን የዓለም ሕዝብ የሚይዙ ሲሆን፤ ይህም ከአጠቃላይ የዓለም ሕዝብ ቁጥር አንጻር 45 በመቶ ማለት ነው።
የሀገራቱ ምጣኔ ኃብት 28 ነጥብ 5 ትሪሊየን ዶላር የሚገመት ሲሆን፤ ይህም ከወቅታዊው የዓለም ምጣኔ ኃብት አንጻር ሲታይ 28 በመቶ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም