Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️

በዛሬው የምክር ቤታችን ውሎ ለ2017 በጀት ዓመት 230.39 ቢሊዮን ብር በጀት አውጀናል።
ከዚህ ውስጥ 146.48 ቢሊዮን ብር (63.6 በመቶ) ለካፒታል የተመደበ ሲሆን፣ 74.55 ቢሊዮን ብር (33.4 በመቶ) ለመደበኛ ወይም ለአስተዳደርዊ ወጪ የተመደበ ነው።

ለካፒታል ከተመደበው ውስጥ 90.4 በመቶ ለድህነት ቅነሳና እድገት ተኮር ዘላቂ ልማት ለሆኑ ፕሮጀክቶች የተመደበ ነው።

ውድ የከተማችን ግብር ከፋዮች፤ ይህን በጀት ማሳካት የጋራ ርብርብ ይጠይቃል።

በ2016 በጀት ዓመት ግብራችሁን በወቅቱ በፈቃደኝነት በመክፈላችሁ 146.8 ቢሊዮን ብር ግብር ሰብስበን 18,091 ፕሮጀክቶችንና የኮሪደር ልማትን ተግብረን ከተማችንን እንደ ስሟ ውብ አበባ በማድረግ የጋራ አሻራችንን እያስቀመጥን ነው።

በዚህ ዓመትም እጅ ለእጅ ተያይዘን የበለጠ ለመስራት ሁላችንም ሃላፊነታችንን እንድንወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህቦቿን ይባርክ
የቡና እና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ ስለቡና ግብይት በሰጡት ማብራሪያ‼️

👉በቡና ግብይት በላኪውና በአቅራቢው መካከል የሚፈጠሩ ችግሮች እንዲፈቱ እንሰራለን፣

👉 የግብይት ስርዓቱን ማሳጠር ብቻ ሳይሆን ከአንድ ኪሎ ቡና ዝቅተኛ ዋጋ ህዳግ ማስተካከል አስፈላጊ ነበር፣

👉 ኮሜርሻል የሚባሉት ደረጃ አራትና አምስት መጠናቸውን በመቀነስ ስፔሻሊቲ ቡና ላይ በመስራት በኒውዮርክ ገበያ ከብራዚል ቡና ጋር እኩል መወዳደር እንዲችል ማሻሻያ ተደርጓል፣

👉 የስፔሻሊቲ ቡናን ድርሻ ከፍ ለማድረግ በ2014 ዓ.ም የስፔሻሊቲ ቡናን ወደ 60 በመቶ ከፍ ማድረግ ተችሏል፣

👉 የኮሜርሻሉ ከ70 በመቶ ወደ 40 በመቶ እንዲወርድ ተደርጓል፣

👉 በ2014 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፣

👉 በልማቱ ዘርፍ ምርትና ምርታማቱ ላይ ያሉ ችግሮችን የመቅረፍ ስራ ተከናውኗል

👉 በ2017 ዓ.ም አንድ ነጥብ 8 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር እናገኛለን ብለን አቅደን እየሰራን ነው፣

👉 በቡና ግብይት ላይ አሁንም ፈተናዎች አሉ፤ ስርቆቱን መቶ በመቶ ቀርፈናል አንልም፤

👉 ሆኖም ግን ቴክኖሎጂ በማበልጸግ ቡና የት እንደሚደርስ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት ስርዓት ተፈጥሯል፣

👉 የቡና ግብይት መመሪያው የሚለው ቡና በተረካከቡ በሶስተኛው ቀን ቅሬታቸው ለባለስልጣኑ ማቅረብ ይችላሉ፣

👉 የቀጥታ ትስስር ግብይትና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አማራጭ ናቸው፣

👉 የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አልተዘጋም የቀጥታ ትስስር ግብይት አስገዳጅ ሳይሆን አማራጭ የገበያ ስርዓት ነው፣

👉 ለምሳሌ ምርት ገበያ ላይ በፈረሱላ አራት ሺ ብር ከሆነ የቀጥታ ትስስር እስከ አራት ሺ 200 ድረስ መገበያየትን ዕድል ይሰጣል፣
https://press.et/?p=132195
በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን በውይይት በዘላቂነት ለመፍታት ተስማምተናል
- የክልሎቹ ርዕሳነ መስተዳድሮች
*****
(ኢ ፕ ድ)

በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን በውይይት በዘላቂነት ለመፍታት ከስምምነት መደረሱን የየክልሎቹ ርዕሳነ መስተዳድሮች ገለጹ።

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በክልሎቹ አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን በውይይት በዘላቂነት ለመፍታት መስማማታቸውን በተመለከተ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚነሱ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ በዘላቂነት ለመፍታት የክልሎቹና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት መደረጉን ተናግረዋል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ በቀጣይም ለግጭቶች ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮችን በመለየት የጋራ መፍትሄ ለመስጠት ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።

ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓም
የአዲስ አበባ ከተማ ምክርቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ
****
(ኢ ፕ ድ)

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

1ኛ) ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና የአረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ

2ኛ) አቶ ያብባል አዲስ ጎበዜ -የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ

3ኛ) አቶ አንድነት ብዙሰው ታመነ- የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር

4ኛ) አቶ ቁሴ ለታ ዋቅጅራ- የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር

5ኛ) አቶ ማሾ ኦላና- የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ

6ኛ) ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ - የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

በማርቆስ በላይ

ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓም
“የምትተክል ሀገር፣ የሚያፀና ትውልድ”

የዘንድሮ የ#አረንጓዴዓሻራ ተካፋይ እንድትሆኑ ጥርዬን አቀርባለው

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የውድድር አድማሱ የሰፋው የባንክ ሥራ
*****
(ኢ ፕ ድ)

ባለፈው ሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመራው የባንክ ሥራ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት እንዲደረግ በመንግሥት የተላለፈውን የፖሊሲ ውሳኔ ወደ ተግባር ለማሸጋገር ያለመ ነው፡፡

ረቂቅ ማሻሻያ አዋጁ የውጭ አገር ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ ዕድል የሚፈጥር ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች ይሰነዘራሉ፡፡

አዋጁን ተከትሎ የውጭ ሀገር ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ሥራ ሲጀምሩ ለዜጎች ጥሩ የባንክ አማራጭ እንደሚሆኑ ብዙ የባንክ ሥራ ባለሙያዎች ይስማማሉ፡፡ አንዳንዶች ደግሞ የባንኮቹ መግባት የሀገር ውስጥ ባንኮችን ሕልውናን ሊፈታተን ይችላል ሲሉ በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ስጋት ይገልጻሉ፡፡

የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ መግባት በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይስማማሉ፡፡ የውጭ ባንኮቹ መግባት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ትልቅ ፋይዳ ቢኖረውም አዋጁን ተከትለው በሚወጡ መመሪያዎች.....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=132427
"የቀድሞው ደቡብ ክልል የጋራ ሀብት በሠላማዊና ፍትሐዊ መንገድ ተከፋፍሎ ተጠናቋል”
– አቶ ደስታ ሌዳሞ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
*****
(ኢ ፕ ድ)

የቀድሞው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የነበረው የጋራ ተንቀሳቃሽና ቋሚ ሀብት ሠላማዊና ፍትሐዊ በሆነ መንገገድ ተከፋፍሎ መጠናቀቁን የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳድሩ እንደተናገሩት፤ የቀድሞው የደቡብ ክልል አሁን ላይ ወደ አራት ክልል ተከፋፍሏል። ይህንን ተከትሎ የሀብት ክፍፍሉን በሠላማዊ መንገድ ለመቋጨት መረጃ ላይ የተመሠረተ ድርድርና ውይይት ሲደረግ ቆይቷል።

በቀድሞው ክልል የነበሩ የተንቀሳቃሽና ቋሚ ሀብት ክፍፍል በሠላማዊና ፍትሐዊ በሆነ መንገገድ ተከፋፍሎ ተጠናቋል ብለዋል።

የሀብት ክፍፍሉን በሠላማዊና ፍትሐዊ መንገድ ለመቋጨት መረጃ ላይ የተመሠረተ ድርድርና ውይይት ሲደረግ ቆይቷል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በመጨረሻም ኮሚቴ ተቋቁሞ የተንቀሳቃሽና የቋሚ ንብረቶች ክፍፍል መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን ሁሉም የየድርሻውን ማግኘቱን ጠቁመው፤ ጥቂት ቀሪ የተንጠባጠቡ ጉዳዮች ካሉ እየታየ በጋራ ውይይት እልባት ያገኛል ሲሉ አስረድተዋል።

ቋሚ ንብረትን ወይም ሕንፃን በሚመለከት ደቡብ ክልል፣ ክልል ከሆነ እና መቀመጫውን ሃዋሳ ከተማ ካደረገ በኋላ በሀዋሳ ከተማ በጋራ የተገነቡ ንብረቶች ማዕቀፍ ውስጥ ያሉ አሉ የሚሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ደስታ፤ በጋራ የተገነቡ ሕንፃዎች ተቆጥረው፤ “የቱ ወዴት ይሂድ?” የሚል ምክክር መደረጉን......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=132443
በሀረሪ ክልል ከ2 ቢሊዮን 253 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ
*****
(ኢ ፕ ድ)

በሀረሪ ክልል በ2016 የበጀት አመት ከ2 ቢሊዮን 253 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ሀላፊ ወ/ሮ ኢክራም አብዱልቃድር በክልሉ በ2016 የበጀት ከ2 ቢሊዮን 243 ሚሊዮን ለመሰብሰብ ታቅዶ 2 ቢሊዮን 253 ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል ብለዋል።

ከተሰበሰበው ገቢ 1 ቢሊዮን 285 ሚሊየን በላይ ከቀጥታ ታክስ፤ 542 ነጥብ 6 ሚሊዮን ቀጥታ ካልሆነ ታክስ፤ 64 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ታክስ ነክ ካልሆኑ ገቢዎች፣ 360 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።

ከግብር አሰባሰብ ጋር በተያያዘ የአገልግሎት አሰጣጥ ስራዎችን ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

በቀጣይም የክልሉ ገቢን ለማጎልበት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓም
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል 97 ነጥብ 5 በመቶው ፈተናውን ወስደዋል
******
(ኢ ፕ ድ)

በሀገር አቀፍ ደረጃ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል 97 ነጥብ 5 በመቶው ፈተናውን መውሰዳቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና መጠናቀቅን ተከትሎ በሰጡት መግለጫ በመላ ሀገሪቱ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡ 701 ሺህ 749 ተማሪዎች መካከል 97 ነጥብ 5 በመቶው ፈተናውን ወስደዋል ብለዋል።

ቀሪዎቹ በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን ዘግይተው በመጀመራቸው ፈተናውን እንዳልወሰዱም ገልጸዋል፡፡

የትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ጠዋት መጠናቀቁን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ፈተናው በመላ ሀገሪቱ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 29ሺህ 718 ተማሪዎች በበይነ መረብ የተፈተኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የበይነ መረብ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ መሰጠቱን ጠቅሰው፣ በቀጣይ ለሚሰጠው ፈተና የተሻለ ተሞክሮ የተገኘበት ነው ማለታቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመላክታል።

ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓም
የአየርላንድ በኢትዮጵያ የሚደረገውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት በተለያዩ ዘርፎች እንደምትደግፍ ገለፀች
******
(ኢ ፕ ድ)

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ከአየርላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የመከላከያ ሚኒስትር ከሆኑት ሚካኤል ማርቲንን ጋር በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የምክክር ሂደት በሚመለከት ውይይት አድርጓል፡፡

በውይይቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአየርላንድ የሰላም ግንባታ ሂደት ተሞክሮ ገልፀው፣ በሂደቱ የፓለቲካ ቁርጠኝነትና ብዘሀነትን የማስተናገድ ፈቃደኝነት ለሀገራዊ ምክክርና ለሰላም ግንባታ ሂደት የነበራቸውን ጉልህ ሚና አብራርተዋል፡፡

በሀገራቸው በተደረጉ የሰላም ግንባታ ሂደቶች ሴቶች ዋነኛ ተሳታፊ መደረጋቸው ሂደቱን ውጤታማ አድርጎታል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የሚደረገውን የሀገራዊ ምክክር ሂደት በተለያዩ ዘርፎች ለመደገፍ ያላትን ቁርጠኝነት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጻቸውን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል።

ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓ.ም