"ያሆዴ" ሠላምና አብሮነትን የሚያጸና በዓል ነው
- የሠላም አምባሳደር ቁፋ ጎቤ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
"ያሆዴ" ሠላምና አብሮነት የሚያጸና በዓል መሆኑን የሠላም አምባሳደር ቁፋ ጎቤ ገለጹ።
የ2017 ዓ.ም የሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓልን ለማክበር የኦሮሞ ብሔረሰብን ወክለው የተገኙት የሠላም አምባሳደር ቁፋ ጎቤ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት የያሆዴ በዓልን ለበርካታ ጊዜ ከብሔሩ ተዋላጆች ጋር ማክበራቸውን በመገልጽ በዓሉ የህዝቦችን ሠላምና አብሮነት ለማጽናት ከፍተኛ ሚና አለው።
በዓሉ የሀድያ ህዝብ ፈጣሪውን የሚያመሰግበት ቂምና ጥላቻን የሚያርቅበት በመሆኑ ልዩ ስሜት ይፈጥራል ብለዋል።
የአርሲ አባ ገዳ ገሪባ ገልገሎ በበኩላቸው፦ በዓሉን ለማከበር በመገኘታቸው መደሠታቸውን ገልጸው የብሔሩ ተዋላጆች የኢሬቻ በዓል ከኦሮሞ ብሔረሰብ ጋር እንዲያከብሩ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
የሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ መከበር ይጀምራል።
በአማን ረሺድ (ከሆሳዕና)
- የሠላም አምባሳደር ቁፋ ጎቤ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
"ያሆዴ" ሠላምና አብሮነት የሚያጸና በዓል መሆኑን የሠላም አምባሳደር ቁፋ ጎቤ ገለጹ።
የ2017 ዓ.ም የሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓልን ለማክበር የኦሮሞ ብሔረሰብን ወክለው የተገኙት የሠላም አምባሳደር ቁፋ ጎቤ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት የያሆዴ በዓልን ለበርካታ ጊዜ ከብሔሩ ተዋላጆች ጋር ማክበራቸውን በመገልጽ በዓሉ የህዝቦችን ሠላምና አብሮነት ለማጽናት ከፍተኛ ሚና አለው።
በዓሉ የሀድያ ህዝብ ፈጣሪውን የሚያመሰግበት ቂምና ጥላቻን የሚያርቅበት በመሆኑ ልዩ ስሜት ይፈጥራል ብለዋል።
የአርሲ አባ ገዳ ገሪባ ገልገሎ በበኩላቸው፦ በዓሉን ለማከበር በመገኘታቸው መደሠታቸውን ገልጸው የብሔሩ ተዋላጆች የኢሬቻ በዓል ከኦሮሞ ብሔረሰብ ጋር እንዲያከብሩ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
የሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ መከበር ይጀምራል።
በአማን ረሺድ (ከሆሳዕና)
ከሲዳማ ክልል ከ36 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ይቀርባል
******************
(ኢ ፕ ድ)
በምርት ዘመኑ ከ36 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን የሲዳማ ክልል ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።
ዘንድሮ ወደ ውጭ ከሚላከው የቡና ምርት 200 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ይገኛልም ተብሏል።
የክልሉ ቡና ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በክልሉ በ170 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ቡና በስፋት ይለማል።
የቡና ምርታማነት የሚጨምሩ ፓኬጆችን በአግባቡ መጠቀም በተቻለበት በ1 ሄክታር 11 ኩንታል የቡና ምርት ይገኛል ያሉት አቶ መስፍን፤ በዘንድሮው የምርት ዘመንም 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርት ለመሰብሰብ......
https://press.et/?p=137037
******************
(ኢ ፕ ድ)
በምርት ዘመኑ ከ36 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን የሲዳማ ክልል ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።
ዘንድሮ ወደ ውጭ ከሚላከው የቡና ምርት 200 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ይገኛልም ተብሏል።
የክልሉ ቡና ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በክልሉ በ170 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ቡና በስፋት ይለማል።
የቡና ምርታማነት የሚጨምሩ ፓኬጆችን በአግባቡ መጠቀም በተቻለበት በ1 ሄክታር 11 ኩንታል የቡና ምርት ይገኛል ያሉት አቶ መስፍን፤ በዘንድሮው የምርት ዘመንም 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርት ለመሰብሰብ......
https://press.et/?p=137037
#በካዛንቺስ፣ አዋሬና ቤተመንግስት ዙሪያ #በኮሪደር_ልማትና በመልሶ ማልማት‼️
✍️ 674 በቀበሌ ቤት የሚኖሩ የልማት ተነሺዎች የተለዋጭ መኖሪያ ቤት ዕጣ አውጥተዋል፣
✍️ ከአካባቢዎቹ እስካሁን 1ሺ 218 የቀበሌ ቤቶች መረጃቸው ተጣርቶ ተደራጅቷል፣
✍️ የልማት ተነሺዎች በሂደቱ ቅሬታቸውን የሚያቀርቡበት ስርዓትም ተዘርግቷል፣
መስከረም 11 ቀን 2017 ዓም
✍️ 674 በቀበሌ ቤት የሚኖሩ የልማት ተነሺዎች የተለዋጭ መኖሪያ ቤት ዕጣ አውጥተዋል፣
✍️ ከአካባቢዎቹ እስካሁን 1ሺ 218 የቀበሌ ቤቶች መረጃቸው ተጣርቶ ተደራጅቷል፣
✍️ የልማት ተነሺዎች በሂደቱ ቅሬታቸውን የሚያቀርቡበት ስርዓትም ተዘርግቷል፣
መስከረም 11 ቀን 2017 ዓም
በትግራይ ክልል የሰፈነውን ሰላም ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በትግራይ ክልል የተገኘውን ሰላም ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባና በየደረጃው ያለው አመራር ይህንን ተገንዝቦ መስራት እንዳለበት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ ገለፁ።
''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የዓለም የሰላም ቀን በመቀሌ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
ቀኑን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንትና የሰላምና የፀጥታ ካቤኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ ፤ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፌደራል መንግስት ጋር የጀመራቸው ሰላምን የማረጋገጥ ሥራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት የተገኘውን ሰላም ጠብቆ እና ተንከባክቦ ለዘላቂነቱ መስራት እንደሚገባ ያመለከቱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ በየደረጃው ያለው አመራርም ይህንን ተገንዝቦ መስራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል።
በውይይቱ የተሳተፈችው ወጣት ፃድቃን ገብረ እግዚአብሔር ሰላም የሁሉም መሰረት በመሆኑ መጠበቅ አለበት ስትል ገልጻለች።
በግጭት ይበልጥ ለጥቃት ተጋላጭ የሚሆኑ ሴቶችና ህፃናት ናቸው ያለችው ወጣትዋ፤ በዚህም ሰላምን የመጠበቅ ኃላፊነት አለብን ብላለች።
እንደ ኢዜአ ዘገባ በክልሉ የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማትና የወጣቶች ተጠቃሚነትን ለማስቀጠል ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጎን ሆነን እንሰራለን ያለው ደግሞ ወጣት ክብሮም ሰለሞን ነው።
መስከረም 11 ቀን 2017 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
በትግራይ ክልል የተገኘውን ሰላም ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባና በየደረጃው ያለው አመራር ይህንን ተገንዝቦ መስራት እንዳለበት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ ገለፁ።
''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የዓለም የሰላም ቀን በመቀሌ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
ቀኑን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንትና የሰላምና የፀጥታ ካቤኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ ፤ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፌደራል መንግስት ጋር የጀመራቸው ሰላምን የማረጋገጥ ሥራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት የተገኘውን ሰላም ጠብቆ እና ተንከባክቦ ለዘላቂነቱ መስራት እንደሚገባ ያመለከቱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ በየደረጃው ያለው አመራርም ይህንን ተገንዝቦ መስራት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል።
በውይይቱ የተሳተፈችው ወጣት ፃድቃን ገብረ እግዚአብሔር ሰላም የሁሉም መሰረት በመሆኑ መጠበቅ አለበት ስትል ገልጻለች።
በግጭት ይበልጥ ለጥቃት ተጋላጭ የሚሆኑ ሴቶችና ህፃናት ናቸው ያለችው ወጣትዋ፤ በዚህም ሰላምን የመጠበቅ ኃላፊነት አለብን ብላለች።
እንደ ኢዜአ ዘገባ በክልሉ የሰፈነውን ሰላም በማፅናት ልማትና የወጣቶች ተጠቃሚነትን ለማስቀጠል ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጎን ሆነን እንሰራለን ያለው ደግሞ ወጣት ክብሮም ሰለሞን ነው።
መስከረም 11 ቀን 2017 ዓም
👍1