Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የዘንድሮ ኢሬቻ በዓል መስከረም 25 እና 26 ይከበራል
*****
(ኢ ፕ ድ)

የ2017 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ መስከረም 25 ቀን በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ ፣ መስከረም 26 ቀን ደግሞ በቢሾፍቱ ሆራ ሃርሰዴ እንደሚከበር የኦሮሚያ ሕብረት አባገዳዎች አስታወቀ።

የመጫ አባገዳ እና የኦሮሚያ ሕብረት አባገዳዎች ሰብሳቢ አባገዳ ወርቅነህ ተሬሳ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የኦሮሞ ሕዝብ ከሚያከብራቸው የእርቅና የሰላም ክብረ በዓላት መካከል ኢሬቻ አንዱ ነው። በዓሉም ዘንድሮ መስከረም 25 ቀን በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ፣ መስከረም 26 ቀን ደግሞ በቢሾፍቱ ሆራ ሃርሰዴ ይከበራል፡፡

የ2017 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል መስከረም 25 ቀን በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ ፣ መስከረም 26 ቀን ደግሞ በቢሾፍቱ ሆራ ሃርሰዴ እንደሚከበር አመልክተው፤ በዓሉን ለመታደም የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች የባህል ልብሳቸውን በመልበስ በዓሉን በፍቅር፣ በአንድነትና በሰላም......

https://press.et/?p=137103
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ፈውስ ያገኙ ልቦች‼️

አክሊለ በቀለ ትባላለች፡፡ ቤተሰቦቿ የልብ ችግር እንዳለባት ያወቁት የስድስት ወር ህጻን እያለች ነው። የነበረብኝ የልብ ህመም የልብ ቀዶ ህክምና ማድረግ እንዳብኝ የሚያስገድድ ነበር የምትለው አክሊለ ከ23 ዓመት በፊት የሁለት ዓመት ከስድስት ወር ህጻን እያለች በእስራኤል ሀገር በሚገኝ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት አማካኝነት የቀዶ የህክምና ማድረጓን ትገልጻለች፡፡

አክሊለ በወቅቱ በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ህክምና ሃኪም አለመኖሩን ገልጻ፤ ነገር ግን የልብ ካርዲዎሎጂስቶች ባደረጉልኝ ህክምና የልብ ችግሩ እንዳብኝና ከሀገር ውጭ ወጥቼ ቀዶ ህክምናውን ማድረግ እንዳብኝ አሳውቀውኛል ትላለች፡፡

ከዛም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አማካኝነት እስራኤል ካለው ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሴቭ ዘ ቺልድረን ጋር መገናኘት በመቻሏ በእስራኤል ሀገር የልብ ቀዶ ህምናውን ማድረጓን ታስታውሳለች፡፡

አሁን ላይ አክሊለ በተደረገላት ህክምና ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ጤነኛ መሆኗንና ነርሲንግ ትምህርት ተምራ በአሁኑ ጊዜ በልብ ቀዶ ህክምና ወቅት ልብና ሳንባን ተክቶ የሚሠራ ማሽን ላይ ለመሥራት የውጭ የትምህርት እድል አግኝታ ለመሄድ ዝግጅት ላይ መሆኗን ተናግራለች፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ወላጆች በዚህ ህመም ምክንያት ከልጆቻቸው ጋር እየተቸገሩ መሆናቸውን የምትገልጸው አክሊለ፤ በኢትዮጵያ ልብ ህሙማ ህጻናት መርጃ ማዕከል ብቻ ከስምንት ሺህ በላይ ህጻናት ወረፋ እየጠበቁ...

https://press.et/?p=137102
ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ለናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ትግበራ በጋራ ለመስራት ተሰማሙ
*******
(ኢ ፕ ድ)

በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ራምዳን ሞሀመድ አብዱላህ ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

ሁለቱ አገራት በናይል ተፋሰስ ፍትሃዊና እኩል ተጠቃሚነት ላይ ባላቸው ወጥ አቋም ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል።

አምባሳደር ታዬ ደቡብ ሱዳን የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በፓርላማ ማፅደቋ የአገሪቱ ሕዝብ በናይል ተፋሰስ በፍትሀዊነትና እኩል ተጠቃሚነት ላይ ያለውን መብት ያስከበረ መሆኑን ገልጸዋል።

በውይይቱ ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ሙሉ ትግበራ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ደቡብ ሱዳን የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍን በፓርላማ አጽድቃ ለአፍሪካ ኀብረት ማቅረቧን ተከትሎ ኡጋንዳ እ.ኤ.አ. በጥቅምት አጋማሽ የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን መመሥረት የሚያስችለውን ሁለተኛውን የናይል ጉባዔ ለማዘጋጀት ያሳየችውን ቁርጠኝነት መደገፏ ይታወሳል።
በሮምና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለዓባይ ግድብ ከ3200 ዩሮ በላይ አበረከቱ
******
(ኢ ፕ ድ)

በሮምና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለዓባይ ግድብ 3250 ዩሮ በቦንድና ስጦታ ሲያበረክቱ፣ 5000 ዩሮ ለመለገስ ቃል ገብተዋል።

በጣሊያን የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ፣ ግድብን ለማጠናቀቅም መንግስት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለቀሪ ስራዎች ማጠናቀቂያ ዳያስፖራው ቦንድ እንዲገዛ ጥሪ ማቅረባቸውን ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

መስከረም 12 ቀን 2017 ዓም
በገበያ መር የኢኮኖሚ ሥርዓት የመንግሥት ሚና
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ ገብታለች። የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረትን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይነሳል።

የሀገር ውስጥ ገቢን፣ የፋይናንስ ዘርፉን አካታችነትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የውጭ ምንዛሬ መዛባትን ለማስተካከል እንደሚያግዝም ተገልጿል።

ማሻሻያው ሀገሪቱን ወደ ገበያ መር ኢኮኖሚ ሥርዓት ሊያስገባት እንደሚችል ደግሞ የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ።

ለመሆኑ ገበያ መር ኢኮኖሚ ሲባል ምን ማለት ነው? በአሁኑ ዘመን ዓለም ላይ በዚህ መንገድ ኢኮኖሚያቸውን የሚያንቀሳቅሱ ሀገራት እነማን ናቸው? ስኬታቸውስ ምን ይመስላል? ስንል ጠይቀናል።

የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ቆስጠንጢኖስ በርኸ (ዶ/ር)፤ ገበያ መር ኢኮኖሚ ሲባል ገበያው ዋጋን እንዲወስን የሚያስችል ነው። ባለሀብቶች የሚሳተፉበት፣ ከፍተኛ...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=137162
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
በአዲስ አበባ በተፈጠረ የቤንዚን እጥረት ለእንግልት መዳረጋቸውን አሽከርካሪዎች ገለጹ
************
(ኢ ፕ ድ)
- የነዳጅ እጥረት የተፈጠረበትን ምክንያት የማጣራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ባለሥልጣኑ አስታውቋል
በአዲስ አበባ ከተማ በማደያዎች ላይ ቤንዚን እጥረት ምክንያት ለእንግልት መዳረጋቸውን የከተማዋ አሽከርካሪዎች ገለጹ። የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን በከተማው ሚስተዋለውን የነዳጅ እጥረት ምክንያት የማጣራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን አስታውቋል።

አሽከርካሪ አቶ ሚኪያስ ሰይፉ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በከተማው ከፍተኛ የነዳጅ ሰልፍ ይታያል። በርካታ አካባቢዎች የሚገኙ ማደያዎች ላይ ቤንዚን የለም እየተባለ ነው።

ከመርካቶ ተክለሃይማኖት አካባቢ ቤንዚን ለመቅዳት ከሁለት ሰዓታት በላይ በወረፋ ማሳለፋቸውን ገልጸው፤ ይህም በሥራቸው ላይ ተጽእኖ የፈጠረባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሽከርካሪ ወይዘሮ መዓዛ አሰግድ በበኩላቸው፤ በአዲስ አበባ በአብዛኛው አካባቢ በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ቤንዚን እንደማይገኝ ማስተዋላቸውን ተናግረዋል። ቤንዚን በሚገኝባቸው የነዳጅ ማደያዎችም ረዥም ሰልፍ መኖሩን አንስተዋል።

በቀበና አካባቢ ከአመሻሹ አስራ አንድ ሰዓት የተሰለፉት ሰልፍ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ድረስ ጠብቀው እንደቀዱ
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=137181
የጎቤና ሺኖዬ ጨዋታ ማጠቃለያ እየተካሄደ ነው
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከጳጉሜ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው አመታዊ የወጣቶች የዘመን መለወጫ የብስራት የአደባባይ ጨዋታ ጎቤና ሺኖዬ ማጠቃለያ እየተካሄደ ነው።

ጎቤና ሺኖዬ በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በአዲስ አበባ ሲከበር ቆይቷል።

ጎቤና ሺኖዬ የተሰኘው የአዲስ ዓመት የአደባባይ የኦሮሞ ወጣት ወንዶችና የልጃገረዶች ጨዋታ (ካርኒቫል) በየዓመቱ በአደባባይ የሚከበር ነው።

በማርቆስ በላይ
መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም
#የዓለም_የቱሪዝም_ቀን

የዓለም የቱሪዝም ቀንን በኢጋድ የቱሪዝም ሻምፒዮኗ ኢትዮጵያ ያክብሩ ።
#አንድነትፓርክ ‼️

መቼ መስከረም 29 ቀን 2012 ዓም ተመረቀ

የት ቤተ መንግስት ግቢ ይገኛል

በምረቃው ላይ ማን ማን ተገኘ

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የቀድሞው የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ፣ የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ አብዱላሂ ሞሃመድ፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት፣ የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ፣ የበርካታ ሀገራት ተወካዮች እና አምባሳደሮች፤ የክልል ፕሬዝዳንቶችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

አንድነት ፓርክን ይጎብኙ
👍1