ሁለቱ ምክር ቤቶች ዛሬ ሥራ ይጀምራሉ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመናቸውን ዛሬ ከሰዓት ከቀኑ 8 ሰዓት በሚያካሂዱት የጋራ ስብሰባ ይጀምራሉ።
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል።
በድንጋጌው መሰረት የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓትም የሪፐብሊኩ ፕሬዚደንት በተገኙበት እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይም የሪፐብሊኩ ፕሬዚደንት ለሁለቱ የፌዴራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌዴራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመናቸውን ዛሬ ከሰዓት ከቀኑ 8 ሰዓት በሚያካሂዱት የጋራ ስብሰባ ይጀምራሉ።
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል።
በድንጋጌው መሰረት የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓትም የሪፐብሊኩ ፕሬዚደንት በተገኙበት እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይም የሪፐብሊኩ ፕሬዚደንት ለሁለቱ የፌዴራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌዴራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም
👍1😁1
የአፋር ክልል ሕብረተሰብ ክፍሎች እና ባለድርሻ አካላት ያደራጁትን አጀንዳ ለኮሚሽኑ አስረከቡ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የአፋር ክልል ሕብረተሰብ ክፍሎች እና ባለድርሻ አካላት ለስድስት ቀናት ሲያካሂዱ በቆዩት አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ ያደራጁትን አጀንዳ በተወካዮቻቸው ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል።
በሀገር ደረጃ በሚደረገው ምክክር ክልሉን የሚወክሉ ተሳታፊዎችንም መርጠዋል።
በርክክብ ሥነስረዓቱ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ብሌን ገብረመድህን፤ ከአፋር ክልል የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ከሌሎች ክልሎች ከተሰበሰቡ አጀንዳዎች ጋር በሀገር ደረጃ በሚካሄደው ጉባኤ ቀርበው ምክክር ይደረግባቸዋል ብለዋል።
ኮሚሽነር አምባሳደር አይሮሪት መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ እንዲሳካ አስተዋፅኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል።
በአጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ በክልሉ ከሚገኙ 49 ወረዳዎች የተመረጡ ከ800 በላይ የሕብረተሰብ ክፍል ወኪሎች እና በክልልሉ የሚገኙ ከ700 በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሦስቱ የመንግስት አካላት፣ የተለያዩ ተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተሳትፈዋል፡፡
ተስፋ ፈሩ (ሰመራ)
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም.
******************
(ኢ ፕ ድ)
የአፋር ክልል ሕብረተሰብ ክፍሎች እና ባለድርሻ አካላት ለስድስት ቀናት ሲያካሂዱ በቆዩት አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ ያደራጁትን አጀንዳ በተወካዮቻቸው ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል።
በሀገር ደረጃ በሚደረገው ምክክር ክልሉን የሚወክሉ ተሳታፊዎችንም መርጠዋል።
በርክክብ ሥነስረዓቱ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ብሌን ገብረመድህን፤ ከአፋር ክልል የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ከሌሎች ክልሎች ከተሰበሰቡ አጀንዳዎች ጋር በሀገር ደረጃ በሚካሄደው ጉባኤ ቀርበው ምክክር ይደረግባቸዋል ብለዋል።
ኮሚሽነር አምባሳደር አይሮሪት መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ እንዲሳካ አስተዋፅኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል።
በአጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ በክልሉ ከሚገኙ 49 ወረዳዎች የተመረጡ ከ800 በላይ የሕብረተሰብ ክፍል ወኪሎች እና በክልልሉ የሚገኙ ከ700 በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሦስቱ የመንግስት አካላት፣ የተለያዩ ተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተሳትፈዋል፡፡
ተስፋ ፈሩ (ሰመራ)
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም.
👍2👎1
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ መቸገራቸውን ገለጹ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የካምባ ከተማ አስተዳደርና ካምባ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ ተቸግረናል ሲሉ ገለጹ፡፡
የካምባ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር የሆኑትና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ግለሰብ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ወርሐዊ ደመወዝ እስከ 15 ቀን ድረስ እየዘገየ ይገባል።
በዚህ መሐል መምህራን ሥራ ስለሚያቆሙ ተማሪዎች እየተጉላሉና እየተበተኑ ይገኛሉ።
አሁን ላይ ጉዳዩን ይበልጥ ከባድ ያደረገው የአንድ ወር ደመወዝ መታጠፉ መሆኑን በመጥቀስ፤ የሐምሌ ወር ደመወዝ ተዘሎ የነሐሴ ወር ነው የተከፈለው።
ጥሬ ገንዘብ የለም በሚል እስካሁንም ድረስ የሐምሌ ደመወዝ አልገባልንም ብለዋል።
መምህር ሌላ ተጨማሪ ሥራ የለውም የወር ደመወዙን ጠብቆ ነው የሚተዳደረው እንዲህ አይነት ችግር ሲገጥም ደግሞ የመምህራንን ኑሮ ያከብደዋል ሲሉም ገልጸዋል።
ወረዳውን ስንጠየቅ ምንም ማድረግ አንችልም፤ ዞን ሲጠየቅ ደግሞ ከኔ አቅም በላይ ነው ይላሉ በማለት እስካሁን በቂ ምክንያት ማግኘት…..
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=138068
******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የካምባ ከተማ አስተዳደርና ካምባ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ ተቸግረናል ሲሉ ገለጹ፡፡
የካምባ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር የሆኑትና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ግለሰብ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ወርሐዊ ደመወዝ እስከ 15 ቀን ድረስ እየዘገየ ይገባል።
በዚህ መሐል መምህራን ሥራ ስለሚያቆሙ ተማሪዎች እየተጉላሉና እየተበተኑ ይገኛሉ።
አሁን ላይ ጉዳዩን ይበልጥ ከባድ ያደረገው የአንድ ወር ደመወዝ መታጠፉ መሆኑን በመጥቀስ፤ የሐምሌ ወር ደመወዝ ተዘሎ የነሐሴ ወር ነው የተከፈለው።
ጥሬ ገንዘብ የለም በሚል እስካሁንም ድረስ የሐምሌ ደመወዝ አልገባልንም ብለዋል።
መምህር ሌላ ተጨማሪ ሥራ የለውም የወር ደመወዙን ጠብቆ ነው የሚተዳደረው እንዲህ አይነት ችግር ሲገጥም ደግሞ የመምህራንን ኑሮ ያከብደዋል ሲሉም ገልጸዋል።
ወረዳውን ስንጠየቅ ምንም ማድረግ አንችልም፤ ዞን ሲጠየቅ ደግሞ ከኔ አቅም በላይ ነው ይላሉ በማለት እስካሁን በቂ ምክንያት ማግኘት…..
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=138068
👍5😢1
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ12ኛ ከፍል ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና ሰጡ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሃገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ላሳለፉ ትምህርት ቤቶች እውቅና ሰጡ።
በእውቅና ሽልማት መርጋግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግርም በ12 ኛ ክፍል ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የከተማዋም የሃገርም ኩራት ናቸው ብለዋል።
የምመጣው ውጤት ባጋጣሚ የመጣ ሳይሆን በብዙ ልፋትና ትጋት የተገኘ ነው ያሉ ከንቲባዋ ውጤቱ ከተማዋንም ሆነ ሃገራችንን ያኮራ ነው ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ውጤት በአስደንጋጭ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን አንስተው መንግስት ለትምህርት ዘርፉ በሰጠው ትኩረት ዘንድሮ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከንቲባዋ ይህ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላረጉ ወላጆች መምህራንና ትምህርትቤቶች ምስጋና አቅርበው፤ ከተማ አስተዳደሩ ከአንድ እስከ ሶስት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት ተማሪዎች የስኮላርሺፕ እድል እንዳመቻቸ አሳውቀዋል ።
በዳግማዊት አበበ
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓም
********************
(ኢ ፕ ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሃገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ላሳለፉ ትምህርት ቤቶች እውቅና ሰጡ።
በእውቅና ሽልማት መርጋግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግርም በ12 ኛ ክፍል ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የከተማዋም የሃገርም ኩራት ናቸው ብለዋል።
የምመጣው ውጤት ባጋጣሚ የመጣ ሳይሆን በብዙ ልፋትና ትጋት የተገኘ ነው ያሉ ከንቲባዋ ውጤቱ ከተማዋንም ሆነ ሃገራችንን ያኮራ ነው ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ውጤት በአስደንጋጭ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን አንስተው መንግስት ለትምህርት ዘርፉ በሰጠው ትኩረት ዘንድሮ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከንቲባዋ ይህ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላረጉ ወላጆች መምህራንና ትምህርትቤቶች ምስጋና አቅርበው፤ ከተማ አስተዳደሩ ከአንድ እስከ ሶስት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት ተማሪዎች የስኮላርሺፕ እድል እንዳመቻቸ አሳውቀዋል ።
በዳግማዊት አበበ
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓም
👍5
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ የሙዝ፣ ፓፓያ እና አቮካዶ ፍራፍሬ ልማት‼️
👍9👎1
በመኖሪያ ቤት ተጀምሮ አደባባይ የወጣው የኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳት ማምረት ሥራ
. . . ምንም ዓይነት የስፌት ስልጠና ሳትወስድ ባለቤቷ የጻፏቸውን የኦሮሞ ባሕላዊና ታሪካዊ እሴቶችን ብቻ በማንበብ የኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳት ምን እንደሚመስሉ ተረድታለች።
አልባሳቱ ላይ የሚደረጉ ጌጣጌጦችንም እንዲሁ በንባብና ከባለቤቷ ታሪኩን በመረዳት ወደ ሥራው የገባችው ወይዘሮ አይሻ፤ ከልጆቿ ጋር በመኖሪያ ቤቷ ውስጥ የጀመረችው ሥራም ወደ ቢዝነስ ተቀይሮ ኑሮዋን መደገፍ ችሏል።
ለኦሮሞ ባሕል ካላት ቅርበት የተነሳ መደበኛ ሥራዋን ቀን ቀን እየሰራች ሌሊት ደግሞ ባሕላዊ አልባሳቱን እየሰራች ገበያ ውስጥ መግባት ችላለች።
የኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳት ከቁርበትና ቆዳ ይሰራ እንደነበር ያስታወሰችው ወይዘሮ አይሻ፤ የዘመኑ ሰው አልባሳቱን በቀላሉ መጠቀም እንዲችልና ከትውልድ ወደ ትውልድ በቀላሉ እንዲተላለፍ ለማድረግ በካባና ተቀራራቢ በሆኑ ጨርቆች ላይ እንዲሰራ ማድረግ የቻሉ ባለቤቷ እንደሆኑ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=137965
. . . ምንም ዓይነት የስፌት ስልጠና ሳትወስድ ባለቤቷ የጻፏቸውን የኦሮሞ ባሕላዊና ታሪካዊ እሴቶችን ብቻ በማንበብ የኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳት ምን እንደሚመስሉ ተረድታለች።
አልባሳቱ ላይ የሚደረጉ ጌጣጌጦችንም እንዲሁ በንባብና ከባለቤቷ ታሪኩን በመረዳት ወደ ሥራው የገባችው ወይዘሮ አይሻ፤ ከልጆቿ ጋር በመኖሪያ ቤቷ ውስጥ የጀመረችው ሥራም ወደ ቢዝነስ ተቀይሮ ኑሮዋን መደገፍ ችሏል።
ለኦሮሞ ባሕል ካላት ቅርበት የተነሳ መደበኛ ሥራዋን ቀን ቀን እየሰራች ሌሊት ደግሞ ባሕላዊ አልባሳቱን እየሰራች ገበያ ውስጥ መግባት ችላለች።
የኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳት ከቁርበትና ቆዳ ይሰራ እንደነበር ያስታወሰችው ወይዘሮ አይሻ፤ የዘመኑ ሰው አልባሳቱን በቀላሉ መጠቀም እንዲችልና ከትውልድ ወደ ትውልድ በቀላሉ እንዲተላለፍ ለማድረግ በካባና ተቀራራቢ በሆኑ ጨርቆች ላይ እንዲሰራ ማድረግ የቻሉ ባለቤቷ እንደሆኑ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=137965
👍2😁2
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ማን ናቸው?
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የተወለዱት በደባርቅ ሰሜን ጎንደር ነው፡፡
የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት አግኝተዋል።
እንግሊዝ ከሚገኘው ላንክስተር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በዓለም አቀፍ ግንኙነት እና በስትራቴጂ ጥናት ሁለተኛ ድግሪያቸውን ወስደዋል።
በተለያዩ ሀገራት አጫጭር የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ፖለቲካል ሳይንስ ሥልጠናዎችን እና ኮርሶችን ወስደዋል።
አምባሳደር ታዬ፤ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ መምሪያ የሥራ ክፍል ፣የምዕራብ አውሮፓ ዋና ክፍል ኃላፊ፣የኢንፎርሜሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር፣ስቶክሆልም የኢፌዲሪ ኤምባሲ በአማካሪነት፣በዋሽንግተን የኢፌዲሪ ኤምባሲ በአማካሪነት።
በሎስአንጀለስ ቆንስል ጀነራል፣ በ1998ዓ.ም ባለሙሉሥልጣን አምባሳደርነት ተሹመዋል፣
በሎስአንጀለስ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ማዕረግ የቆንስላ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ በአውሮፓ እና አሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል፣ በ2008 ዓ.ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሰርተዋል።
በግብፅ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ሰርተዋል፤
አምባሳደር ታዬ እስከዛሬዋ ዕለት ድረስም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ሠርተዋል።
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የተወለዱት በደባርቅ ሰሜን ጎንደር ነው፡፡
የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት አግኝተዋል።
እንግሊዝ ከሚገኘው ላንክስተር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በዓለም አቀፍ ግንኙነት እና በስትራቴጂ ጥናት ሁለተኛ ድግሪያቸውን ወስደዋል።
በተለያዩ ሀገራት አጫጭር የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ፖለቲካል ሳይንስ ሥልጠናዎችን እና ኮርሶችን ወስደዋል።
አምባሳደር ታዬ፤ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ መምሪያ የሥራ ክፍል ፣የምዕራብ አውሮፓ ዋና ክፍል ኃላፊ፣የኢንፎርሜሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር፣ስቶክሆልም የኢፌዲሪ ኤምባሲ በአማካሪነት፣በዋሽንግተን የኢፌዲሪ ኤምባሲ በአማካሪነት።
በሎስአንጀለስ ቆንስል ጀነራል፣ በ1998ዓ.ም ባለሙሉሥልጣን አምባሳደርነት ተሹመዋል፣
በሎስአንጀለስ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ማዕረግ የቆንስላ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ በአውሮፓ እና አሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል፣ በ2008 ዓ.ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሰርተዋል።
በግብፅ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ሰርተዋል፤
አምባሳደር ታዬ እስከዛሬዋ ዕለት ድረስም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ሠርተዋል።
👍10🔥2❤1
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ‼️
👉 ኢኮኖሚያችን አዲስ የታሪክ እጥፋት ላይ ነው
👉 በግብርና መስክ ባለፈው አመት 6 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ተመዝግቧል
👉በ2016 በጀት አመት 230 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ተመርቷል
👉 በ2016 በጀት አመት 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ታርሷል፤
👉 በሌማት ቱሩፋት በሁሉም ክልሎች ከፍተኛ ምርት ተገኝቷል፤
👉በአረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ስድስት አመታት 40 ቢሊዮን ችግኝ ተተክሏል፤
👉 በኢንዱስትሪው መስክ 9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፤
👉 የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ምርታማነት እድገት 59 በመቶ ደርሷል፤
👉 395 ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ተመልስዋል፤
👉በአገልግሎት መስክ 7 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፤
👉 737 የመንግስት አገልግሎቶች በኤሌክትሮኒክስ እየተሰጡ ነው፤
👉 የሁሉም ባንኮች ሀብት 2 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፤
👉የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች 39 ነጥብ 6 ሚሊዮን ደርሷል፤
👉 በዲጂታል የተላለፈ የብር መጠን 9 ነጥብ 6 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፤
👉የመንገድ ሽፋን 169 ሺ 600 ደርሷል፤
👉 የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ ቁጥር 83 ነጥብ 3 ሚሊዮን ደርሷል፤
👉የንጹህ ውሃ ተጠቃሚዎች ቁጥር 74 ነጥብ 8 ሚሊዮን ደርሷል፤
👉 የአባይ ግድብ አጠቃላይ ግንባታ 96 ነጥብ 7 በመቶ በላይ ተጠናቋል
👉 ኢኮኖሚያችን አዲስ የታሪክ እጥፋት ላይ ነው
👉 በግብርና መስክ ባለፈው አመት 6 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ተመዝግቧል
👉በ2016 በጀት አመት 230 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ተመርቷል
👉 በ2016 በጀት አመት 26 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ታርሷል፤
👉 በሌማት ቱሩፋት በሁሉም ክልሎች ከፍተኛ ምርት ተገኝቷል፤
👉በአረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ስድስት አመታት 40 ቢሊዮን ችግኝ ተተክሏል፤
👉 በኢንዱስትሪው መስክ 9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፤
👉 የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ምርታማነት እድገት 59 በመቶ ደርሷል፤
👉 395 ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ተመልስዋል፤
👉በአገልግሎት መስክ 7 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፤
👉 737 የመንግስት አገልግሎቶች በኤሌክትሮኒክስ እየተሰጡ ነው፤
👉 የሁሉም ባንኮች ሀብት 2 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፤
👉የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች 39 ነጥብ 6 ሚሊዮን ደርሷል፤
👉 በዲጂታል የተላለፈ የብር መጠን 9 ነጥብ 6 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፤
👉የመንገድ ሽፋን 169 ሺ 600 ደርሷል፤
👉 የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ ቁጥር 83 ነጥብ 3 ሚሊዮን ደርሷል፤
👉የንጹህ ውሃ ተጠቃሚዎች ቁጥር 74 ነጥብ 8 ሚሊዮን ደርሷል፤
👉 የአባይ ግድብ አጠቃላይ ግንባታ 96 ነጥብ 7 በመቶ በላይ ተጠናቋል
👍19🕊6😁2🤔1
የአፍሪካ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
**************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል መታሰቢያ “አፍሪካን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማላቅ” በሚል ይካሄዳል፡፡
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት የሚካሄደዉ 3ኛው ዙር ፓን አፍሪኮን ኤ.አይ 2024 ኮንፈረንስ ለሁለት ቀናት መስከረም 28 እና 29፣ 2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ኢንሰቲትዩት አሰታውቋል።
መስከረም 28 ቀን 2017 ዓም
**************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል መታሰቢያ “አፍሪካን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማላቅ” በሚል ይካሄዳል፡፡
በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት የሚካሄደዉ 3ኛው ዙር ፓን አፍሪኮን ኤ.አይ 2024 ኮንፈረንስ ለሁለት ቀናት መስከረም 28 እና 29፣ 2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ኢንሰቲትዩት አሰታውቋል።
መስከረም 28 ቀን 2017 ዓም
👍2
በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ የኢትዮጵያን ተሳትፎ ለማሳደግ የንግድ ማህበራት በትኩረት ሊሠሩ ይገባል
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ የኢትዮጵያን ተሳትፎ ለማሳደግ የንግድ ማህበራት በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ ተገለጸ።
የዓለም አቀፍ ንግድ ፖሊሲ ባለሙያ አቶ ጃሌቶ ገመዲ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ በቅርቡ በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ዙሪያ ሊኖሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ውጤታማ ትግበራ እንዲኖር ለማስቻል እንዲሁም የግሉ ሴክተር እና ላኪዎችን ተደራሽነት ለማሳደግ ያለመ ጥናት መካሄዱን ጠቁመው፤ በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ዙሪያ የንግዱ ማህበረሰብ ግንዛቤ አናሳ መሆኑን አንስተዋል።
በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ የኢትዮጵያን ተሳትፎ ለማሳደግም የንግድ ማህበራት በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የተቀመጡ አሠራሮችና ሕጎች፣ ውስብስብ የፈቃድ አሰጣጥ ሥርዓቶችና የቁጥጥር ማነቆዎች ተግዳሮት እየፈጠሩ መሆኑን የጠቀሱት ባለሙያው፤ ወጥነት የጎደለው የአፈፃፀምና የአሰራር ቅልጥፍናም ተጽዕኖ እየፈጠረ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ላይ ያላትን ግንዛቤ የተመለከተውን ጥናት መነሻ አድርገው እንደገለጹት፤ በተለይም ከአፈፃፀሙ ጋር በተያያዙ የተለያዩ ተግዳሮቶች መኖራቸውን....
https://press.et/?p=138142
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ የኢትዮጵያን ተሳትፎ ለማሳደግ የንግድ ማህበራት በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ ተገለጸ።
የዓለም አቀፍ ንግድ ፖሊሲ ባለሙያ አቶ ጃሌቶ ገመዲ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ በቅርቡ በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ዙሪያ ሊኖሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ውጤታማ ትግበራ እንዲኖር ለማስቻል እንዲሁም የግሉ ሴክተር እና ላኪዎችን ተደራሽነት ለማሳደግ ያለመ ጥናት መካሄዱን ጠቁመው፤ በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ዙሪያ የንግዱ ማህበረሰብ ግንዛቤ አናሳ መሆኑን አንስተዋል።
በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ የኢትዮጵያን ተሳትፎ ለማሳደግም የንግድ ማህበራት በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የተቀመጡ አሠራሮችና ሕጎች፣ ውስብስብ የፈቃድ አሰጣጥ ሥርዓቶችና የቁጥጥር ማነቆዎች ተግዳሮት እየፈጠሩ መሆኑን የጠቀሱት ባለሙያው፤ ወጥነት የጎደለው የአፈፃፀምና የአሰራር ቅልጥፍናም ተጽዕኖ እየፈጠረ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ላይ ያላትን ግንዛቤ የተመለከተውን ጥናት መነሻ አድርገው እንደገለጹት፤ በተለይም ከአፈፃፀሙ ጋር በተያያዙ የተለያዩ ተግዳሮቶች መኖራቸውን....
https://press.et/?p=138142
❤1👍1👎1
የማህበረሰቡ ልሳናት
************
(ኢ ፕ ድ)
ሀገራዊ እሴቶችን በማህበረሰቡ ቋንቋ ለየአካባቢው ማህበረሰብ ተደራሽ ለማድረግ የማህበረሰብ መገናኛ ብዙኃን የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑ እሙን ነው።
በሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማይሸፈኑ አካባቢያዊ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ በማድረስ የማህበረሰቡ ወግ፣ ባህልና ቋንቋ እንዲዳብር ከመስራት በተጨማሪ የማህበረሰቡ ትስስር እንዲጠናከርና ሰላም እንዲሰፍን በየአካባቢው ቋንቋ በማህበረሰቡ ዘንድ ግንዛቤ ሊፈጥሩ እንደሚገባ ይገለጻል።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ጣቢያ ጊዜያዊ ተጠሪ አቶ ኤፍሬም አክሊሉ እንደሚገልጹት፤ የሬዲዮ ጣቢያው በድሬዳዋ ከተማና አካባቢው ለሚኖሩ ዜጎች መረጃን ተደራሽ ለማድረግ በ2014 ዓ.ም የተቋቋመ ሲሆን፤ ለአንድ ዓመት የሙከራ ስርጭት ካከናወነ በኋላ ወደ መደበኛ ስርጭት መግባት ችሏል።
በአካባቢው የተለያዩ የሬዲዮ ጣቢያዎች ቢኖሩም ከእነኝህ ጣቢያዎች በተለየ መልኩ ታችኛውን የማህበረሰብ ክፍል አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚዳሰሱባቸውን መሰናዶዎች......
https://press.et/?p=138139
************
(ኢ ፕ ድ)
ሀገራዊ እሴቶችን በማህበረሰቡ ቋንቋ ለየአካባቢው ማህበረሰብ ተደራሽ ለማድረግ የማህበረሰብ መገናኛ ብዙኃን የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑ እሙን ነው።
በሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማይሸፈኑ አካባቢያዊ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ በማድረስ የማህበረሰቡ ወግ፣ ባህልና ቋንቋ እንዲዳብር ከመስራት በተጨማሪ የማህበረሰቡ ትስስር እንዲጠናከርና ሰላም እንዲሰፍን በየአካባቢው ቋንቋ በማህበረሰቡ ዘንድ ግንዛቤ ሊፈጥሩ እንደሚገባ ይገለጻል።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ጣቢያ ጊዜያዊ ተጠሪ አቶ ኤፍሬም አክሊሉ እንደሚገልጹት፤ የሬዲዮ ጣቢያው በድሬዳዋ ከተማና አካባቢው ለሚኖሩ ዜጎች መረጃን ተደራሽ ለማድረግ በ2014 ዓ.ም የተቋቋመ ሲሆን፤ ለአንድ ዓመት የሙከራ ስርጭት ካከናወነ በኋላ ወደ መደበኛ ስርጭት መግባት ችሏል።
በአካባቢው የተለያዩ የሬዲዮ ጣቢያዎች ቢኖሩም ከእነኝህ ጣቢያዎች በተለየ መልኩ ታችኛውን የማህበረሰብ ክፍል አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚዳሰሱባቸውን መሰናዶዎች......
https://press.et/?p=138139
👍2