Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
#ከተራ_ጥምቀት

የከተራ በዓል አከባበር በአዲስ አበባ በፎቶ‼️
👍8
#ጎንደር_የጥምቀት_በዓል

በርካታ የውጪ አገራት ጎብኚዎች የተሳተፉበት የማለዳው የጎንደር የጥምቀት በዓል ድባብ
******
(ኢ ፕ ድ)

በጎንደር ባህረ ጥምቀት ለሚካሄደው ሥርዓተ ጥምቀት ለመሳተፍ በርካታ ቁጥር ያላቸው የበዓሉ ተሳታፊዎች ወደ ስፍራው እያቀኑ ነው።

በበዓሉ አከባበር ላይ ለመሳተፍ በርካታ የውጪ አገራት ዜጎች በጎንደር ባህረ ጥምቀት ተገኝተዋል።

በአሁኑ ሰዓት የቅዳሴ ሥርዓት የተጠናቀቀ ሲሆን በቀጣይ የዝማሬና የጥምቀት ሥርዓት የሚካሄድ ይሆናል።

ማርቆስ በላይ (ጎንደር)
👍3👏3
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ዐህመድ የተላከ መልዕክት ለዩጋንዳ እና ለኬንያ መሪዎች አደረሱ
*******
(ኢ ፕ ድ)

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተላከ መልዕክት ለዩጋንደው ፕሬዚደንት ዩዌሪ ሙሰቬኒና ለኬንያው ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ አደረሱ።

አምባሳደር ሬድዋን ሁለቱ መሪዎች መልካም ጉርብትናና ቀጣናዊ ትብበር እንዲጠናከር ለተጫወቱት በጎ ሚና እንዲሁም ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ላሳዩት ቀናዒነት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ያላቸዉን አድናቆት ገልጸውላቸዋል።

ፕሬዚደንቶቹም ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅትና በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር እንዲሁም በራሷ አቅም በሶማሊያና በሌሎችም ሀገራት ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የበረከተችውን አይተኬ ሚና በማውሳት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመጫወት ላይ ያሉትን ጉልህ ሚና ማድነቃቸውንና  በቀጣይም በሶማሊያ ሰላምና ሽብርተኝነትን በማዋጋት ረገድ የሚኖራትን ወሳኝ ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥል ያላቸውን ደጋፍና እምነት ገልፀዋል።

ከዚሁ በተያያዘ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጎልበትነና በኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና እንዲሰፍን ጠቀላይ ሚኒስተር ዐብይ በማድረግ ላይ ያሉት ጥረት እንደሚደግፉ የገለ‍ፁላቸው መሆኑንና የሀገሪቱ የፀጥታና ደህንነት ተቋማትም ለኢትዮጵያ አቻዎቻቸው አስፈላጊውን  ትብብር እንዲለግሱ መመሪያ መስጠታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢፕድ በላከው መረጃ አመላክቷል።

ጥር 11 ቀን  2017 ዓ.ም
👍4🔥1
#ጥምቀት በባቱ በወጣት ሁሴን ባቶ አንደበት

ወጣት ሁሴን ባቶ ይባላል። በደምበል ሐይቅ ጥምቀት በዓል ላይ በአስተባባሪነት በየዓመቱ ይሳተፋል።

ወጣቱ የእስልምና እምነት ተከታይ ቢሆንም በዓሉ የፍቅርና የአንድነትና በመሆኑ እዚህ ቦታ ላይ መገኘቱን ገልጾልናል።

ጥምቀት ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለም ቅርስ የሆነ በዓል ስለሆነ በየዓመቱ በዓሉ ላይ በአስተባባሪነት እሳተፋለሁ ብሏል።

ሁላችንም በዓሉን በፍቅርና በአንድነት ልንጠብቀው፣ ልንንከባከበውና ልናከብረው ይገባል ብሏል።

#ባቱ #ጥምቀት #ቱሪዝም #የዓለምቅርስ

በፋንታነሽ ክንዴ

ጥር 11 ቀን 2017 ዓም
6👍4👏1
ሁላችንም በፍቅርና በአንድነት በመቆም ለሀገር ሰላምና እድገት የሚጠበቅብንን ልንወጣ ይገባል
- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
*****
(ኢ ፕ ድ)
ሁላችንም በፍቅርና በአንድነት በመቆም ለሀገር ሰላም እና እድገት የሚጠበቅብንን ሃላፊነት ልንወጣ ይገባል ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ገለጹ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው ሃይማኖቶታዊ በዓላት መካከል ጥምቀት አንዱ ነው። በአዲስ አበባም በጃንሜዳ የጥምቀት በአል በልዩ ልዩ ሀይማኖታዊ ክንዋኔዎች በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመላው ሀገሪቱ የጥምቀትን በዓል እያከበሩ ለሚገኙ ምዕምናን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሰው ልጅ ዘላቂ ሕይወትን መቀዳጀት የሚችለው ፈርሃ እግዚአብሄርን መላበስ ሲችል ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በአሁኑ ጊዜ ፈጣሪ ከሰዎች የሚጠብቀውን መልካም ስብእናዎች ከመላበስ አኳያ የሚስተዋሉ ችግሮች የሰው ልጅን ለአደጋ ሲያጋልጡ ማስተዋል እየተለመደ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ሁሉም ቆም ብሎ ስለሰላም ማሰብ ይኖርበታል ብለዋል።

ሁሉም በፍቅርና በአብሮነት በመቆም ለሀገር ሰላም እና እድገት የሚጠበቅበትን ሃላፊነት መወጣት እንዳለበት ነው የገለጹት።

ህብረተሰቡ ፈጣሪ የሰጠውን ጸጋ በመጠቀም እርስ በእርስ በመተሳሰብና በአብሮነት ለሀገር ሰላም እና እድገት ማነቆ የሆኑ ችግሮችን መቅረፍ ይኖርበታል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

#ጥምቀት
👍133👏2
የአረንጓዴ ዓሻራ ስራችን በፍራፍሬ እጅጉን ተስፋ ሰጪ ጅማሮ ያሳያል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍8