This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በኢትዮጵያ በሁሉም የአየር ጠባይ የሚያገለግሉ መንገዶች ከ126 ሺህ ወደ 170 ሺህ ኪሎ ሜትር አድጓል
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ በሁሉም የአየር ጠባይ የሚያገለግሉ መንገዶች በስድስት አመታት ብቻ ከ126 ሺህ ኪሎ ሜትር ወደ 170 ሺህ ኪሎ ሜትር እንዳደገ ያውቃሉ?
በፌዴራል መንግሥት የተሰሩ የአስፋልት መንገዶች ብቻ 26 ሺህ 722 ኪሎ ሜትር ያህል ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት በተለያየ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ከነዚህም መካከል የ63 ኪሎ ሜትር የጅማ-አጋሮ-በሻሻ የመንገድ ፕሮጀክት የሚገኝበት ሲሆን ወደ ታሪካዊው የጅማ አባጅፋር ቤተ መንግሥት የሚያዳርስ ዐበይት ከተሞችን የሚያገናኙ ሰፋፊ መንገዶች የተካተቱበት መንገድ ይገኛል።
በጅማ እና አጋሮ ብቻ ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ የከተማ መንገዶች የተለዩ የብስክሌት መጋለቢያዎች አካተዋል።
#መንገድ #ኢትዮጵያ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ በሁሉም የአየር ጠባይ የሚያገለግሉ መንገዶች በስድስት አመታት ብቻ ከ126 ሺህ ኪሎ ሜትር ወደ 170 ሺህ ኪሎ ሜትር እንዳደገ ያውቃሉ?
በፌዴራል መንግሥት የተሰሩ የአስፋልት መንገዶች ብቻ 26 ሺህ 722 ኪሎ ሜትር ያህል ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት በተለያየ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ከነዚህም መካከል የ63 ኪሎ ሜትር የጅማ-አጋሮ-በሻሻ የመንገድ ፕሮጀክት የሚገኝበት ሲሆን ወደ ታሪካዊው የጅማ አባጅፋር ቤተ መንግሥት የሚያዳርስ ዐበይት ከተሞችን የሚያገናኙ ሰፋፊ መንገዶች የተካተቱበት መንገድ ይገኛል።
በጅማ እና አጋሮ ብቻ ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ የከተማ መንገዶች የተለዩ የብስክሌት መጋለቢያዎች አካተዋል።
#መንገድ #ኢትዮጵያ
👍7❤1
በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ ከግብጽ ጉቦ የተቀበሉት ሴናተር በ11 ዓመት እስራት ተቀጡ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ የግብፅን ጥቅም ለማስጠበቅ ጉቦ የተቀበሉት የቀድሞው የኒው ጀርዚ ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የ11 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል።
ሌላ ሀገርን በመርዳት 16 ክሶች የቀረቡባቸው ሜንዴዝ፣ ቢያንስ 15 ዓመታት ሊያስፈርድባቸው እንደሚገባ ተገልጿል።
በተለይ ከግብፅ መንግሥት የተቀበሏቸው ጥፍጥፍ ወርቆች፣ ጥሬ ገንዘብና መርሴዲስ ቤንዝ መኪና ለወንጀላቸው ማረጋገጫ ተደርገው ለፍርድ ቤት በማሰረጃነት መቅረባቸውን የሮይተርስ ዘገባ ያመላክታል።
ሜንዴዝ በጠበቃቸው በኩል ቀለል ያለ የማኅበራዊ አገልግሎት ቅጣት ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ ጥያቄያውን አልተቀበለውም።
በፈረንጆቹ 2020 ላይ የወቅቱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጫና አድርገው እንደነበር አይዘነጋም።
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን የወቅቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ውይይት ወደ ዋሸንግተን እንዲመጣ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡
ሜኔንዴዝ ዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤትን ከመቀላቀላቸው በፊት የኒው ጀርሲዋ ዩኒየን ሲቲን በከንቲባነት መርተዋል፡፡
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
#የዓባይ_ግድብ #የሁለትዮሽ_ድርድር #ኢትዮጵያ #ግብፅ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ የግብፅን ጥቅም ለማስጠበቅ ጉቦ የተቀበሉት የቀድሞው የኒው ጀርዚ ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የ11 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል።
ሌላ ሀገርን በመርዳት 16 ክሶች የቀረቡባቸው ሜንዴዝ፣ ቢያንስ 15 ዓመታት ሊያስፈርድባቸው እንደሚገባ ተገልጿል።
በተለይ ከግብፅ መንግሥት የተቀበሏቸው ጥፍጥፍ ወርቆች፣ ጥሬ ገንዘብና መርሴዲስ ቤንዝ መኪና ለወንጀላቸው ማረጋገጫ ተደርገው ለፍርድ ቤት በማሰረጃነት መቅረባቸውን የሮይተርስ ዘገባ ያመላክታል።
ሜንዴዝ በጠበቃቸው በኩል ቀለል ያለ የማኅበራዊ አገልግሎት ቅጣት ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ ጥያቄያውን አልተቀበለውም።
በፈረንጆቹ 2020 ላይ የወቅቱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጫና አድርገው እንደነበር አይዘነጋም።
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን የወቅቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ውይይት ወደ ዋሸንግተን እንዲመጣ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡
ሜኔንዴዝ ዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤትን ከመቀላቀላቸው በፊት የኒው ጀርሲዋ ዩኒየን ሲቲን በከንቲባነት መርተዋል፡፡
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
#የዓባይ_ግድብ #የሁለትዮሽ_ድርድር #ኢትዮጵያ #ግብፅ
👍14❤3
የአየር ወለድ ትምህርት ቤት የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላትን በአየር ወለድነት አሰልጥኖ አስመረቀ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር ሠልጣኞችን በአየር ወለድነት አሰልጥኖ አስመርቋል።
የኮማዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ለተመራቂ የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላት የአየር ወለድ ልዩ ምልክት የሆነውን የደረት ክንፍ አልብሰዋል።
የአየር ወለድ ስልጠና የወሰዱት የክፍሉ አባላት ቀደም ብለው እጅግ ፈታኝና ውስብስብ የሆነ የልዩ ሀይል ፀረ- ሽብር ስልጠናን መውሰዳቸውን አስታውሰው የክፍሉ አባላት የአየር ወለድ ስልጠናን በተጨማሪነት መሰልጠን አስፈላጊና ወሳኝ በመሆኑ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላት በግልም ሆነ በቡድን የሚሰጣቸውን ውስብስብና ልዩ ግዳጅ ለመወጣ የሚያስችላቸው አቅም እንዲኖራቸው ተደርገው በላቀ ደረጃ መሰልጠናቸውን የገለፁት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ተመራቂዎችም የሀገሪቷ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የዜጎቿን ህይወት የመቀየር ልማታዊ ጉዞ እንዳይደናቀፍ የተዘጋጁበትን ልዩ ግዳጅ በፍፁም ዲሲፕሊንና ፅናት ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
አዛዡ ዕዙና ተቋሙ የትምህርት ቤቱን አቅም ለመገንባት በርካታ ስራዎችን መስራታቸውን በማስታወስ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት በዚሁ ደረጃ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በብቃት እየተወጣ የሚገኝ በመሆኑ ለተገኘው ውጤት ያለእረፍት ለተጉት አሰልጣኞች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ በበኩላቸው የአየር ወለድ ትምህርት ቤት በማዕከሉ ስር ከሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ መሆኑን በመግለፅ ትምህርት ቤቱም ራሱን በማብቃት ተቋሙ በሀገር ላይ በየትኛውም ወቅት እና ቦታ የሚቃጣን ጥቃት ለመመከት ለልዩ ግዳጅ የሚፈልገውን የሰው ሀይል በላቀ ቴክኖሎጂ እያሰለጠነ እና እያበቃ የሚገኝ ሥለመሆኑ አስገንዝበዋል፡፡
የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የአየር ወለድ ትምህርት ቤት አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ፀጋዬ ካሱ ትምህርት ቤቱ ተመራቂ የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላትን በልዩ ሁኔታ በጥራት በማሰልጠን የሚፈለገውን አቅም እንዲገነቡ ማደረጉን ገልፀው ለስልጠናው ስኬት የአሰልጣኙ ሀገራዊ ፍቅርና አንድነት የጎላ አስተዋፅኦ ነበረው ማለታቸውን ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመለክታል።
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር ሠልጣኞችን በአየር ወለድነት አሰልጥኖ አስመርቋል።
የኮማዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ለተመራቂ የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላት የአየር ወለድ ልዩ ምልክት የሆነውን የደረት ክንፍ አልብሰዋል።
የአየር ወለድ ስልጠና የወሰዱት የክፍሉ አባላት ቀደም ብለው እጅግ ፈታኝና ውስብስብ የሆነ የልዩ ሀይል ፀረ- ሽብር ስልጠናን መውሰዳቸውን አስታውሰው የክፍሉ አባላት የአየር ወለድ ስልጠናን በተጨማሪነት መሰልጠን አስፈላጊና ወሳኝ በመሆኑ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላት በግልም ሆነ በቡድን የሚሰጣቸውን ውስብስብና ልዩ ግዳጅ ለመወጣ የሚያስችላቸው አቅም እንዲኖራቸው ተደርገው በላቀ ደረጃ መሰልጠናቸውን የገለፁት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ተመራቂዎችም የሀገሪቷ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የዜጎቿን ህይወት የመቀየር ልማታዊ ጉዞ እንዳይደናቀፍ የተዘጋጁበትን ልዩ ግዳጅ በፍፁም ዲሲፕሊንና ፅናት ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
አዛዡ ዕዙና ተቋሙ የትምህርት ቤቱን አቅም ለመገንባት በርካታ ስራዎችን መስራታቸውን በማስታወስ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት በዚሁ ደረጃ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በብቃት እየተወጣ የሚገኝ በመሆኑ ለተገኘው ውጤት ያለእረፍት ለተጉት አሰልጣኞች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ በበኩላቸው የአየር ወለድ ትምህርት ቤት በማዕከሉ ስር ከሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ መሆኑን በመግለፅ ትምህርት ቤቱም ራሱን በማብቃት ተቋሙ በሀገር ላይ በየትኛውም ወቅት እና ቦታ የሚቃጣን ጥቃት ለመመከት ለልዩ ግዳጅ የሚፈልገውን የሰው ሀይል በላቀ ቴክኖሎጂ እያሰለጠነ እና እያበቃ የሚገኝ ሥለመሆኑ አስገንዝበዋል፡፡
የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የአየር ወለድ ትምህርት ቤት አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ፀጋዬ ካሱ ትምህርት ቤቱ ተመራቂ የልዩ ሀይል ፀረ-ሽብር አባላትን በልዩ ሁኔታ በጥራት በማሰልጠን የሚፈለገውን አቅም እንዲገነቡ ማደረጉን ገልፀው ለስልጠናው ስኬት የአሰልጣኙ ሀገራዊ ፍቅርና አንድነት የጎላ አስተዋፅኦ ነበረው ማለታቸውን ኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመለክታል።
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
👍5❤2👏1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍7
ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር የሚያሰችል አዋጅ ፀደቀ
****
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል።
የአዋጁ መፅደቅ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል።
የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ለምክርቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለፁት፣ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍን መሠረት አድርገው ከተቀረጹ መርሐግብሮችና ዕቅዶች አንጻር ትምህርትን ለመምራት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ አላደገም።
ይህንን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት አዲስ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። አዋጁ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚደረገውን ሪፎርም ያግዛል።
በአዋጁ ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር እንዲችሉ ተደርጎ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።
አዋጁ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር ይረዳል ያሉት ሰብሳቢው፣ በመላው ሀገሪቱ ሁሉም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት የሀገሪቱን እሴት ጠብቆ እንዲካሄድ ግልጽ አቅጣጫ የሚሰጥ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
በክብረአብ በላቸው
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል።
የአዋጁ መፅደቅ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል።
የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ለምክርቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለፁት፣ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍን መሠረት አድርገው ከተቀረጹ መርሐግብሮችና ዕቅዶች አንጻር ትምህርትን ለመምራት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ አላደገም።
ይህንን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት አዲስ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። አዋጁ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚደረገውን ሪፎርም ያግዛል።
በአዋጁ ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር እንዲችሉ ተደርጎ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።
አዋጁ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር ይረዳል ያሉት ሰብሳቢው፣ በመላው ሀገሪቱ ሁሉም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት የሀገሪቱን እሴት ጠብቆ እንዲካሄድ ግልጽ አቅጣጫ የሚሰጥ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
በክብረአብ በላቸው
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
👍8
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ 56 ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል
*******
(ኢ ፕ ድ)
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ 56 ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ።
በአዲስ አበባ የተሰሩት የልማት ስራዎች የሀሳብ፣ የአመራር፣ የህብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ ድምር ውጤት ናቸው ብለዋል
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ብልጽግና ፓርቲ በአንደኛ ጠቅላለ ጉባኤው ለመተግበር ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ወደተግባር መቀየራቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ተመልክተናል ብለዋል።
በአዲስ አበባ ተጀምሮ ተጨባጭ ውጤት ካስገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ተሞክሮ በመውሰድ ወደሌሎች ከተሞች በማስፋት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የከተሞቹን ገጽታ በመቀየርና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ጉልህ ሚና አበርክቷል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ህዝብና በርካታ ጸጋዎች ያሏት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ ለሀገሪቱ የሚያስፈልጋት አዳዲስ ቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን ያላትን ሀብት አቧራውን በማራገፍ መግለጥ ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
በሄለን ወንድምነው
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ 56 ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ።
በአዲስ አበባ የተሰሩት የልማት ስራዎች የሀሳብ፣ የአመራር፣ የህብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ ድምር ውጤት ናቸው ብለዋል
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ብልጽግና ፓርቲ በአንደኛ ጠቅላለ ጉባኤው ለመተግበር ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ወደተግባር መቀየራቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ተመልክተናል ብለዋል።
በአዲስ አበባ ተጀምሮ ተጨባጭ ውጤት ካስገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ተሞክሮ በመውሰድ ወደሌሎች ከተሞች በማስፋት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የከተሞቹን ገጽታ በመቀየርና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ጉልህ ሚና አበርክቷል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ህዝብና በርካታ ጸጋዎች ያሏት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ ለሀገሪቱ የሚያስፈልጋት አዳዲስ ቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን ያላትን ሀብት አቧራውን በማራገፍ መግለጥ ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
በሄለን ወንድምነው
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
👍6
ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ‼️
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በደረሰው የአውሮፕላን አደጋ የተሰማውን ሀዘን ገለፀ።
ለአሜሪካ መንግሥትና ሕዝብ ያለውን አጋርነት በመግለፅ በአደጋው ለተጎዱ ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝቷል።
በአሜሪካ 64 ሰዎችን ይዞ ሲበር የነበረ የመንገደኞች አውሮፕላን በሮናልድ ሬገን አየር ማረፊያ ለማረፍ ሲቃረብ አራት የበረራ አባላትን ከያዘ የጦር ሄሊኮብተር ጋር ተጋጭቶ መከስከሱ መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በደረሰው የአውሮፕላን አደጋ የተሰማውን ሀዘን ገለፀ።
ለአሜሪካ መንግሥትና ሕዝብ ያለውን አጋርነት በመግለፅ በአደጋው ለተጎዱ ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝቷል።
በአሜሪካ 64 ሰዎችን ይዞ ሲበር የነበረ የመንገደኞች አውሮፕላን በሮናልድ ሬገን አየር ማረፊያ ለማረፍ ሲቃረብ አራት የበረራ አባላትን ከያዘ የጦር ሄሊኮብተር ጋር ተጋጭቶ መከስከሱ መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
😁13😢5👍2
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2017 ዓም መካሄድ ይጀምራል
*******
(ኢ ፕ ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከዛሬ ጥር 23 ቀን ጀምሮ እስከ 25 ቀን 2017 ዓም ድረስ 'ከቃል እስከ ባህል' በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በጉባኤው ለመሳተፍ፤
👉 የሩሲያው ዩናይትድ ራሺያ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዲ.ኤ ሜዴቭዴቭ፣
👉 የደቡብ አፍሪካው አፍሪካ ናሽናል ኮንግረንስ ፓርቲ የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ኖጦሉ ኪይቬት፣
👉 የካዛኪስታን አማናት ፓርቲ እና የሀገሪቱ ፓርላማ የታችኛው ምክር ቤት አባል ሳማት ኑር ታተዛ፣
👉 የኩባው ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሜቴ አባል ዩዲ ሜርሴዲስ ኸርናንዴዝ
👉 የቱርኬሚስታን ዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪ አታ ሰርዳሮቭ እና በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛዉ ምስራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ያዝጉሊ ማምዶቭ በጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
እንግዶቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በጉባዔው ላይ የጎረቤት ሀገራት እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ይታደማሉ ተብሏል።
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በማርቆስ በላይ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከዛሬ ጥር 23 ቀን ጀምሮ እስከ 25 ቀን 2017 ዓም ድረስ 'ከቃል እስከ ባህል' በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በጉባኤው ለመሳተፍ፤
👉 የሩሲያው ዩናይትድ ራሺያ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዲ.ኤ ሜዴቭዴቭ፣
👉 የደቡብ አፍሪካው አፍሪካ ናሽናል ኮንግረንስ ፓርቲ የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ኖጦሉ ኪይቬት፣
👉 የካዛኪስታን አማናት ፓርቲ እና የሀገሪቱ ፓርላማ የታችኛው ምክር ቤት አባል ሳማት ኑር ታተዛ፣
👉 የኩባው ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሜቴ አባል ዩዲ ሜርሴዲስ ኸርናንዴዝ
👉 የቱርኬሚስታን ዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪ አታ ሰርዳሮቭ እና በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛዉ ምስራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ያዝጉሊ ማምዶቭ በጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
እንግዶቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በጉባዔው ላይ የጎረቤት ሀገራት እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ይታደማሉ ተብሏል።
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በማርቆስ በላይ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
❤5👍5👏1