Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍7
ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር የሚያሰችል አዋጅ ፀደቀ
****
(ኢ ፕ ድ)
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል።

የአዋጁ መፅደቅ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል።

የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ለምክርቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለፁት፣ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍን መሠረት አድርገው ከተቀረጹ መርሐግብሮችና ዕቅዶች አንጻር ትምህርትን ለመምራት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ አላደገም።

ይህንን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት አዲስ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። አዋጁ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚደረገውን ሪፎርም ያግዛል።

በአዋጁ ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር እንዲችሉ ተደርጎ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።

አዋጁ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር ይረዳል ያሉት ሰብሳቢው፣ በመላው ሀገሪቱ ሁሉም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት የሀገሪቱን እሴት ጠብቆ እንዲካሄድ ግልጽ አቅጣጫ የሚሰጥ ስለመሆኑ አስረድተዋል።

በክብረአብ በላቸው

ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
👍8
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ገበታ_ለትውልድ_በጅማ

በጅማ የቦዬ ሀይቅን መልሶ እንዲያገግም የተሰራበት እና በአረንጓዴ የተሸፈነው ፕሮጀክት‼️
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ 56 ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ይገኛል
*******
(ኢ ፕ ድ)

በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ 56 ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ።

በአዲስ አበባ የተሰሩት የልማት ስራዎች የሀሳብ፣ የአመራር፣ የህብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ ድምር ውጤት ናቸው ብለዋል

የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ብልጽግና ፓርቲ በአንደኛ ጠቅላለ ጉባኤው ለመተግበር ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ወደተግባር መቀየራቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ተመልክተናል ብለዋል።

በአዲስ አበባ ተጀምሮ ተጨባጭ ውጤት ካስገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ተሞክሮ በመውሰድ ወደሌሎች ከተሞች በማስፋት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የከተሞቹን ገጽታ በመቀየርና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ጉልህ ሚና አበርክቷል።

ኢትዮጵያ ትልቅ ህዝብና በርካታ ጸጋዎች ያሏት ሀገር መሆኗን ገልጸው፤ ለሀገሪቱ የሚያስፈልጋት አዳዲስ ቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን ያላትን ሀብት አቧራውን በማራገፍ መግለጥ ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

በሄለን ወንድምነው

ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
👍6
ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ‼️

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በደረሰው የአውሮፕላን አደጋ የተሰማውን ሀዘን ገለፀ።

ለአሜሪካ መንግሥትና ሕዝብ ያለውን አጋርነት በመግለፅ በአደጋው ለተጎዱ ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝቷል።

በአሜሪካ 64 ሰዎችን ይዞ ሲበር የነበረ የመንገደኞች አውሮፕላን በሮናልድ ሬገን አየር ማረፊያ ለማረፍ ሲቃረብ አራት የበረራ አባላትን ከያዘ የጦር ሄሊኮብተር ጋር ተጋጭቶ መከስከሱ መረጃዎች ያመላክታሉ።

ጥር 22 ቀን 2017 ዓም
😁13😢5👍2
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2017 ዓም መካሄድ ይጀምራል
*******
(ኢ ፕ ድ)

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከዛሬ ጥር 23 ቀን ጀምሮ እስከ 25 ቀን 2017 ዓም ድረስ 'ከቃል እስከ ባህል' በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በጉባኤው ለመሳተፍ፤

👉 የሩሲያው ዩናይትድ ራሺያ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዲ.ኤ ሜዴቭዴቭ፣

👉 የደቡብ አፍሪካው አፍሪካ ናሽናል ኮንግረንስ ፓርቲ የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ኖጦሉ ኪይቬት፣

👉 የካዛኪስታን አማናት ፓርቲ እና የሀገሪቱ ፓርላማ የታችኛው ምክር ቤት አባል ሳማት ኑር ታተዛ፣

👉 የኩባው ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሜቴ አባል ዩዲ ሜርሴዲስ ኸርናንዴዝ

👉 የቱርኬሚስታን ዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪ አታ ሰርዳሮቭ እና በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛዉ ምስራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ያዝጉሊ ማምዶቭ በጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

እንግዶቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በጉባዔው ላይ የጎረቤት ሀገራት እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ይታደማሉ ተብሏል።

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በማርቆስ በላይ

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
5👍5👏1
ከባህርና ደረቅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከ46 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል
*****
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለፋት ስድስት ወራት ከባህርና ደረቅ ትራንስፖርት አገልግሎት 46 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ። 9 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብርም ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልጻል።

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር)፣ በሰጡት ማብራሪያ፤ በባለፉት ስድስት ወራት ከባህርና ደረቅ ትራንስፖርት አገልግሎት 44 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 46 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል።

በግማሽ አመቱ 6 ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ትርፍ ለማግኘት ታቅዶ 9 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ተገኝቷል።

ድርጅቱ በባህርና በደረቅ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፤ አገልግሎቱን በዲጅታል የማዘመን ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ደርጅቱ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ሰራዎች እየተሰሩ ነው ሲሉ ጠቁመዋል።

በታደሠ ብናልፈው

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
4
"የአገው ፈረሰኞች #የኢትዮጵያን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ታላቅ ሚና ነበራቸው። ለዚህም #የዓድዋ ዘመቻ ተሳትፏቸው ጉልሕ ምስክር ነው። ዛሬም የአባቶቻቸውን ፈለግ በመከተል ሰላምንና ጸጥታን በማስከበር ተገቢውን ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። ዛሬ የሚከበረው በዓል፣ ፈረሰኞቻችንና ፈረሶቻችን የሰላምና የልማት ዘብ መሆናቸውን ለትውልድ የሚመሰክሩበት እንደሚሆን አምናለሁ"

- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👏1
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍31🥰1