"የአንጎላ ፕሬዝዳንት ማኑኤል ጎንካልቬስ ሎሬንቾን ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ እላለሁ። ውይይታችን የሁለትዮሽ ጉዳዮችን ለመዳሰስ እንዲሁም ክቡር ፕሬዝደንቱ በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነታቸው ቁልፍ አኅጉራዊና ባለ ብዙወገን ጉዳዮችን ለመመልከት ችለናል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
👍1
ኢትዮጵያና ሩዋንዳ በወታደራዊ ዘርፍ በትብብር ለመስራት ተፈራረሙ
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ሩዋንዳ በተለያዩ ወታደራዊ መስኮች በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የሩዋንዳ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ ተፈራርመዋል።
የመከላከያ ውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ ኢትዮጵያና ሩዋንዳ በልዩ ልዩ ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለረጅም ዓመታት ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
አሁን ላይ የነበረውን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸውም ተገልጿል።
በወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና፣ በተሞክሮ ልውውጥ፣ ሽብርተኝነትን በመከላከል እና በሌሎች ተያያዥ ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል።
በሩዋንዳ መከላከያ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄነራል ብርጋዲየር ጄኔራል ፓትሪክ ካሪታዋ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ሩዋንዳ ረጅም ጊዜያትን ያስቆጠረ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰዋል።
ኢትዮጵያ በችግራችን ጊዜ ፈጥና የደረሰችልን ሀገር ነች ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራሉ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ ጉዳዮች ያለንን ግንኙነት አጠናክረን እንቀጥላለን ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ሩዋንዳ በተለያዩ ወታደራዊ መስኮች በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የሩዋንዳ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ ተፈራርመዋል።
የመከላከያ ውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ ኢትዮጵያና ሩዋንዳ በልዩ ልዩ ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለረጅም ዓመታት ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
አሁን ላይ የነበረውን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸውም ተገልጿል።
በወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና፣ በተሞክሮ ልውውጥ፣ ሽብርተኝነትን በመከላከል እና በሌሎች ተያያዥ ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል።
በሩዋንዳ መከላከያ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄነራል ብርጋዲየር ጄኔራል ፓትሪክ ካሪታዋ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ሩዋንዳ ረጅም ጊዜያትን ያስቆጠረ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰዋል።
ኢትዮጵያ በችግራችን ጊዜ ፈጥና የደረሰችልን ሀገር ነች ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራሉ ከኢትዮጵያ ጋር በወታደራዊ ጉዳዮች ያለንን ግንኙነት አጠናክረን እንቀጥላለን ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
👍4👏1
ኢትዮጵያና ኩባ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር ለመሥራት የመግባቢያ ስምምነቶች ተፈራረሙ
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ኩባ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መሥራት የሚያስችሏቸውን የመግባቢያ ስምምነቶች ተፈራርመዋል።
ሁለቱ ሀገራት በባህል፣ በስፖርት፣ በቴክኖሎጂ፣ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፎች በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ከኩባ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ኤድዋርዶ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ጋር የባህል ዘርፍ ትብብርን ለማጠናከር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመዋል።
ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) እና በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር መይሊን ሱዋሬዝ አልቫሬዝ ፈርመውታል።
የኩባ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ኤድዋርዶ ሮድሪጌዝ ፓሪላ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን ገልጸዋል። የሁለቱ ሀገራት የረጅም ዘመናት ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የኩባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡሩኖ ኤድዋርዶ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ እና ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸው ኢዜአ ዘግቧል።
የኢትዮጵያና ኩባ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመረው እ.አ.አ ከ1975 ጀምሮ መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ኩባ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መሥራት የሚያስችሏቸውን የመግባቢያ ስምምነቶች ተፈራርመዋል።
ሁለቱ ሀገራት በባህል፣ በስፖርት፣ በቴክኖሎጂ፣ ኢነርጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፎች በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ከኩባ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ኤድዋርዶ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ጋር የባህል ዘርፍ ትብብርን ለማጠናከር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመዋል።
ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) እና በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር መይሊን ሱዋሬዝ አልቫሬዝ ፈርመውታል።
የኩባ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ኤድዋርዶ ሮድሪጌዝ ፓሪላ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውን ገልጸዋል። የሁለቱ ሀገራት የረጅም ዘመናት ግንኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የኩባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡሩኖ ኤድዋርዶ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ እና ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸው ኢዜአ ዘግቧል።
የኢትዮጵያና ኩባ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመረው እ.አ.አ ከ1975 ጀምሮ መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
👍3❤2👏2🥰1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአንጎላ ፕሬዝዳንት ጆኣኦ ማኑኤል ጎንካልቬስ ሎሬንቾን ጋር የነበራቸው ቆይታ‼️
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓም
👍6❤2👏2
👍2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
✍️ ማንኛውም ጎረቤት በኃይማኖት አይለይም፣
✍️ እንዴት ለካህኑ አዛን ናፈቃቸው፣
✍️ ዓዛን ካልሰማን ዛሬ ዓዛን ያልተደረገበት ምክንያት ምንድነው የሚለው እኔን ይጨንቀኛል፣ ሙስሊሙ እንደዛው፣
✍️ ዛሬ ቅዳሴ የለም ብለው ይጠይቃሉ፣
👉 የአብሮነትና የሰላም ምድር ከተሰኘ ዘጋቢ ፊልም የተወሰደ https://youtu.be/EefsdA9mZvE?feature
#አብሮነት #ስለኢትዮጵያ #ዓዛን #ቅዳሴ
✍️ እንዴት ለካህኑ አዛን ናፈቃቸው፣
✍️ ዓዛን ካልሰማን ዛሬ ዓዛን ያልተደረገበት ምክንያት ምንድነው የሚለው እኔን ይጨንቀኛል፣ ሙስሊሙ እንደዛው፣
✍️ ዛሬ ቅዳሴ የለም ብለው ይጠይቃሉ፣
👉 የአብሮነትና የሰላም ምድር ከተሰኘ ዘጋቢ ፊልም የተወሰደ https://youtu.be/EefsdA9mZvE?feature
#አብሮነት #ስለኢትዮጵያ #ዓዛን #ቅዳሴ
👍2👏1
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ማክሸፍ አስችሏል
- አቶ ይርጋ ሲሳይ
****
(ኢ ፕ ድ)
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው በመርሕ ላይ የተመሰረተ አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ለማክሸፍ አስችሏል ሲሉ በፓርቲው የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ገለጹ፡፡
በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩና አካባቢውን ለማተራመስ ሲጥሩ በነበሩ ፀረ-ሰላም ቡድኖች በርካታ ፈተናዎችን ሲያስተናግድ መቆየቱን ጠቁመዋል።
በሕዝቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ክልሉ አስደናቂ ለውጦችን እውን ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
- አቶ ይርጋ ሲሳይ
****
(ኢ ፕ ድ)
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው በመርሕ ላይ የተመሰረተ አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ለማክሸፍ አስችሏል ሲሉ በፓርቲው የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ገለጹ፡፡
በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩና አካባቢውን ለማተራመስ ሲጥሩ በነበሩ ፀረ-ሰላም ቡድኖች በርካታ ፈተናዎችን ሲያስተናግድ መቆየቱን ጠቁመዋል።
በሕዝቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ክልሉ አስደናቂ ለውጦችን እውን ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
👍7
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👏2👍1
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ማክሸፍ አስችሏል - አቶ ይርጋ ሲሳይ **** (ኢ ፕ ድ) ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው በመርሕ ላይ የተመሰረተ አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ለማክሸፍ አስችሏል ሲሉ በፓርቲው የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ገለጹ፡፡ በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩና አካባቢውን ለማተራመስ ሲጥሩ በነበሩ ፀረ…
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ማክሸፍ አስችሏል - አቶ ይርጋ ሲሳይ
****
(ኢ ፕ ድ)
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው በመርሕ ላይ የተመሰረተ አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ለማክሸፍ አስችሏል ሲሉ በፓርቲው የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ገለጹ፡፡
በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩና አካባቢውን ለማተራመስ ሲጥሩ በነበሩ ፀረ-ሰላም ቡድኖች በርካታ ፈተናዎችን ሲያስተናግድ መቆየቱን ጠቁመዋል።
በሕዝቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ክልሉ አስደናቂ ለውጦችን እውን ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የለውጡ አመራር የሚከተላቸው ሀገራዊ አንድነትን ማዕከል ያደረጉ፣ ፖለቲካዊ ልዩነቶችን በውይይት የመፍታት እና ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ልማትን እውን የማድረግ መርሆዎች ውጤት አስመዝግበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሁሉም ማዕዘናት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ያለው ቁርጠኛ አቋም ፍሬዎች መታየት መጀመራቸው የፓርቲውን እሳቤዎችና ሀገራዊ ራዕይ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ማስቻሉን አንስተዋል፡፡
የፓርቲው ጥረት በአማራ ክልል ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገቡን ጠቁመው÷ የክልሉን ሰላምና የሕዝቡን ደህንነት ለአደጋ አጋልጠው የቆዩትን ፀረ-ሰላም ቡድኖች እውነተኛ ማንነትና ዓላማ ሕዝብ እንዲገነዘብ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ፀረ-ሰላም ቡድኖቹ በከፍተኛ ሁኔታ ተዳክመው ወደማይቀረው የክስመት ደረጃ ላይ ደርሰዋል መድረሳቸውን ያመላከቱት አቶ ይርጋ ሲሳይ ፓርቲው ከምሥረታው ጀምሮ ዘላቂ ሰላምን እውን ማድረግ ቅድሚያ የሚሰጠው አጀንዳዉ አድርጎ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
የማህበረሰብ ውይይትን በስፋት በማካሄድ፣ ከታሪክ የተወረሱ ሀገራዊ የትርክት ቅራኔዎችን ለመፍታት በመስራትና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማምጣት የሚያስችሉ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውንም አንስተዋል፡፡
ሁሉን አቀፍ፣ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሰራ መቆየቱን አብራርተዋል።
በመከላከያ ሰራዊት፣ የፌዴራልና የክልል መንግስታትና የፀጥታ ሃይሎች የተቀናጀ ጥረትም የፀረ-ሰላም ቡድኖች ተጽእኖ በእጅጉ መቀነሱን አንስተዋል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ችግሩን ለመፍታት መሰረታዊ የማህበረሰብ ተሳትፎን በማበረታታቱና በሕዝብ ባለቤትነት በሚመራ ስልት ላይ ትኩረት በማድረጉ የፅንፈኛ ቡድኖችን አጀንዳዎችና ዓላማ በማክሸፍ ዜጎች በጋራ ሆነው በሰላም ዙሪያ እንዲሰባሰቡ በማድረግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የፓርቲው መረጃ ያመላክታል፡፡
መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ብልጽግና ፓርቲ የተከተለው በመርሕ ላይ የተመሰረተ አካሄድ የጸረ ሰላም ቡድኖችን ዓላማና ሕልውና ለማክሸፍ አስችሏል ሲሉ በፓርቲው የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ ገለጹ፡፡
በአማራ ክልል ሲንቀሳቀሱ የነበሩና አካባቢውን ለማተራመስ ሲጥሩ በነበሩ ፀረ-ሰላም ቡድኖች በርካታ ፈተናዎችን ሲያስተናግድ መቆየቱን ጠቁመዋል።
በሕዝቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ክልሉ አስደናቂ ለውጦችን እውን ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የለውጡ አመራር የሚከተላቸው ሀገራዊ አንድነትን ማዕከል ያደረጉ፣ ፖለቲካዊ ልዩነቶችን በውይይት የመፍታት እና ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚያዊ ልማትን እውን የማድረግ መርሆዎች ውጤት አስመዝግበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሁሉም ማዕዘናት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ያለው ቁርጠኛ አቋም ፍሬዎች መታየት መጀመራቸው የፓርቲውን እሳቤዎችና ሀገራዊ ራዕይ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ማስቻሉን አንስተዋል፡፡
የፓርቲው ጥረት በአማራ ክልል ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገቡን ጠቁመው÷ የክልሉን ሰላምና የሕዝቡን ደህንነት ለአደጋ አጋልጠው የቆዩትን ፀረ-ሰላም ቡድኖች እውነተኛ ማንነትና ዓላማ ሕዝብ እንዲገነዘብ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ፀረ-ሰላም ቡድኖቹ በከፍተኛ ሁኔታ ተዳክመው ወደማይቀረው የክስመት ደረጃ ላይ ደርሰዋል መድረሳቸውን ያመላከቱት አቶ ይርጋ ሲሳይ ፓርቲው ከምሥረታው ጀምሮ ዘላቂ ሰላምን እውን ማድረግ ቅድሚያ የሚሰጠው አጀንዳዉ አድርጎ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
የማህበረሰብ ውይይትን በስፋት በማካሄድ፣ ከታሪክ የተወረሱ ሀገራዊ የትርክት ቅራኔዎችን ለመፍታት በመስራትና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማምጣት የሚያስችሉ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውንም አንስተዋል፡፡
ሁሉን አቀፍ፣ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ሲሰራ መቆየቱን አብራርተዋል።
በመከላከያ ሰራዊት፣ የፌዴራልና የክልል መንግስታትና የፀጥታ ሃይሎች የተቀናጀ ጥረትም የፀረ-ሰላም ቡድኖች ተጽእኖ በእጅጉ መቀነሱን አንስተዋል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ችግሩን ለመፍታት መሰረታዊ የማህበረሰብ ተሳትፎን በማበረታታቱና በሕዝብ ባለቤትነት በሚመራ ስልት ላይ ትኩረት በማድረጉ የፅንፈኛ ቡድኖችን አጀንዳዎችና ዓላማ በማክሸፍ ዜጎች በጋራ ሆነው በሰላም ዙሪያ እንዲሰባሰቡ በማድረግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የፓርቲው መረጃ ያመላክታል፡፡
መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓም
👍9
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኅብረት ልዩ የማኅበረሰብ ጤና ተቋም የሆነውን የአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል መቀመጫ በመሆኗ ክብር ይሰማታል።
በማዕከሉ ያሉት ላቦራቶሪዎችና የምርምር አቅሞች በበሽታ መቆጣጠር ብሎም በወረርሽኞችና ተላላፊ በሽታዎች ምላሽ በመስጠት ሥራ ከፍ ያለ ሚና ይጫወታሉ። ይኽ እድል ለሀገራችን የጤናው ዘርፍ ተመራማሪዎችና ባለሞያዎች በአኅጉራዊ የምርምር ጥረቶች በመሳተፍ በዘመናዊ ላብራቶሪዎች እንዲጠቀሙም መንገድ ይከፍታል።
አባል ሀገራት ከአጋሮች ጋር በመተባበር ይኽን ተቋም ማጠናከር ይገባናል። በመሆኑም የአፍሪካ መሪዎች አኅጉራዊ የማኅበረሰብ ጤና ተቋማችን በመላው አኅጉራችን የጤና አገልግሎት በማሳደግ ላይ ተቀዳሚ በማድረግ ሥራ ላይ በሙሉ ኃላፊነት እንድንተባበር ጥሪ አቀርባለሁ።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በማዕከሉ ያሉት ላቦራቶሪዎችና የምርምር አቅሞች በበሽታ መቆጣጠር ብሎም በወረርሽኞችና ተላላፊ በሽታዎች ምላሽ በመስጠት ሥራ ከፍ ያለ ሚና ይጫወታሉ። ይኽ እድል ለሀገራችን የጤናው ዘርፍ ተመራማሪዎችና ባለሞያዎች በአኅጉራዊ የምርምር ጥረቶች በመሳተፍ በዘመናዊ ላብራቶሪዎች እንዲጠቀሙም መንገድ ይከፍታል።
አባል ሀገራት ከአጋሮች ጋር በመተባበር ይኽን ተቋም ማጠናከር ይገባናል። በመሆኑም የአፍሪካ መሪዎች አኅጉራዊ የማኅበረሰብ ጤና ተቋማችን በመላው አኅጉራችን የጤና አገልግሎት በማሳደግ ላይ ተቀዳሚ በማድረግ ሥራ ላይ በሙሉ ኃላፊነት እንድንተባበር ጥሪ አቀርባለሁ።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
❤5👍3👏1🤔1
ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ አዲስ ለሚገነባው ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ
********
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሾፍቱ አቅራቢያ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚገነባው ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የፍላጎት መግለጫ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።
የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንዌሚ አዴሲና ለኢትዮጵያ ልዑክ አቀባበል አድርገዋል።
ልዑኩ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ያካተተ ነው።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ አቅራቢያ የሚገነባ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋል ተብሎም ይጠበቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓም
********
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሾፍቱ አቅራቢያ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚገነባው ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የፍላጎት መግለጫ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።
የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንዌሚ አዴሲና ለኢትዮጵያ ልዑክ አቀባበል አድርገዋል።
ልዑኩ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ያካተተ ነው።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ አቅራቢያ የሚገነባ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋል ተብሎም ይጠበቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓም
👍8👏2❤1