በ‘አዲስ ምዕራፍ” ፕሮግራም ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወሰደ
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ‘አዲስ ምዕራፍ’ በተሰኘ ፕሮግራም ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ፕሮግራሙ እሑድ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ያሰራጨውን ፕሮግራም ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና ከዘርፉ ሕጎች አንጻር መገምገሙን ገልጿል።
በዚሁ መሰረት በጣቢያው የቀረበው ፕሮግራም በሐሰተኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ሕዝብን የሚያሳስትና ጥርጣሬን የሚፈጥር፣ የመገናኛ ብዘኃን አዋጅ 1238/2013፣ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ 1185/2012 እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያ ስነ-ምግባርን፣ መደበኛ የጋዜጠኝነት አሰራርን የሚጥስ የፓራጆርናሊዝም አሰራርን የተከተለ ሆኖ ተገኝቷል ብሏል፡፡
ጣቢያውም በፕሮግራሙ ዙሪያ ተጠይቆ ለባለሥልጣኑ በሰጠው ምላሽ ያሰራጨው ፕሮግራም ሐሰተኛ መሆኑንና ስህተት መፈጸሙን ማረጋገጡን ባለሥልጣኑ ባወጣው መረጃ አመላክቷል።
ባለሥልጣኑ ጉዳዩን መርምሮ በጣቢያው የሚሰራጨው “አዲስ ምዕራፍ” የተሰኘ ፕሮግራም በኤዲቶሪያል አሰራሩ ላይ አስፈላጊውን እርምት ወስዶ ለባለሥልጣኑ እስኪያሳውቅና ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ፕሮግራሙ ከስርጭት ታግዶ እንዲቆይ መወሰኑን እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠ መሆኑን ገልጿል።
መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ‘አዲስ ምዕራፍ’ በተሰኘ ፕሮግራም ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ፕሮግራሙ እሑድ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ያሰራጨውን ፕሮግራም ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና ከዘርፉ ሕጎች አንጻር መገምገሙን ገልጿል።
በዚሁ መሰረት በጣቢያው የቀረበው ፕሮግራም በሐሰተኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ሕዝብን የሚያሳስትና ጥርጣሬን የሚፈጥር፣ የመገናኛ ብዘኃን አዋጅ 1238/2013፣ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ 1185/2012 እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያ ስነ-ምግባርን፣ መደበኛ የጋዜጠኝነት አሰራርን የሚጥስ የፓራጆርናሊዝም አሰራርን የተከተለ ሆኖ ተገኝቷል ብሏል፡፡
ጣቢያውም በፕሮግራሙ ዙሪያ ተጠይቆ ለባለሥልጣኑ በሰጠው ምላሽ ያሰራጨው ፕሮግራም ሐሰተኛ መሆኑንና ስህተት መፈጸሙን ማረጋገጡን ባለሥልጣኑ ባወጣው መረጃ አመላክቷል።
ባለሥልጣኑ ጉዳዩን መርምሮ በጣቢያው የሚሰራጨው “አዲስ ምዕራፍ” የተሰኘ ፕሮግራም በኤዲቶሪያል አሰራሩ ላይ አስፈላጊውን እርምት ወስዶ ለባለሥልጣኑ እስኪያሳውቅና ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ፕሮግራሙ ከስርጭት ታግዶ እንዲቆይ መወሰኑን እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠ መሆኑን ገልጿል።
መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓም
👍5❤1🥰1
የቁጭት መዝገብ ሊዘጋ የ’180′ ቀናት ዕድሜ ብቻ ቀሩት
****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያውያን በጋራ የተረባረቡበት፤ ዓለም አቀፍ ጫናን በውስጥ አቅም በብቃት የመከቱበት፤ ከኢትዮጵያ አልፎ የቀጣናውና የአፍሪካ ሀገራት ኩራት የሆነው የቁጭት መዝገብ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ታሪክ ሆኖ ሊቆምና ሕያውነቱም ሊበሰር 180 ቀናት ብቻ ቀርተውታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ ኩራት፣ የመላው አፍሪካ መቻል የታየበት፣ ስህተትም የታረመበት፣ ውስጣዊ ውድቀትም ጨከን ተብሎ የታረመበት 74 ቢሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውሃ የተያዘበትና ከፍተኛ የኃይል ምንጭ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
አፍሪካውያን ብድር ቢከለከሉ፣ የዲፕሎማሲ ጫና ቢደረግባቸው የራሳቸውን ሀብት በዜጎቻቸው ማልማትና መቀየር እንደሚችሉ በተግባር ያስተማሩበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ለምርቃቱ ስድስት ወራት ያስፈለገው ዝግጅት ስለሚያስፈልግና አካባቢው ሞቃታማ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የክረምት ዝናብ ስለሚያስፈልግ መሆኑን በማመልከትም፤ ግድቡ በቀጣዩ ዓመት መጀመሪያ ላይ ታሪክ ሆኖ የሚያልፍ ይሆናል ሲሉም አመልክተዋል።
የዓባይ ግድብ አንድ ብር ርዳታም ሆነ ብድር ከውጭ ሀገራት ሳይገኝ የተገነባ፣ ግንባታውም ብዙ ፈተና የታየበት እንደነበርም አስታውሰዋል። የገንዘቡ እና የውጭ ጫናው ሳያንስ ለግንባታው የሚውሉ ግብዓቶችን ከሁለት ወራት ተኩል ያላነሰ ከጅቡቲ ወደብ እስከ ዓባይ ግድብ ድረስ በፀጥታ ኃይሎች ታጅቦ ተጓጉዟል።
ከግብፅ ጋር በውይይት፣ በትብብርና በመደጋገፍ በጋራ መሥራት እንዳለብን እናምናለን፤ በጋራ ስንሠራ የሁለቱ ሀገራት ሕዝቦች ተጠቃሚ ይሆናሉ..... https://press.et/?p=147964
****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያውያን በጋራ የተረባረቡበት፤ ዓለም አቀፍ ጫናን በውስጥ አቅም በብቃት የመከቱበት፤ ከኢትዮጵያ አልፎ የቀጣናውና የአፍሪካ ሀገራት ኩራት የሆነው የቁጭት መዝገብ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ታሪክ ሆኖ ሊቆምና ሕያውነቱም ሊበሰር 180 ቀናት ብቻ ቀርተውታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ ኩራት፣ የመላው አፍሪካ መቻል የታየበት፣ ስህተትም የታረመበት፣ ውስጣዊ ውድቀትም ጨከን ተብሎ የታረመበት 74 ቢሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውሃ የተያዘበትና ከፍተኛ የኃይል ምንጭ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
አፍሪካውያን ብድር ቢከለከሉ፣ የዲፕሎማሲ ጫና ቢደረግባቸው የራሳቸውን ሀብት በዜጎቻቸው ማልማትና መቀየር እንደሚችሉ በተግባር ያስተማሩበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ለምርቃቱ ስድስት ወራት ያስፈለገው ዝግጅት ስለሚያስፈልግና አካባቢው ሞቃታማ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የክረምት ዝናብ ስለሚያስፈልግ መሆኑን በማመልከትም፤ ግድቡ በቀጣዩ ዓመት መጀመሪያ ላይ ታሪክ ሆኖ የሚያልፍ ይሆናል ሲሉም አመልክተዋል።
የዓባይ ግድብ አንድ ብር ርዳታም ሆነ ብድር ከውጭ ሀገራት ሳይገኝ የተገነባ፣ ግንባታውም ብዙ ፈተና የታየበት እንደነበርም አስታውሰዋል። የገንዘቡ እና የውጭ ጫናው ሳያንስ ለግንባታው የሚውሉ ግብዓቶችን ከሁለት ወራት ተኩል ያላነሰ ከጅቡቲ ወደብ እስከ ዓባይ ግድብ ድረስ በፀጥታ ኃይሎች ታጅቦ ተጓጉዟል።
ከግብፅ ጋር በውይይት፣ በትብብርና በመደጋገፍ በጋራ መሥራት እንዳለብን እናምናለን፤ በጋራ ስንሠራ የሁለቱ ሀገራት ሕዝቦች ተጠቃሚ ይሆናሉ..... https://press.et/?p=147964
👍23👏4😢1
በ600 ሺህ ብር አንድ ሺህ መጽሀፍትን በማሳተም 990ውን ለህዳሴ
*******
(ኢ ፕ ድ)
ዓባይ በኢትዮጵያውያን የድጋፍ ማዕበል ታጅቦ፣ በጠላት ዓይን እየተገለመጠ፣ ጉዞው ከተገታና በቤቱ ማደር ከጀመረ ዓመታትን አስቆጠሯል፡፡ በርካታ ተግዳሮቶችን በመሻገር የተስፋ ፍሬውን ለልጆቹ ማቅመስ ከጀመረም ሰነባብቷል።
እናቶች በመቀነታቸው ከቋጠሯት፤ ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እስከ ባለሀብት በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበትና በቴክኒካል ጉዳዮች ድጋፍ አድርገዋል። ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለግድቡ ግንባታ ያለማቋረጥ አለኝታነታቸውን አረጋግጠዋል።
አስቀናቸው ገብረየስ ይባላሉ፡፡ ግምታዊ ዋጋቸው 600 ሺህ ብር የሚሆን አንድ ሺህ መጽሀፍትን በማሳተም 990ውን መጽሃፍት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ብርሃን ለሆነው ለህዳሴው ግድብ በስጦታ አበርክተዋል።
በሙያቸው ኤሌክትሪካል ኢንጂነር ናቸው፡፡ #በአሜሪካን የቴክሳስን 90 በመቶ የኤሌክትሪክ ሃይል ድርሻ በሚሸፍንና ከ80 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ አቅም ባለው፣ ከ24 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች 99 ነጥብ 99 በመቶ ኤሌክትርክ እንዳይቋረጥ በሚሰራ ድርጅት ውስጥ ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል።
ምኞታቸው በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት እንዲስፋፋና አስተማማኝ ኃይል እንዲኖራት ነው።
ሀገሬ ላይ በገበየሁት እውቀት ውጭ ሀገር ሄጀ መስራት ችያለሁ የሚሉት ባለታሪካችን፤ ከሀገሬ ያገኘሁትን አቅሜ በፈቀደ መጠን መመለስ እንዳለብኝ በማሰብ በሀገረ አሜሪካ በስራ ላይ የማግኛቸውን ልምድና ተሞክሮዎች በማስታወሻ መመዝገብ የየዕለት ተግባሬ ሆኗል ይላሉ፡፡
ህልማቸው ዕውን ሆኖ "የሀገሬን ለሀገሬ!" በሚል ውጭ ሀገር በቆዩበት ወቅት ያገኙትን እውቀት ሰንደው፣ ግምታዊ
ዋጋቸው 600 ሺህ ብር የሚሆን አንድ ሺህ መጽሀፍትን በማሳተም 990ውን መጽሃፍት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ብርሃን የመሆን ስንቅን ይዞ እየተገነባ ላለው ለዓባይ ግድብ በስጦታ አበርክተዋል።
የዓባይ ግድብ በሚጠናቀቅበት ወቅት መጽሃፉ የባለድርሻ አካላት እጅ መግባቱ ወቅታዊና ታሪካዊ ነው ይላሉ፡፡
የአንድ ሀገር የኤሌክትሪካል ግሪድ ትስስርን፣ በሀገሮች የኤሌክትሪክ ግሪዶች መካከል ስለሚኖር ግንኙነትና ትስስር ትኩረት ሊሰጣቸው ስለሚገቡ አሰራሮች በመጽሃፋቸው በስፋት አስረድተዋል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከዓባይ ትሩፋቶች መካከል አንዱ በመሆኑ፤ ከግድቡ የሚመነጨው ኃይል ሳይቆራረጥና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም በቀጣናው የተጀመረውን የኃይል ትስስር ለማጠናክር መጽሃፉ ከፍተኛ አስትዋፅኦ ያበረክታል ይላሉ፡፡
መጽሀፉ ስለተለያዩ የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያዎች፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች፤ በመስመሮቹ ላይ የኤሌክትሪክ ብክነትን ስለመቆጣጠር በስፋት ተተንትኖበታል፡፡
በኤሌክትሪክ የማስተላለፊያና ማሰራጫ መስመሮች ዙሪያ ስለሚፈጠር የኃይል መተፋፈግና በኤሌክትሪክ ሃይል አጠቃቀምና ቁጥጥር ላይ ስለሚያስፈልጉ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎች አሰራርና አተገባበር በመጽሃፉ ተዘርዝሯል።
ሀገራት በመካከላቸው የኤሌክትሪክ ኃይልን ሲጋሩ ሊኖር ስለሚገባው አስፈላጊ ጥንቃቄም ያብራራል፡፡
መፅሀፉ "ዘመናዊነት ያለኤሌክትሪክ የሚታሰብ አይደለም"( Modernity Without Electricity Unthinkable) እንዲሁም "የኤሌክትሪክ ግሪድ አሰራር ("Foundational Concepts of Electric Grid Operations") በሚል ርዕሰ ጉዳይ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተዘጋጀ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡
በሄለን ወንድምነው
መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
ዓባይ በኢትዮጵያውያን የድጋፍ ማዕበል ታጅቦ፣ በጠላት ዓይን እየተገለመጠ፣ ጉዞው ከተገታና በቤቱ ማደር ከጀመረ ዓመታትን አስቆጠሯል፡፡ በርካታ ተግዳሮቶችን በመሻገር የተስፋ ፍሬውን ለልጆቹ ማቅመስ ከጀመረም ሰነባብቷል።
እናቶች በመቀነታቸው ከቋጠሯት፤ ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እስከ ባለሀብት በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበትና በቴክኒካል ጉዳዮች ድጋፍ አድርገዋል። ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለግድቡ ግንባታ ያለማቋረጥ አለኝታነታቸውን አረጋግጠዋል።
አስቀናቸው ገብረየስ ይባላሉ፡፡ ግምታዊ ዋጋቸው 600 ሺህ ብር የሚሆን አንድ ሺህ መጽሀፍትን በማሳተም 990ውን መጽሃፍት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ብርሃን ለሆነው ለህዳሴው ግድብ በስጦታ አበርክተዋል።
በሙያቸው ኤሌክትሪካል ኢንጂነር ናቸው፡፡ #በአሜሪካን የቴክሳስን 90 በመቶ የኤሌክትሪክ ሃይል ድርሻ በሚሸፍንና ከ80 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ አቅም ባለው፣ ከ24 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች 99 ነጥብ 99 በመቶ ኤሌክትርክ እንዳይቋረጥ በሚሰራ ድርጅት ውስጥ ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል።
ምኞታቸው በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት እንዲስፋፋና አስተማማኝ ኃይል እንዲኖራት ነው።
ሀገሬ ላይ በገበየሁት እውቀት ውጭ ሀገር ሄጀ መስራት ችያለሁ የሚሉት ባለታሪካችን፤ ከሀገሬ ያገኘሁትን አቅሜ በፈቀደ መጠን መመለስ እንዳለብኝ በማሰብ በሀገረ አሜሪካ በስራ ላይ የማግኛቸውን ልምድና ተሞክሮዎች በማስታወሻ መመዝገብ የየዕለት ተግባሬ ሆኗል ይላሉ፡፡
ህልማቸው ዕውን ሆኖ "የሀገሬን ለሀገሬ!" በሚል ውጭ ሀገር በቆዩበት ወቅት ያገኙትን እውቀት ሰንደው፣ ግምታዊ
ዋጋቸው 600 ሺህ ብር የሚሆን አንድ ሺህ መጽሀፍትን በማሳተም 990ውን መጽሃፍት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ብርሃን የመሆን ስንቅን ይዞ እየተገነባ ላለው ለዓባይ ግድብ በስጦታ አበርክተዋል።
የዓባይ ግድብ በሚጠናቀቅበት ወቅት መጽሃፉ የባለድርሻ አካላት እጅ መግባቱ ወቅታዊና ታሪካዊ ነው ይላሉ፡፡
የአንድ ሀገር የኤሌክትሪካል ግሪድ ትስስርን፣ በሀገሮች የኤሌክትሪክ ግሪዶች መካከል ስለሚኖር ግንኙነትና ትስስር ትኩረት ሊሰጣቸው ስለሚገቡ አሰራሮች በመጽሃፋቸው በስፋት አስረድተዋል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከዓባይ ትሩፋቶች መካከል አንዱ በመሆኑ፤ ከግድቡ የሚመነጨው ኃይል ሳይቆራረጥና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም በቀጣናው የተጀመረውን የኃይል ትስስር ለማጠናክር መጽሃፉ ከፍተኛ አስትዋፅኦ ያበረክታል ይላሉ፡፡
መጽሀፉ ስለተለያዩ የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያዎች፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች፤ በመስመሮቹ ላይ የኤሌክትሪክ ብክነትን ስለመቆጣጠር በስፋት ተተንትኖበታል፡፡
በኤሌክትሪክ የማስተላለፊያና ማሰራጫ መስመሮች ዙሪያ ስለሚፈጠር የኃይል መተፋፈግና በኤሌክትሪክ ሃይል አጠቃቀምና ቁጥጥር ላይ ስለሚያስፈልጉ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎች አሰራርና አተገባበር በመጽሃፉ ተዘርዝሯል።
ሀገራት በመካከላቸው የኤሌክትሪክ ኃይልን ሲጋሩ ሊኖር ስለሚገባው አስፈላጊ ጥንቃቄም ያብራራል፡፡
መፅሀፉ "ዘመናዊነት ያለኤሌክትሪክ የሚታሰብ አይደለም"( Modernity Without Electricity Unthinkable) እንዲሁም "የኤሌክትሪክ ግሪድ አሰራር ("Foundational Concepts of Electric Grid Operations") በሚል ርዕሰ ጉዳይ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተዘጋጀ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡
በሄለን ወንድምነው
መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓም
👍8❤1👏1
መጋቢት 24 አካታች የፖለቲካ ስርዓት የተፈጠረበት ታሪካዊ ቀን ነው - አቶ ኦርዲን በድሪ
****
(ኢ ፕ ድ)
መጋቢት 24 በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ አካታችና አቃፊ የፖለቲካ ስርዓት የተፈጠረበትና የሀሳብ ልዕልና የበላይነት መጎናፀፍ የቻለበት ታሪካዊ ቀን ነው ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 7ኛ ዓመት አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፥ መጋቢት 24 በሀገራችን የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍና ሀገራዊ ተስፋን ሰንቆ የመጣ ነው ብለዋል፡፡
ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች ሀሳባቸውን በነፃነት ማራመድ እንዲችሉና የፍትህና የዳኝነት ሰርዓት ከማንኛውም ጣልቃ ገብነት ነፃ እንዲሆን ማስቻሉን ገልጸው፥ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች እልባት ያገኙበትና ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ችግሮች የተፈቱበት ነው ብለዋል።
በብሔራዊ ገዥ ትርክት ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት ጥረት የተደረገበትና የፖለቲካ ቁርሾን በማስቀረት የበቀልና የመጠፋፋት ፖለቲካን በሽግግር ፍትህና ሀገራዊ ምክክር ለመፍታት የሚያስችል ተስፋ የተሰነቀበት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
መጋቢት 24 የህዝቦችን የዘመናት ጥያቄዎች በህገ መንግስታዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ እንዲመለሱ በማስቻል አበርክቶው የጎላ መሆኑን መግለፃቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
መሰል ስኬቶችና ነፃነቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የውስጥ አንድነትን ማጠናከር ሉአላዊነትን መጠበቅ እንዲሁም የመልማትና የመበልፀግ አቅሞችን መጠቀም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የነገ ኢትዮጵያን ዛሬ መስራትና ለነገ ትውልድ በየፈርጃችን ዛሬ ላይ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
መጋቢት 24 በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ አካታችና አቃፊ የፖለቲካ ስርዓት የተፈጠረበትና የሀሳብ ልዕልና የበላይነት መጎናፀፍ የቻለበት ታሪካዊ ቀን ነው ሲሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 7ኛ ዓመት አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፥ መጋቢት 24 በሀገራችን የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍና ሀገራዊ ተስፋን ሰንቆ የመጣ ነው ብለዋል፡፡
ሀገራዊ ለውጡ ዜጎች ሀሳባቸውን በነፃነት ማራመድ እንዲችሉና የፍትህና የዳኝነት ሰርዓት ከማንኛውም ጣልቃ ገብነት ነፃ እንዲሆን ማስቻሉን ገልጸው፥ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች እልባት ያገኙበትና ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ችግሮች የተፈቱበት ነው ብለዋል።
በብሔራዊ ገዥ ትርክት ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት ጥረት የተደረገበትና የፖለቲካ ቁርሾን በማስቀረት የበቀልና የመጠፋፋት ፖለቲካን በሽግግር ፍትህና ሀገራዊ ምክክር ለመፍታት የሚያስችል ተስፋ የተሰነቀበት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
መጋቢት 24 የህዝቦችን የዘመናት ጥያቄዎች በህገ መንግስታዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ እንዲመለሱ በማስቻል አበርክቶው የጎላ መሆኑን መግለፃቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
መሰል ስኬቶችና ነፃነቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የውስጥ አንድነትን ማጠናከር ሉአላዊነትን መጠበቅ እንዲሁም የመልማትና የመበልፀግ አቅሞችን መጠቀም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የነገ ኢትዮጵያን ዛሬ መስራትና ለነገ ትውልድ በየፈርጃችን ዛሬ ላይ መትጋት ይኖርብናል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓም
👍7👎6👏1
ከ22 ቶን በላይ ወርቅ ለውጪ ገበያ ቀርቧል
****
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 በጀት ባለፉት ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ወርቅ ለውጪ ገበያ ማቅረቡን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢንዲስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የስምንት ወር የዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።
የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ ባለፉት ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ወርቅ ለውጪ ገበያ መቅረቡን ለኢንዲስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ ባቀረቡት ሪፖርተር ገልጸዋል።
በስምንት ወራት ውስጥ ሰድስት ቶን ወርቅ ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ጠቅሰው፤ 22 ነጥብ 5 ቶን ወርቅ ማቀርብ መቻሉን ገልጸዋል።
ለውጪ ገበያ እየቀረበ ያለው የወርቅ ምርት አሁን ባለበት ሁኔታ ከቀጠለ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 33 ቶን ወርቅ ይደርሳል። ይህም ኢትዮጵያን ከፍተኛ ወርቅ ለውጪ ከሚያቀርቡ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፍ ነው ብለዋል።
የወርቅ ምርት በኩባንያዎችና በባህላዊ መንገድ እየተመረተ መሆኑንን በሪፖርታቸው የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ከተመረተው ወርቅ 95 በመቶ የሚሆነው በባህላዊ መንገድ የተመረተ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፋት ስምንት ወራት ከማዕድን ዘርፍ ወጪ ንግድ ከተገኘው አንድ ነጥብ 88 ቢሊዮን ዶላር ትልቁን ድርሻ ይይዛል።
የወርቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አነስተኛ የወርቅ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ስራ እንደሚጀምሩም ገልጸዋል።
በታደሠ ብናልፈው
መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 በጀት ባለፉት ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ወርቅ ለውጪ ገበያ ማቅረቡን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢንዲስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ የማዕድን ሚኒስቴርን የስምንት ወር የዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።
የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ ባለፉት ስምንት ወራት 22 ነጥብ 5 ቶን ወርቅ ለውጪ ገበያ መቅረቡን ለኢንዲስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ ባቀረቡት ሪፖርተር ገልጸዋል።
በስምንት ወራት ውስጥ ሰድስት ቶን ወርቅ ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ጠቅሰው፤ 22 ነጥብ 5 ቶን ወርቅ ማቀርብ መቻሉን ገልጸዋል።
ለውጪ ገበያ እየቀረበ ያለው የወርቅ ምርት አሁን ባለበት ሁኔታ ከቀጠለ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 33 ቶን ወርቅ ይደርሳል። ይህም ኢትዮጵያን ከፍተኛ ወርቅ ለውጪ ከሚያቀርቡ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፍ ነው ብለዋል።
የወርቅ ምርት በኩባንያዎችና በባህላዊ መንገድ እየተመረተ መሆኑንን በሪፖርታቸው የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ከተመረተው ወርቅ 95 በመቶ የሚሆነው በባህላዊ መንገድ የተመረተ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፋት ስምንት ወራት ከማዕድን ዘርፍ ወጪ ንግድ ከተገኘው አንድ ነጥብ 88 ቢሊዮን ዶላር ትልቁን ድርሻ ይይዛል።
የወርቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አነስተኛ የወርቅ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ስራ እንደሚጀምሩም ገልጸዋል።
በታደሠ ብናልፈው
መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓም
👍7
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
Photo
👉 ባለፉት ስምንት ወራት የኢትዮጵያ የውጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ደርሷል፣
👉 የጥራት መንደሩ በአመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን ጥራት ያረጋግጣል፣
👉 በኢትዮጵያ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተጀምሯል፣
*****
(ኢ ፕ ድ)
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ በ2010 ዓም የኢትዮጵያ የውጪ ንግድ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የነበረ መሆኑን ጠቅሰው በስምንት ወራት የውጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ደርሷል።
በ2017 በጀት ዓመት መጨረሻ ከ6 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግስት የንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪና ተገማች ለማድረግ በመስራት ላይ መሆኑን መሆኑን ጠቅሰው ንግዱ ቀጠናውን የሚያስተሳስር የንግድ ልውውጥ ለማድረግ መሆኑንም ገልጸዋል።
በሀገሪቱ የንግድ ፖሊሲ እንዳልነበረ በመግለጽ ከብዙ ጥረትና ድካም በኋላ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ባለፉት ስምንት ወራት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የንግድ ማህበረሰብ አዲስ የንግድ ፈቃድ አውጥቷል። ከአንድ ሺህ 300 በላይ የቅዳሜና እሁድ ገብያዎችን በማደራጀት ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በንግዱ ዘርፉ ላይ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ ጠቅሰው የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የሚያስችል ተጨባጭ ተስፋ ታይቶበታል ያሉት ሚኒስትሩ የንግድ ፖሊሲው ሀገሪቱ ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
ሀገሪቱ ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የጥራት መንደርን ከ8 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መገንባቱን ጠቅሰው በዓመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን የጥራት የማረጋገጥ ሥራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በማርቆስ በላይ
መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
👉 የጥራት መንደሩ በአመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን ጥራት ያረጋግጣል፣
👉 በኢትዮጵያ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተጀምሯል፣
*****
(ኢ ፕ ድ)
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ በ2010 ዓም የኢትዮጵያ የውጪ ንግድ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የነበረ መሆኑን ጠቅሰው በስምንት ወራት የውጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ደርሷል።
በ2017 በጀት ዓመት መጨረሻ ከ6 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግስት የንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪና ተገማች ለማድረግ በመስራት ላይ መሆኑን መሆኑን ጠቅሰው ንግዱ ቀጠናውን የሚያስተሳስር የንግድ ልውውጥ ለማድረግ መሆኑንም ገልጸዋል።
በሀገሪቱ የንግድ ፖሊሲ እንዳልነበረ በመግለጽ ከብዙ ጥረትና ድካም በኋላ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ባለፉት ስምንት ወራት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የንግድ ማህበረሰብ አዲስ የንግድ ፈቃድ አውጥቷል። ከአንድ ሺህ 300 በላይ የቅዳሜና እሁድ ገብያዎችን በማደራጀት ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በንግዱ ዘርፉ ላይ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ ጠቅሰው የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የሚያስችል ተጨባጭ ተስፋ ታይቶበታል ያሉት ሚኒስትሩ የንግድ ፖሊሲው ሀገሪቱ ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
ሀገሪቱ ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የጥራት መንደርን ከ8 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መገንባቱን ጠቅሰው በዓመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን የጥራት የማረጋገጥ ሥራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በማርቆስ በላይ
መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
👍5❤1👏1
የኢትዮጵያ አየር መንገዱ ወደ ማካው ከተማ የመጀመሪያ የካርጎ በረራውን አደረገ
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይናዋ ማካው ከተማ የመጀመሪያ የካርጎ በረራውን በዛሬው ዕለት አድርጓል።
አየር መንገዱ በማካው ባስጀመረው የካርጎ አገልግሎት ስነ ስርዓት ላይ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው እንደገለፁት የአገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ የካርጎ ትስስሩን ለማስፋትና የዓለም ንግድን ለማሳለጥ ያለው ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አየር መንገዱ በቻይና የካርጎ መዳረሻውን ወደ 10 ከፍ ማድረጉን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይናዋ ማካው ከተማ የመጀመሪያ የካርጎ በረራውን በዛሬው ዕለት አድርጓል።
አየር መንገዱ በማካው ባስጀመረው የካርጎ አገልግሎት ስነ ስርዓት ላይ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው እንደገለፁት የአገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ የካርጎ ትስስሩን ለማስፋትና የዓለም ንግድን ለማሳለጥ ያለው ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አየር መንገዱ በቻይና የካርጎ መዳረሻውን ወደ 10 ከፍ ማድረጉን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
👍9👏1