“ማንኛውም ትንኮሳና ፈተና ኢትዮጵያን ከብልጽግና ጉዞ ማስቆም አይችልም”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ማንኛውም ትንኮሳና ፈተና ኢትዮጵያን ከብልጽግና ጉዞ ማቆም አይችልም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማንኛውም ፈተና፣ ትንኮሳና ክፉ ሃሳብ ኢትዮጵያን ከብልጽግና ማቆም አይችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ጠላቶች አንድ በአንድ እናራግፋለን ብለዋል።
ከአባቶቻችን በደም የወረስነውን ነጻነት በብልጽግና ማጽናት ከዚህ ትውልድ እንደሚጠበቅ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኑን ገልጸዋል።
ብልጽግናን ማሳካት ፈታኝ መሆኑን በመግለጽ፤ የወረስነውን ነጻነት ብቻ ሳይሆን የተሸከምነውን የትውልድ አደራ ማሰብ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ማየት አለብን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ትውልድ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ፍልፍሎ የማየትና የማውጣት ብቃት አለው ብለዋል።
ከኢትዮጵያ መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትም እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ የጸናች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊነት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአገርን መሻትና የባዳን ክፋት መለየት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ፤ ኢትዮጵያዊያን ለባዳ ፍላጎት መሳሪያ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያዊያን ቀልብ ገዝተን ሰላማችንን እናጽና ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የአገርን ክብርና የዜጎችን ጥቅም እናስከብር ብለዋል።
ኢትዮጵያ በብዙ ተስፋ የተመላች አገር መሆኑኗን ጠቅሰው፤ አስደናቂ ጅማሮና ውጤት እያሳየች መሆኑንም ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ብሔርብሔረሰቦች #በዓል #ሆሳዕና #ዐቢይ_አሕመድ
#ጠቅላይ_ሚኒስትር
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ማንኛውም ትንኮሳና ፈተና ኢትዮጵያን ከብልጽግና ጉዞ ማቆም አይችልም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማንኛውም ፈተና፣ ትንኮሳና ክፉ ሃሳብ ኢትዮጵያን ከብልጽግና ማቆም አይችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ጠላቶች አንድ በአንድ እናራግፋለን ብለዋል።
ከአባቶቻችን በደም የወረስነውን ነጻነት በብልጽግና ማጽናት ከዚህ ትውልድ እንደሚጠበቅ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኑን ገልጸዋል።
ብልጽግናን ማሳካት ፈታኝ መሆኑን በመግለጽ፤ የወረስነውን ነጻነት ብቻ ሳይሆን የተሸከምነውን የትውልድ አደራ ማሰብ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ማየት አለብን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ትውልድ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ፍልፍሎ የማየትና የማውጣት ብቃት አለው ብለዋል።
ከኢትዮጵያ መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትም እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ የጸናች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊነት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአገርን መሻትና የባዳን ክፋት መለየት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ፤ ኢትዮጵያዊያን ለባዳ ፍላጎት መሳሪያ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያዊያን ቀልብ ገዝተን ሰላማችንን እናጽና ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የአገርን ክብርና የዜጎችን ጥቅም እናስከብር ብለዋል።
ኢትዮጵያ በብዙ ተስፋ የተመላች አገር መሆኑኗን ጠቅሰው፤ አስደናቂ ጅማሮና ውጤት እያሳየች መሆኑንም ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ብሔርብሔረሰቦች #በዓል #ሆሳዕና #ዐቢይ_አሕመድ
#ጠቅላይ_ሚኒስትር
👍8❤5👏1
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በጄኔቫ ስዊዘርላንድ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ድርጅታዊ ስብሰባ ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የቢሮ አባል በመሆን ተመርጣለች።
በዚህም ኢትዮጵያ አፍሪካን በመወከል ለአንድ ዓመት ያህል በመሪነት ሚና እንደምታገለግል ተመላክቷል።
የኢትዮጵያን መመረጥ ተከትሎ በተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋብ ክበበው ዳካ እና በስዊዘርላንድ የሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው እንደሚያገለግሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
በአማን ረሺድ
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በጄኔቫ ስዊዘርላንድ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ድርጅታዊ ስብሰባ ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የቢሮ አባል በመሆን ተመርጣለች።
በዚህም ኢትዮጵያ አፍሪካን በመወከል ለአንድ ዓመት ያህል በመሪነት ሚና እንደምታገለግል ተመላክቷል።
የኢትዮጵያን መመረጥ ተከትሎ በተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋብ ክበበው ዳካ እና በስዊዘርላንድ የሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው እንደሚያገለግሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
በአማን ረሺድ
❤4👎1👏1
የኢትዮጵያን የአየር ክልል ከማንኛውም ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል አቅም ተገንብቷል
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያን የአየር ክልል ከማንኛውም ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል አቅም መገንባቱን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴል ጀነራል መሰረት ጌታቸው ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የአየር ኃይሉ ዋነኛ ተልዕኮ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በማንኛው ሰዓት ከማንኛውም ሁኔታ መጠበቅና መከላከል ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት የተቋሙን ራዕይ ለማሳካት አገርና መንግሥት የሰጠንን ተልዕኮና ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ታጥቀናል ያሉት ብርጋዴል ጀነራል መሰረት፣ አየር ኃይሉ ማንኛውንም ግዳጅ በአስተማማኝ ሁኔታ መወጣት የሚችል፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ መፍጠር፤ መታጠቅና መጠቀም የሚችል ነው ብለዋል፡፡
ቴክኖሎጂን መሸከም፣ ማፍለቅና መጠቀም የሚችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ ቴክኖሎጂዎችን የራስ ማድረግና በራስ አቅም መጠቀም መቻሉንም ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያን አየር ክልል የማስጠበቅ ጉዳይ የ24 ሰዓት ሥራ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
የውጊያ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋትና የመገንባት ሥራ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸው፤ ከለውጡ ወዲህ አየር ኃይል የውጊያ መሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቱን አስረድተዋል፡፡
አየር ኃይሉ ጥራት ያለው የሰው ኃይል በማፍራት ግዳጅን የመወጣት አቅሙን የተሻለ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በ2030 ከአፍሪካ ምርጥ አየር ኃይሎች አንዱ ለማድረግ መታቀዱንም ገልጸዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #gazetteplus #አየር_ኃይል #ውጊያ #ኢትዮጵያ
#አየር_ክልል #ብርጋዴል_ጀነራል #አዛዥ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያን የአየር ክልል ከማንኛውም ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል አቅም መገንባቱን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴል ጀነራል መሰረት ጌታቸው ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የአየር ኃይሉ ዋነኛ ተልዕኮ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በማንኛው ሰዓት ከማንኛውም ሁኔታ መጠበቅና መከላከል ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት የተቋሙን ራዕይ ለማሳካት አገርና መንግሥት የሰጠንን ተልዕኮና ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ታጥቀናል ያሉት ብርጋዴል ጀነራል መሰረት፣ አየር ኃይሉ ማንኛውንም ግዳጅ በአስተማማኝ ሁኔታ መወጣት የሚችል፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ መፍጠር፤ መታጠቅና መጠቀም የሚችል ነው ብለዋል፡፡
ቴክኖሎጂን መሸከም፣ ማፍለቅና መጠቀም የሚችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ ቴክኖሎጂዎችን የራስ ማድረግና በራስ አቅም መጠቀም መቻሉንም ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያን አየር ክልል የማስጠበቅ ጉዳይ የ24 ሰዓት ሥራ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
የውጊያ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋትና የመገንባት ሥራ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸው፤ ከለውጡ ወዲህ አየር ኃይል የውጊያ መሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቱን አስረድተዋል፡፡
አየር ኃይሉ ጥራት ያለው የሰው ኃይል በማፍራት ግዳጅን የመወጣት አቅሙን የተሻለ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በ2030 ከአፍሪካ ምርጥ አየር ኃይሎች አንዱ ለማድረግ መታቀዱንም ገልጸዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #gazetteplus #አየር_ኃይል #ውጊያ #ኢትዮጵያ
#አየር_ክልል #ብርጋዴል_ጀነራል #አዛዥ
❤5
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ከ114 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት ደረሰ
++++++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በስርቆትና ውድመት የተነሳ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ከ114 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት እና የኃይል ስርቆት ላይ የደረሰበትን ጉዳት አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
መግለጫውን የሰጡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር፤ ባለፉት አራት ወራት በመሰረተ ልማት በተፈጸመ ስርቆት፣ በመኪና አደጋ በደረሰ ውድመት እና በኃይል ስርቆት በድምሩ 114 ሚሊዮን 299 ሺህ 93 ብር የሚገመት ጉዳት በተቋሙ ላይ ደርሷል ብለዋል።
በ17 ትራንስፎርመሮች ላይ በተፈጸመ ስርቆት 23 ሚሊዮን 85 ሺህ 847 ብር ኪሳራ ደርሷል ያሉት ኃላፊው፤ በኤሌክትሪክ ኃይል አስተላላፊ ኬብል ስርቆት ደግሞ 88 ሚሊዮን 849 ሺህ 858 ብር ጉዳት ደርሷል ሲሉ ገልጸዋል።
በመኪና ግጭት የደረሰ የመሠረተ ልማት ውድመት ብዛት 15 ሲሆን፣ በብር ሲተመን 18 ሚሊዮን 178 ሺህ 731 ብር ጉዳት ማጋጠሙን አብራርተዋል።
ተቋሙ ባለፉት አራት ወራት 36 ነጥብ 45 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት መፈጸሙን ጠቁመው፤ በዚህም ምክንያት ተቋሙ 13 ሚሊዮን 184 ሺህ 677 ብር አጥቷል ሲሉ አብራርተዋል።
በአጠቃላይ ባለፉት አራት ወራት 107 ጉዳቶች እንደተመዘገቡ ጠቅሰው፤ 10 የወንጀል ክሶች ተመስርተው በፍርድ ሂደት ላይ እንደሚገኙ፣ ቀሪዎቹም በፖሊስ የምርመራ ሂደት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በታደሠ ብናልፈው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኤሌክትሪክ #መሠረተልማት #ኢትዮጵያ
++++++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በስርቆትና ውድመት የተነሳ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ከ114 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት እና የኃይል ስርቆት ላይ የደረሰበትን ጉዳት አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
መግለጫውን የሰጡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር፤ ባለፉት አራት ወራት በመሰረተ ልማት በተፈጸመ ስርቆት፣ በመኪና አደጋ በደረሰ ውድመት እና በኃይል ስርቆት በድምሩ 114 ሚሊዮን 299 ሺህ 93 ብር የሚገመት ጉዳት በተቋሙ ላይ ደርሷል ብለዋል።
በ17 ትራንስፎርመሮች ላይ በተፈጸመ ስርቆት 23 ሚሊዮን 85 ሺህ 847 ብር ኪሳራ ደርሷል ያሉት ኃላፊው፤ በኤሌክትሪክ ኃይል አስተላላፊ ኬብል ስርቆት ደግሞ 88 ሚሊዮን 849 ሺህ 858 ብር ጉዳት ደርሷል ሲሉ ገልጸዋል።
በመኪና ግጭት የደረሰ የመሠረተ ልማት ውድመት ብዛት 15 ሲሆን፣ በብር ሲተመን 18 ሚሊዮን 178 ሺህ 731 ብር ጉዳት ማጋጠሙን አብራርተዋል።
ተቋሙ ባለፉት አራት ወራት 36 ነጥብ 45 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት መፈጸሙን ጠቁመው፤ በዚህም ምክንያት ተቋሙ 13 ሚሊዮን 184 ሺህ 677 ብር አጥቷል ሲሉ አብራርተዋል።
በአጠቃላይ ባለፉት አራት ወራት 107 ጉዳቶች እንደተመዘገቡ ጠቅሰው፤ 10 የወንጀል ክሶች ተመስርተው በፍርድ ሂደት ላይ እንደሚገኙ፣ ቀሪዎቹም በፖሊስ የምርመራ ሂደት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በታደሠ ብናልፈው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኤሌክትሪክ #መሠረተልማት #ኢትዮጵያ
❤4🤔1
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራ ተጀመረ
+++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራን ዛሬ በጋራ ማስጀመራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቁ።
የፋይናንስ ዘርፍ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ወሳኝ ምዕራፍ የሆነውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራ በይፋ መጀመሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በወጣው መግለጫ ገልጿል።
+++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራን ዛሬ በጋራ ማስጀመራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቁ።
የፋይናንስ ዘርፍ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ወሳኝ ምዕራፍ የሆነውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከባንክ ስርዓት ጋር የማጣመር ሥራ በይፋ መጀመሩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በወጣው መግለጫ ገልጿል።
👍7🙏1
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የሰላም ስምምነቱ ድርጅታዊ ዕውቅና ያለው መሆኑን ገለጸ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ድርጅታዊ ዕውቅና ያለው መሆኑን አፋህድ አስታውቋል።
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የሰላም ስምምነቱን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ መምሪያ ምክትል ኃላፊ እያሱ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ድርጅታዊ ዕውቅና ያለው ነው።
የፈጸመው ስምምነት የአማራ ህዝብን ወደ ሰላም የሚመልስ መሆኑን ጠቁመው፤ ስምምነቱም በድርጅቱ አመራሮች እና ሠራዊት ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
የአማራ ህዝብን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ከመንግስት ጋር በመሆን ለመፍታት እንደሚሰራም ኃላፊው ተናግረዋል።
ሀገርን በሚያፈርስ ተግባር የተሰማሩ አካላት እየሄዱበት ያለው ሂደት ለማንም እንደማይጠቅም የገለጹት ኃላፊው፤ ለአማራ ሕዝብ እንታገላለን የሚሉ አደረጃጀቶች የሰላም አማራጭን እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአፈሕድ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ፋይናንስ ኃላፊ ከፈለ ዓለሙ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ የአማራ ህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ሲታገል መቆየቱን አውስተው፤ የተደረሰው ሰምምነት ህዝቡን ወደ ልማት የሚመልስ ነው ብለዋል።
የወሎ ቤተ አማራ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የህዝብ አስተዳደርና ማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ ግርማ እጅጋየሁ በበኩላቸው፤ የአፋሕድ የትጥቅ ትግል አካሄድ ለአማራ ህዝብ ጥቅም ባለማስገኘቱ ወደ ድርድር መመለሱን ጠቁመዋል።
በአማን ረሺድ
#ጋዜጣ_ፕላስ #አፋህድ #ሰላምስምምነት #አማራ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ድርጅታዊ ዕውቅና ያለው መሆኑን አፋህድ አስታውቋል።
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የሰላም ስምምነቱን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ መምሪያ ምክትል ኃላፊ እያሱ አበራ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት ድርጅታዊ ዕውቅና ያለው ነው።
የፈጸመው ስምምነት የአማራ ህዝብን ወደ ሰላም የሚመልስ መሆኑን ጠቁመው፤ ስምምነቱም በድርጅቱ አመራሮች እና ሠራዊት ተቀባይነት ያገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
የአማራ ህዝብን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ከመንግስት ጋር በመሆን ለመፍታት እንደሚሰራም ኃላፊው ተናግረዋል።
ሀገርን በሚያፈርስ ተግባር የተሰማሩ አካላት እየሄዱበት ያለው ሂደት ለማንም እንደማይጠቅም የገለጹት ኃላፊው፤ ለአማራ ሕዝብ እንታገላለን የሚሉ አደረጃጀቶች የሰላም አማራጭን እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የአፈሕድ ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ፋይናንስ ኃላፊ ከፈለ ዓለሙ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ የአማራ ህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ሲታገል መቆየቱን አውስተው፤ የተደረሰው ሰምምነት ህዝቡን ወደ ልማት የሚመልስ ነው ብለዋል።
የወሎ ቤተ አማራ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የህዝብ አስተዳደርና ማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ ግርማ እጅጋየሁ በበኩላቸው፤ የአፋሕድ የትጥቅ ትግል አካሄድ ለአማራ ህዝብ ጥቅም ባለማስገኘቱ ወደ ድርድር መመለሱን ጠቁመዋል።
በአማን ረሺድ
#ጋዜጣ_ፕላስ #አፋህድ #ሰላምስምምነት #አማራ
❤8😁1
የሶፍ ዑመር የባቡር መንገድ ግንባታ በተያዘው ዓመት ይጠናቀቃል
++++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በሶፍ ዑመር ዋሻና ሎጅ ፕሮጀክቶች ውስጥ ለቱሪስት አገልግሎት መስጫ እየተገነባ የሚገኘው የባቡር መስመር በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የባቡር ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ስለሺ ካሳ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የባሌ አካባቢን ቱሪዝም ለማሳደግ ሶፍ ዑመር ላይ እየተገነባ ያለው የባቡር መንገድ ግንባታ በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል።
ኢትዮጵያ ከአሏት ዕምቅ ሀብቶች መካከል አንዱ ቱሪዝም ነው ያሉት ኢንጂነር ስለሺ፤ ሀገሪቱን ባላት የቱሪዝም ሀብት ልክ ተጠቃሚ ለማድረግ በትራንስፖርት ማስተሳሰር ቀዳሚ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
በውስጥ አቅም በመገንባት የመጀመሪያ የሆነው ይህ ፕሮጀክት እስካሁን ከ50 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ገልጸው፣ አጠቃላይ ርዝመቱ አምስት ኪሎ ሜትር መሆኑን አስረድተዋል።
የባቡር መንገዱ በቀጣይም እንደ ሁኔታው ሊሰፋ የሚችልበት ዕድል መኖሩን ጠቅሰው፤ ለጎብኝዎች ያለ ስጋት መንቀሳቀስ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።
በሀገሪቱ በአጠቃላይ የባቡር መስመሮች ላይ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ስለሺ፤ አዋሽ - ኮምቦልቻ - ሀራ ገበያ የባቡር መንገድ ከዚህ በፊት የነበረውን የመሠረተ ልማት ስርቆት ችግር በመቅረፍ ከአማራና ከአፋር ክልሎች ጋር በተሰራ ስራ መቀነስ መቻሉን አያይዘው አመልክተዋል።
የባቡር መስመሩ አገልግሎቱን ለማስጀመር በውስጥ አቅም የመጠገን ተግባራት እየተከናወኑ ሲሆን፤ በቅርቡም ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ባቡር #ሶፍ_ዑመር #ባሌ #ቱሪዝም
++++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በሶፍ ዑመር ዋሻና ሎጅ ፕሮጀክቶች ውስጥ ለቱሪስት አገልግሎት መስጫ እየተገነባ የሚገኘው የባቡር መስመር በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የባቡር ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ስለሺ ካሳ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የባሌ አካባቢን ቱሪዝም ለማሳደግ ሶፍ ዑመር ላይ እየተገነባ ያለው የባቡር መንገድ ግንባታ በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል።
ኢትዮጵያ ከአሏት ዕምቅ ሀብቶች መካከል አንዱ ቱሪዝም ነው ያሉት ኢንጂነር ስለሺ፤ ሀገሪቱን ባላት የቱሪዝም ሀብት ልክ ተጠቃሚ ለማድረግ በትራንስፖርት ማስተሳሰር ቀዳሚ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
በውስጥ አቅም በመገንባት የመጀመሪያ የሆነው ይህ ፕሮጀክት እስካሁን ከ50 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ገልጸው፣ አጠቃላይ ርዝመቱ አምስት ኪሎ ሜትር መሆኑን አስረድተዋል።
የባቡር መንገዱ በቀጣይም እንደ ሁኔታው ሊሰፋ የሚችልበት ዕድል መኖሩን ጠቅሰው፤ ለጎብኝዎች ያለ ስጋት መንቀሳቀስ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።
በሀገሪቱ በአጠቃላይ የባቡር መስመሮች ላይ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ስለሺ፤ አዋሽ - ኮምቦልቻ - ሀራ ገበያ የባቡር መንገድ ከዚህ በፊት የነበረውን የመሠረተ ልማት ስርቆት ችግር በመቅረፍ ከአማራና ከአፋር ክልሎች ጋር በተሰራ ስራ መቀነስ መቻሉን አያይዘው አመልክተዋል።
የባቡር መስመሩ አገልግሎቱን ለማስጀመር በውስጥ አቅም የመጠገን ተግባራት እየተከናወኑ ሲሆን፤ በቅርቡም ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ባቡር #ሶፍ_ዑመር #ባሌ #ቱሪዝም
❤12
“ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በባዳዎችና ባንዳዎች ዕኩይ ተግባር ነው”
- የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባል
++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በባዳዎችና ባንዳዎች ዕኩይ ተግባር ነው ሲሉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባል ፒቲ ኦፊሰር ፈረደ ፍትሃነገስት ገለጹት።
የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባል ፒቲ ኦፊሰር ፈረደ ፍትሃነገስት ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በባዳዎችና ባንዳዎች ዕኩይ ተግባር ነው።
ሉዓላዊ ሀገርን መዝጋት በራሱ በህግ አግባብ ተጠያቂ የሚያደርግ በመሆኑ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ከህግ አግባብ ውጪ የሚሆንበት አንዳች ምክንያት የለም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ አሰብን ማጣት ያልነበረባት መሆኑን የጠቀሱት አባሉ፤ ያለፈውን መውቀስ ብቻ ሳይሆን ከነበረው ሁኔታ ትምህርት ተወስዶ ችግሮችን እያረሙ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ለተፈጠረው ችግር ከቀድሞ ባህር ኃይሎች ምን ይጠበቃል የሚለውን ምላሽ ለመስጠት ማህበር ተቋቁሞ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
አያይዘው እንደገለጹትም፤ ለ36 ዓመታት በጠንካራ መሰረት ላይ የተገነባ ባህር ኃይል ማፍረስ በሀገር ላይ የተሰነዘረ ከባድ ጥቃት ነው።
በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ባህር_በር #ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህር
- የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባል
++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በባዳዎችና ባንዳዎች ዕኩይ ተግባር ነው ሲሉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባል ፒቲ ኦፊሰር ፈረደ ፍትሃነገስት ገለጹት።
የኢትዮጵያ ባህር ኃይል አባል ፒቲ ኦፊሰር ፈረደ ፍትሃነገስት ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በባዳዎችና ባንዳዎች ዕኩይ ተግባር ነው።
ሉዓላዊ ሀገርን መዝጋት በራሱ በህግ አግባብ ተጠያቂ የሚያደርግ በመሆኑ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ከህግ አግባብ ውጪ የሚሆንበት አንዳች ምክንያት የለም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ አሰብን ማጣት ያልነበረባት መሆኑን የጠቀሱት አባሉ፤ ያለፈውን መውቀስ ብቻ ሳይሆን ከነበረው ሁኔታ ትምህርት ተወስዶ ችግሮችን እያረሙ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ለተፈጠረው ችግር ከቀድሞ ባህር ኃይሎች ምን ይጠበቃል የሚለውን ምላሽ ለመስጠት ማህበር ተቋቁሞ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
አያይዘው እንደገለጹትም፤ ለ36 ዓመታት በጠንካራ መሰረት ላይ የተገነባ ባህር ኃይል ማፍረስ በሀገር ላይ የተሰነዘረ ከባድ ጥቃት ነው።
በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ባህር_በር #ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህር
❤6👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በአምባሳደር ባጫ ደበሌ የመጽሐፍ ምረቃ ላይ ከተናገሩት የተወሰደ‼️
❤4🤯1