Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
አትክልትና ፍራፍሬን ለህብረተሰቡ በቀጥታ ለማቅረብ እየሰራን ነው -አርሶ አደሮች
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አትክልትና ፍራፍሬን ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በቀጥታ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑን በከተማ ግብርና የተሰማሩ የአዳማ ከተማ አርሶ አደሮች ገለጹ።
አርሶ አደር ነገዎ ወርጂ እንደገለጹት በ12 ሄክታር መሬት ላይ ቃሪያ፣ ሽንኩርትና ቲማቲም እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ምርቱ እየደረሰ በመሆኑ ደላላ ጣልቃ ሳይገባ ለሸማቹ ህብረተሰብ በቀጥታ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጭዎቹ 10 ቀናት ውስጥ የቲማትምና የቃሪያ ምርት ለገበያ ማቅረብ እንደሚጀምሩ አመላክተዋል ።
ምርታቸውን ለምግብነት ከመጠቀም አልፈው ለህብረተሰቡ በቀጥታ በማቅረብ የዋጋ ንረቱን ለማቃለል የመሸጫ ቦታ ከመስተዳድሩ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸዋል።
“ወደ ከተማ ከተካለልን ወዲህ ብዙ እገዛ ተደርጎልን በከተማ ግብርና ተሰማርተን የጓሮ አትክልት እያለማን ነው” ያሉት ደግሞ የአዳማ ከተማ መልካ ሂዳ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ለገሰ ጉደታ ናቸው።
በአሁኑ ወቅት ለራሳቸው ለምግብነትም ሆነ ለከተማው ህብረተሰብ ለማቅረብ ቃሪያና ቲማቲም እንዲሁም ፓፓያ እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
ቀደም ብሎ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ያመርቱ የነበረውን አሁን በዓመት ሶስት ጊዜ እያመረቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ምርታቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየተጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ከአትክልት በተጨማሪ በበጋ ስንዴ ልማት ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
የአዳማ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ሂርጶ በበኩላቸው “በአሁኑ ወቅት በመንግስት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በከተማዋ ከ627 ሄክታር በላይ መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ስንዴን በመስኖ እያለማን ነው” ብለዋል።
በተጨማሪም 10 ትምህርት ቤቶች ላይ በ6 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑንም አቶ ጌታቸው መናገራቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።
“ምግባችን ከጓሮአችን” በሚል መሪ ሃሳብ አብዛኛው የከተማው ነዋሪ ቶሎ የሚደርስ አትክትልና ፍራፍሬ እንዲያለማ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከላት በዘርፉ ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ተጠቆመ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በሆቴልና ቱሪዝም ሙያ ስልጠና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያበረታታ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከጀርመን ልማት ትብብር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መድረክ ሚኒስትር ዴኤታ በከር ሻሌ (ዶ/ር) በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ትብብርን አጠናክሮ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት ምቹ ሥራ መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪው ባለድርሻ አካላት ሥርዓተ ስልጠናውን በጋራ በመቅረፅ ፣ በማሰልጠንና በመመዘን ጭምር ከሆቴልና ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ማሰልጠኛ ማዕከላት ጋር ትኩረት ሰጥተው በጋራ መሥራት አለባቸው።
በቀጣይም በጋራ በመሥራት የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፉን ማሳደግ እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
የጀርመን መንግስት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እያደረገ ካለው ድጋፍ ባሻገር ይህንን ውይይት በማዘጋጀቱ አመስግነዋል፡፡
የጀርመን ትብብር ልማትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ቤንጃሚን ሀከር ኢትዮጵያ በቱሪዝም ብዙ ሀብት ያላት በመሆኑ ዘርፉን በብቁ ባለሞያዎች በማሳደግ ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻል የጀርመን መንግስት ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ቱሪዝም ኢንስቲትዩት፣ ኃይሌ ሪዞርት፣ሃያት ሪጀንሲ፣ ኩሪፍቱ ሪዞርት፣ ኢትዮጵያ ሼፍ ማህበር፣ ኢትዮጵያ የባህልና ቱሪዝም ጋዜጠኞች ማህበር ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ለብላቴ ልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል አባላት የማዕረግ ማልበስና የእውቅና መስጠት መርሃ-ግብር ተካሄደ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በብላቴ ልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል የኮማንዶ ሰልጣኞች በተደረገው የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ ለማሰልጠኛ ማዕከሉ አባላት የማዕረግ ማልበስና የእውቅና መስጠት መርሃ-ግብር ተከናውኗል፡፡
በስነ-ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የማሰልጠኛ ማዕከሉ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ የሃገርን ደህንነት ከውስጥና ከውጭ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ትንኮሳዎችን የሚመክት ዘመናዊ የሆነ የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማሰልጠንና መገንባት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል።
ሰልጣኝ ኮማንዶዎች በማሰልጠኛ ማዕከሉ የሚሰጡ ስልጠኛዎችን በጀግንነት፣ በታታሪነት መወጣት አለባችው ሲሉም አሳስበዋል፡፡
ዋና አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ የማዕረግ እድገትና እውቅና ላገኙ ለማሠልጠኛ ማዕከሉ አባላት በቀጣይ የሚሰጣቸውን ኃላፊነት በታማኝነትና በቆራጥነት መወጣት አለባቸው። ለሰልጣኞችም አርያዓያ ሆነው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
የቀድሞ አየር ወለድ ሰራዊት አባል መሰረታዊ ወታደር ፈቀደ ሃብተወልድ እኔ እያለሁ ኢትዮጵያ አትፈርስም፤ የሀገርን ጥሪ ተቀብሎ በማሠልጠኛ ማዕከሉ የአሰልጣኝነት ሚናውን ተወጥቷል። ላበረከተው አስተዋፅኦ የተሰጠው ሽልማት ለቀጣይ ስራ መነሳሳትን እንደፈጠረለት መግለጹን ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የእሥራኤል የጤና ቡድን በኢትዮጵያ የሦስት ቀናት ጉብኝቱን ማካሄድ ጀመረ
*************
(ኢ ፕ ድ)
የእሥራኤልን ሦስት የፓርላማ አባላት ያካተተው የጤና ባለሙያዎች ቡድን፤ ሀገሪቱ ውስጥ በተከሰተው የጦርነት የተጎዱ የጤና ተቋማት የሚያካሂደውን ይፋዊ ጉብኝት በዛሬው ዕለት ጀመረ፡፡
በኢትዮጵያ በሚኖረው የሦስት ቀናት ቆይታው፤ ለጦርነት ተጋላጭ ሆነው በቆዩት ክልሎች ውስጥ የሚገኙትን የተጎዱ የጤና ተቋማት እንደሚጎብኙ የቡድኑ መሪ ሚስተር ጋዲ ባርከን አስታውቀዋል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ነገዎ (ዶ/ር)፤ የልዑካን ቡድኑን ዛሬ ጠዋት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተገኝተው አቀባበል አድርገዋል።
የእሥራኤል የፓርላማ አባል እና የቀድሞው የሀገሪቱ የደኅንነት መሥሪያ ቤት ምክትል ሚኒስትር የነበሩት ሚስተር ጋዲ ባርከን በዚሁ ወቅት፤ የልዑካን ቡድኑ የአሁኑ ጉብኝት፣ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቶ ድጋፍ ለማድረግ እና እሥራኤል በችግር ጊዜም ቢሆን ከኢትዮጵያ ጎን መሆኗን ለማሳየት የታለመ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ ጉብኝት በጦርነቱ የተጎዳው ሕዝብ ሕክምና እንዲያገኝ የሚረዳ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶ/ር ዲማ በበኩላቸው፤ የልዑካን ቡድኑ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ጎብኝቶ ድጋፍ ለማድረግ በመምጣቱ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ሰብሳቢው አያይዘውም፤ ቡድኑ በሦስት ቀናት ቆይታው ከጉብኝት በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመገናኘት ለወደሙ የጤና ተቋማት ድጋፍ ለማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ለመወያየት መዘጋጀቱንም በአድናቆት ተመልክተዋል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች የምክር ቤት አባል አቶ ባያብል ሙላትም በበኩላቸው፤ በእሥራኤል የፓርላማ አባል በተበከበሩ ሚስተር ጋዲ ባርከን አነሳሽነት የልዑካን ቡድኑ መምጣቱ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ተግባር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
አቶ ባያብል ሌሎች የጤና ባለሙያዎችም ከዚህ በፊት መምጣታቸው እና አሁንም ተመሳሳይ ጉብኝት መደረጉ ሀገራችን ከእሥራኤል ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ መልካም ግንኙነት እንደሚያመላክት አስረድተዋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
"ዓለም አቀፍ ተቋማትና የረድኤት ድርጅቶች በአፋርና አማራ ክልል ያለውን ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ ዘንግተውታል"
-አሜሪካዊቷ ጋዜጠኛ አን ጋሪሰን
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ዓለም አቀፍ ተቋማትና የረድኤት ድርጅቶች በአፋርና በአማራ ክልል ያለውን ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ ሊገነዘቡና አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል ስትል አሜሪካዊቷ ጋዜጠኛ አን ጋሪሰን ተናገረች።
ሂዩማን ራይትስዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል በቅርቡ በሰሜኑ ኢትዮጵያ ተከስቷል ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተመለከተ ያወጡት የጋራ ሪፖርትም ፖለቲካዊ ይዘት አለው ብላለች።
አን ጋሪሰን በኢትዮጵያ በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች ያደረገችውን ጉብኝት አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር በነበራት ቆይታ ጦርነቱ ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ ማስከተሉን ገልጻለች።
አሸባሪው ሕወሓት በሰው ህይወት ላይ ካደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ማውደሙንና ይህም በርካታ ሰዎች በሰብዓዊ ቀውስ ውስጥ እንዲቆዮ አድርጓቸዋል ብላለች።
ይህንንም ተከትሎ አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በሕዝቡ ላይ የፈጸመው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እጅግ አሰቃቂ መሆኑን ተዘዋውራ በተመለከተቻቸው ሥፍራዎች ባደረገችው ምልከታ ማረጋገጧን ጠቁማለች።
ያም ሆኖ ዓለም አቀፍ ተቋማትና የረድኤት ድርጅቶች በአማራና በአፋር ክልል ያለውን የሰብዓዊ ቀውስ ዘንግተውታል፤ የሚያደርጉትም ድጋፍ ከሚጠበቀው በታችና ሁሉን አቀፍ አለመሆኑን አመልክታ በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ ቀውስ በትግራይ ብቻ ሳይሆን በአፋርና በአማራ ክልል መኖሩን በማወቅ ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ትናግራለች።
በሌላ በኩል ሂዩማን ራይትስ ዎች እና አምነስቲ ኢንተርናሽናል በቅርቡ በሰሜኑ ኢትዮጵያ ተከስቷል ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተመለከተ ያወጡት የጋራ ሪፖርትም ፖለቲካዊ ይዘት አለው ብላለች።
ሪፖርቱ የወጣው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጉዳዩ ላይ ያጠናውን ሪፖርት ከመለቀቁ ከቀናት በፊት መሆኑን አንስታ፤ ይህም አንድ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት በማለም የተደረገ መሆኑን ገልጻለች።
ከዚህም በላይ ሪፖርቱ የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ ማዕቀብ እንዲጥሉ ሁኔታዎችን ለማመቻቸትና ማዕቀብ ካልተጣለ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ሊባባስ ይችላል የሚል እምነት በሰዎች ውስጥ እንዲያድር ያለመ መሆኑንም ነው ያነሳችው።
ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል በአሜሪካን መንግሥት ውስጥ ያሉ የአንዳንድ ግለሰቦች ፍላጎትን ለማስፈጸም እየሰሩ መሆኑንም ጠቁማለች።
በተለይም የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ጄነራል የሆኑት ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ስለ ትግራይ የሰብዓዊ ቀውስ ብቻ በተደጋጋሚ የሚያደርጉት ውግንና የፖለቲካ አቋማቸውን አመላካች ነው፣ይህም ገለልተኛ በመሆን ድርጅቱን ለመምራት ከገቡት ቃል ጋር የሚጻረር ነው ብላለች።
በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ ቀውስና ሌሎች ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ትክክለኛ መረጃዎች በማሰራጨት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የኢትዮጵያን እውነታ እንዲረዳ የበኩሏን እንደምትሰራ አን ጋሪሰን ተናግራለች።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️