በህገወጥ መንገድ ሊጓጓዝ የነበረ አራት ሺህ 476 ሊትር በላይ የምግብ ዘይትና የተለያዩ ሸቀጦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ልዩ ስሙ ሞቢል ማደያ አካባቢ ከምሽቱ 12 ሰዓት ከአይሱዙ መኪና ላይ ወደ ኮንቴይነር ተሸካሚ 2 ሎቤድ ተሽከርካሪዎች ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን በመጫን ላይ ሳለ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክፍለ ከተማው ንግድ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ሎቤድ መኪኖቹ ላይ በተደረገ ፍተሻም አራት ሺህ 476 ሊትር ፓልም የምግብ ዘይት እንዲሁም 12 ኬሻ ቡና፣ 39 ካርቶን ፈሳሽ የምግብ ዘይት መገኘቱና ምርመራውም በሚመለከተው የህገ አካል እንደቀጠለ ጽ/ቤቱ አስታውቋል።
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ሽፈራው አለሙ እንደገለፁት ህጋዊ ሂደታቸውን ያልተከተሉ ምርቶችን ከተለያዩ ህጋዊ ደረሰኝ ካላቸው ምርቶች ጋር በመቀላቀል ህጋዊ አስመስሎ ለማሳለፍ እየተደረገ የነበረውን ሂደት በአካባቢው የተመለከቱ ነዋሪዎች በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን ገልፀዋል።
ህብረተሰቡ መሰል ሕገወጥ ተግባራትን ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የህግ አካል ወይም በስልክ በማሳወቅ የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ቡድን መሪው አቶ ሽፈራው መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
********************
(ኢ ፕ ድ)
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ልዩ ስሙ ሞቢል ማደያ አካባቢ ከምሽቱ 12 ሰዓት ከአይሱዙ መኪና ላይ ወደ ኮንቴይነር ተሸካሚ 2 ሎቤድ ተሽከርካሪዎች ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን በመጫን ላይ ሳለ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክፍለ ከተማው ንግድ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ሎቤድ መኪኖቹ ላይ በተደረገ ፍተሻም አራት ሺህ 476 ሊትር ፓልም የምግብ ዘይት እንዲሁም 12 ኬሻ ቡና፣ 39 ካርቶን ፈሳሽ የምግብ ዘይት መገኘቱና ምርመራውም በሚመለከተው የህገ አካል እንደቀጠለ ጽ/ቤቱ አስታውቋል።
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ ሽፈራው አለሙ እንደገለፁት ህጋዊ ሂደታቸውን ያልተከተሉ ምርቶችን ከተለያዩ ህጋዊ ደረሰኝ ካላቸው ምርቶች ጋር በመቀላቀል ህጋዊ አስመስሎ ለማሳለፍ እየተደረገ የነበረውን ሂደት በአካባቢው የተመለከቱ ነዋሪዎች በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን ገልፀዋል።
ህብረተሰቡ መሰል ሕገወጥ ተግባራትን ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኝ የህግ አካል ወይም በስልክ በማሳወቅ የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ቡድን መሪው አቶ ሽፈራው መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የአርባምንጭ ከተማን ጨምሮ በደቡብ ክልል የተለያዩ ከተሞች የወጣቶች የውይይት መድረክ መካሄድ ጀምሯል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ክልል ከ94ሺ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት ክልል አቀፍ የውይይት መድረክ በተለያዩ ከተሞች እየተካሔደ ነው።
በብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በተቀመጡ አቅጣጫዎችና ውሳኔዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ያለመ ክልል አቀፍ የወጣቶች መድረክ በ157 ከተሞች ወጣቶችን ያሳተፈ ውይይት እየተካሄደ ነው።
በብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ስመኘው አድነው በሆሳዕና ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት በብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማሳደግ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ መቻሉን ተናግረዋል።
በፓርቲው የተቀመጡ አቅጣጫዎችንና ውሳኔዎችን በመፈጸም ሂደት ወጣቱ ግንባር ቀደም ተዋናይ ነው ያሉት ኃላፊው በውይይት መድረኮች ወጣቶች ገንቢ አስተያየት በማቅረብ በሀገሪቱ እየተካሔደ ያለውን የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
በጉባኤው በኢኮኖሚያዊ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውጤታማ የሚያደርጉ ውሳኔዎች መተላለፋቸውንም አብራርተዋል።
የዉይይት መድረኮች በቡታጅራ፣በሀላባ ቁሊቶ፣ በከምባታ ጠምባሮ ዞን እና በሌሎች ከተሞች እየተካሄደ እንደሚገኝ ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ክልል ከ94ሺ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት ክልል አቀፍ የውይይት መድረክ በተለያዩ ከተሞች እየተካሔደ ነው።
በብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በተቀመጡ አቅጣጫዎችና ውሳኔዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ያለመ ክልል አቀፍ የወጣቶች መድረክ በ157 ከተሞች ወጣቶችን ያሳተፈ ውይይት እየተካሄደ ነው።
በብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ስመኘው አድነው በሆሳዕና ከተማ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት በብልጽግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማሳደግ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ መቻሉን ተናግረዋል።
በፓርቲው የተቀመጡ አቅጣጫዎችንና ውሳኔዎችን በመፈጸም ሂደት ወጣቱ ግንባር ቀደም ተዋናይ ነው ያሉት ኃላፊው በውይይት መድረኮች ወጣቶች ገንቢ አስተያየት በማቅረብ በሀገሪቱ እየተካሔደ ያለውን የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
በጉባኤው በኢኮኖሚያዊ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውጤታማ የሚያደርጉ ውሳኔዎች መተላለፋቸውንም አብራርተዋል።
የዉይይት መድረኮች በቡታጅራ፣በሀላባ ቁሊቶ፣ በከምባታ ጠምባሮ ዞን እና በሌሎች ከተሞች እየተካሄደ እንደሚገኝ ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️