በመጪው አርብ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በአዲስ አበባ ይካሄዳል
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
በመጪው አርብ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የ"ከኢድ እስከ ኢድ" አስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
የኮሚቴው ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ መርሀግብሩን ለመታደም እንግዶች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወደ ሀገራቸው በመግባት ላይ የሚገኙ ሲሆን በመጪው አርብ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡
ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ለማስተባበር እስካሁን ከሁለት ሺህ አምስት መቶ በላይ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተሳትፈዋል ያሉት ኡስታዝ አቡበከር በመጪው ረቡዕ የኢድ ኤክስፖ መርሀግብር እንደሚከፈትም ተናግረዋል፡፡
መርሀግብሩ የኢትዮጵያን በጎ ጎን ለዓለም ማስተዋወቂያ እድል እንደሚፈጥርም ኡስታዝ አቡበከር ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ቀደም ሲል ኢድን በአገር ቤት እናክብር በማለት “ታላቁ የኢድ ሰላት በኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል ለኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ለኢትዮጵያ ወዳጆች ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል።
በዳግማዊት ግርማ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
በመጪው አርብ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የ"ከኢድ እስከ ኢድ" አስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
የኮሚቴው ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ መርሀግብሩን ለመታደም እንግዶች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወደ ሀገራቸው በመግባት ላይ የሚገኙ ሲሆን በመጪው አርብ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡
ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ለማስተባበር እስካሁን ከሁለት ሺህ አምስት መቶ በላይ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተሳትፈዋል ያሉት ኡስታዝ አቡበከር በመጪው ረቡዕ የኢድ ኤክስፖ መርሀግብር እንደሚከፈትም ተናግረዋል፡፡
መርሀግብሩ የኢትዮጵያን በጎ ጎን ለዓለም ማስተዋወቂያ እድል እንደሚፈጥርም ኡስታዝ አቡበከር ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፤ ቀደም ሲል ኢድን በአገር ቤት እናክብር በማለት “ታላቁ የኢድ ሰላት በኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል ለኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ለኢትዮጵያ ወዳጆች ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል።
በዳግማዊት ግርማ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውሰጥ ከ248 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ
******
(ኢ ፕ ድ)
በ2014 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውሰጥ 248 ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ
መቻሉን የገቢዎች ሚኒስትሩ አስታወቁ።
ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መረጃ መሰረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 267 ቢሊዮን 558 ሚሊዮን 565 ሺህ 762 ብር ከ 32 ለመሰብሰብ ታቅዶ፤ 248 ቢሊዮን 618 ሚሊዮን 35 ሺህ 417 ብር ከ 89 መሰብሰብ ተችሏል።
ይህ አፈጻጸም ከእቅዱ አንጻር የ93 በመቶ ድርሻ እንዳለው ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
የተሰበሰበው ገቢ ከ2013 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንጻር ሲታይ የብር 36 ቢሊዮን 310 ሚሊዮን 719 ሺህ 438 ብር ከ79 ወይም የ17 ነጥብ 10 ከመቶ እድገት አለውም ብለዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
******
(ኢ ፕ ድ)
በ2014 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውሰጥ 248 ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ
መቻሉን የገቢዎች ሚኒስትሩ አስታወቁ።
ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መረጃ መሰረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 267 ቢሊዮን 558 ሚሊዮን 565 ሺህ 762 ብር ከ 32 ለመሰብሰብ ታቅዶ፤ 248 ቢሊዮን 618 ሚሊዮን 35 ሺህ 417 ብር ከ 89 መሰብሰብ ተችሏል።
ይህ አፈጻጸም ከእቅዱ አንጻር የ93 በመቶ ድርሻ እንዳለው ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
የተሰበሰበው ገቢ ከ2013 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንጻር ሲታይ የብር 36 ቢሊዮን 310 ሚሊዮን 719 ሺህ 438 ብር ከ79 ወይም የ17 ነጥብ 10 ከመቶ እድገት አለውም ብለዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
በኦሮሚያ ክልል ድርቁ ባስከተለው ጉዳት አንድ ነጥብ ሦስት ሚሊዮን እንስሳት መሞታቸው ተገለጸ
******
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከ26 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመቱ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን እንስሳት መሞታቸውን የክልሉ የአደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
በኮሚሽኑ የቅድመ ማስጠንቀቂያና አደጋ ስጋት ቅነሳ ዳይሬክተር አቶ ቤኛ ዱሬሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በክልሉ በስምንት ዞኖች በተከሰተው ደርቅ 14 ሚሊዮን የሚሆኑ እንስሳት ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከ26 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመቱ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን እንስሳት ሞተዋል።
በክልሉ የበልግና የመኸር ወቅት በተከታታይነት መጥፋቱ ስምንቱም ዞኖች ከፍተኛ ድርቅ እንዲከሰት አድርጓል ያሉት አቶ ቤኛ፤ በአጠቃላይ የምግብ እጥረትና የውሃ ችግር የገጠማቸውና ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብለው በጥናት የተለዩት 14 ሚሊዮን ከብቶች
https://www.press.et/?p=71592
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
******
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከ26 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመቱ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን እንስሳት መሞታቸውን የክልሉ የአደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
በኮሚሽኑ የቅድመ ማስጠንቀቂያና አደጋ ስጋት ቅነሳ ዳይሬክተር አቶ ቤኛ ዱሬሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በክልሉ በስምንት ዞኖች በተከሰተው ደርቅ 14 ሚሊዮን የሚሆኑ እንስሳት ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከ26 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመቱ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን እንስሳት ሞተዋል።
በክልሉ የበልግና የመኸር ወቅት በተከታታይነት መጥፋቱ ስምንቱም ዞኖች ከፍተኛ ድርቅ እንዲከሰት አድርጓል ያሉት አቶ ቤኛ፤ በአጠቃላይ የምግብ እጥረትና የውሃ ችግር የገጠማቸውና ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብለው በጥናት የተለዩት 14 ሚሊዮን ከብቶች
https://www.press.et/?p=71592
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ፍራንኮ ቫሉታ ለህገ ወጥ የውጭ ምንዛሬ ዝውውር እንዳይዳርግ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል
****
(ኢ ፕ ድ)
ፍራንኮ ቫሉታ ለሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሬ ዝውውር እንዳይዳርግ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ሲሉ የፖሊሲ ጉዳዮች ባለሙያው አቶ አማንይሁን ረዳ አስታወቁ።
የፖሊሲ ጉዳዮች ባለሙያው አቶ አማንይሁን ረዳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ያለ ውጭ ምንዛሬ ፈቃድ መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ የሚፈቅደው “ፍራንኮ ቫሉታ” አሁን ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታ የተለየ ችግር የተከሰተበት ወቅት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እንደ አገር የገጠመውን የምርት እጥረት ለመቅረፍ ጊዜያዊ መፍትሄ የሚሰጥ ነው። ሆኖም ለህገ ወጥነት በር የሚከፍት በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
ፍራንኮ ቫሉታ የአጭር ጊዜ መፍትሄ ነው ያሉት ባለሙያው፤ ለአጭር ጊዜ መፍትሄ የምርት እጥረት ችግርን ለመቅረፍ በተለይ ምግብ ነክ እቃዎች ከውጭ በበቂ መጠን እንዲገቡና ሕዝቡን ለምሬትና ለብሶት እያደረገ ያለውን የዋጋ ንረት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ ሚና እንዳለው
https://www.press.et/?p=71586
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
****
(ኢ ፕ ድ)
ፍራንኮ ቫሉታ ለሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሬ ዝውውር እንዳይዳርግ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ሲሉ የፖሊሲ ጉዳዮች ባለሙያው አቶ አማንይሁን ረዳ አስታወቁ።
የፖሊሲ ጉዳዮች ባለሙያው አቶ አማንይሁን ረዳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ያለ ውጭ ምንዛሬ ፈቃድ መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ የሚፈቅደው “ፍራንኮ ቫሉታ” አሁን ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታ የተለየ ችግር የተከሰተበት ወቅት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እንደ አገር የገጠመውን የምርት እጥረት ለመቅረፍ ጊዜያዊ መፍትሄ የሚሰጥ ነው። ሆኖም ለህገ ወጥነት በር የሚከፍት በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
ፍራንኮ ቫሉታ የአጭር ጊዜ መፍትሄ ነው ያሉት ባለሙያው፤ ለአጭር ጊዜ መፍትሄ የምርት እጥረት ችግርን ለመቅረፍ በተለይ ምግብ ነክ እቃዎች ከውጭ በበቂ መጠን እንዲገቡና ሕዝቡን ለምሬትና ለብሶት እያደረገ ያለውን የዋጋ ንረት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ ሚና እንዳለው
https://www.press.et/?p=71586
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
መንግሥት የዜጎችን ደህንነት ለማስከበር ፈጣን እርምጃ መውሰድ እንደሚኖርበት ተገለጸ
*****
(ኢ ፕ ድ)
መንግስት የዜጎችን ሰላምና ደህንነትን ለማስከበር ስርአትን የተከተለና ፈጣን እርምጃ መውሰድ እንደሚኖርበት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሽዋስ አሰፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤቱ ከዚህ በፊት በርካታ ጊዜ መግለጫ አውጥቷል።
ኢዜማም ሀገሪቱ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢ እንደነበር በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።
ከዚህ አኳያ የዜጎችን መፈናቀል ለመታደግ ብሎም የዜጎችን ሰላምና ደህንነትን ለማስከበር መንግስት ስርአትን የተከተለና ፈጣን እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል።
የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ችግሮች ከመፈጠራቸው በፊት ቀድሞ ዜጎች ሳይጎዱ መድረስ አለበት ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ሀገርንና ዜጎችን ከጥቃት መጠበቅ፤ በሰላም ወጥተው እንዲገቡና ስራቸውን በነጻነት እንዲሰሩ ማስቻል ቀዳሚ ስራው መሆን አለበት።
የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ያውጣም መግለጫ ጥሩ ቢሆንም ስርአትን የተከተለና ፈጣን እርምጃን ተጋባራዊ ማድረግን
https://www.press.et/?p=71589
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
*****
(ኢ ፕ ድ)
መንግስት የዜጎችን ሰላምና ደህንነትን ለማስከበር ስርአትን የተከተለና ፈጣን እርምጃ መውሰድ እንደሚኖርበት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሽዋስ አሰፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤቱ ከዚህ በፊት በርካታ ጊዜ መግለጫ አውጥቷል።
ኢዜማም ሀገሪቱ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢ እንደነበር በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።
ከዚህ አኳያ የዜጎችን መፈናቀል ለመታደግ ብሎም የዜጎችን ሰላምና ደህንነትን ለማስከበር መንግስት ስርአትን የተከተለና ፈጣን እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል።
የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ችግሮች ከመፈጠራቸው በፊት ቀድሞ ዜጎች ሳይጎዱ መድረስ አለበት ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ሀገርንና ዜጎችን ከጥቃት መጠበቅ፤ በሰላም ወጥተው እንዲገቡና ስራቸውን በነጻነት እንዲሰሩ ማስቻል ቀዳሚ ስራው መሆን አለበት።
የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ያውጣም መግለጫ ጥሩ ቢሆንም ስርአትን የተከተለና ፈጣን እርምጃን ተጋባራዊ ማድረግን
https://www.press.et/?p=71589
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
"የዘንድሮው የፊቼ ጫምባላላ በዓል በልዩ ሁኔታ በደማቅ አውድ ይከበራል"
- አቶ ደስታ ሌዳሞ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ዘንድሮ ሚያዚያ 20 እና 21 የሚከበረውን የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፊቼ ጫምባላላ በዓልን በማስመልከት ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው እንኳን አደረሳችሁ በማለት የሲዳማ ህዝብና መንግሥትም አስፈላጊ ዝግጅት በማድረጉ ህዝቡም የዘንድሮውን ልዩ የሆነውን በዓል በነቂስ ወጥቶ እንዲያከብር ጥሪ አቅርበዋል።
ፊቼ ጫምባላላ ከዓመት ዓመት መሸጋገሪያ በዓል በመሆኑ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተለያዩ ሰዎች የሚገናኙበትና ፍቅር የሚጨምሩበት፣ ሰላም የሚወርድበት በዓል ነው ያሉት አቶ ደስታ፤ መረዳዳት ጎልቶ የሚታይበት፣ ሁሉም በየቤቱ ተደስቶ የሚያከብርበትና ትልቅ ትንሽ ሳይባል ሁሉም በአንድነት የሚያከብርበት በዓል ነው ብለዋል።
በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ ነው፤ መገፋፋትና መጣላት የሌለበትና ብዙ እሴቶች ያሉበት በመሆኑ የአለም ቅርስ ሆኖ ተመዝግቧል ነው ያሉት።
በበዓሉ ላይ ሚንስትሮች፣ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙም አንስተዋል።
የፊቼ ጫምባላላ በዓል ለአንድ ሁለት ቀን ብቻ የሚከበር ስላልሆነ ለአንድ ወር ያህል በሁሉም ወረዳ ይከበራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ከዚህ በተጨማሪ ፊቼ ጫምባላላ የአለም ቅርስ በመሆኑ በአዲስ አበባ ከተማም ይከበራል ብለዋል
- አቶ ደስታ ሌዳሞ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
******
(ኢ.ፕ.ድ)
የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ዘንድሮ ሚያዚያ 20 እና 21 የሚከበረውን የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፊቼ ጫምባላላ በዓልን በማስመልከት ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው እንኳን አደረሳችሁ በማለት የሲዳማ ህዝብና መንግሥትም አስፈላጊ ዝግጅት በማድረጉ ህዝቡም የዘንድሮውን ልዩ የሆነውን በዓል በነቂስ ወጥቶ እንዲያከብር ጥሪ አቅርበዋል።
ፊቼ ጫምባላላ ከዓመት ዓመት መሸጋገሪያ በዓል በመሆኑ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተለያዩ ሰዎች የሚገናኙበትና ፍቅር የሚጨምሩበት፣ ሰላም የሚወርድበት በዓል ነው ያሉት አቶ ደስታ፤ መረዳዳት ጎልቶ የሚታይበት፣ ሁሉም በየቤቱ ተደስቶ የሚያከብርበትና ትልቅ ትንሽ ሳይባል ሁሉም በአንድነት የሚያከብርበት በዓል ነው ብለዋል።
በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ ነው፤ መገፋፋትና መጣላት የሌለበትና ብዙ እሴቶች ያሉበት በመሆኑ የአለም ቅርስ ሆኖ ተመዝግቧል ነው ያሉት።
በበዓሉ ላይ ሚንስትሮች፣ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙም አንስተዋል።
የፊቼ ጫምባላላ በዓል ለአንድ ሁለት ቀን ብቻ የሚከበር ስላልሆነ ለአንድ ወር ያህል በሁሉም ወረዳ ይከበራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ከዚህ በተጨማሪ ፊቼ ጫምባላላ የአለም ቅርስ በመሆኑ በአዲስ አበባ ከተማም ይከበራል ብለዋል
“የሲሚንቶ ገበያውን ለማረጋጋት የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል”
- የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ “የተጋነነ እና ሕገ-ወጥነት የሚስተዋልበትን የሲሚንቶ ገበያ ለማረጋጋት፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል” ሲል አሳሰበ፡፡
ቋሚ ኮሚቴው ይህንን የመስክ ምልከታ ጥቆማ የሰጠው፤ ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ በአካል ተገኝቶ ናሽናል ሲሚንቶ እና ቱሬ ሲሚንቶ ፋብሪካዎችን በአካል ተዘዋውሮ በጎበኘበት ወቅት፤ ከፋብሪካዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ውይይት ነው፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በዚሁ የመስክ ምልከታቸው፤ የናሸናል ሲሚንቶ እና የቱሬ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበሮች፤ አንዱን ከረጢት ሲሚንቶ እስከ 4 መቶ 40 ብር ብቻ እንደሚሸጡ ተረድተዋል። ይሁን እንጂ ከፋብሪካዎቹ በዚሁ ተመን የሚወጡት እነዚሁ ምርቶች፤ እስከ 1 ሺህ 2 መቶ ብር እና ከዚያ በላይ የሚሸጡበት ሁኔታ፣ በባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ርብርብ መፍትሔ ሊበጅለት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ፋብሪካው ጥሬ ዕቃ በሚያገኝበት ቦታ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ እየተደረገ ስለመሆኑም፤ የየፋብሪካው አመራሮች ለቋሚ ኮሚቴው አባላት በተጨማሪነት አስረድተዋል።
የናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ እግዝኤል ብዙአየሁ እንደጠቆሙት፤ ገበያን በማረጋጋት ረገድ መንግስት ክትትል እና ቁጥጥር ሊያደርግ ይገባል፡፡ የዘርፉን የምርት አቅርቦት እና ፍላጎቱን ለማመጣጠን አክሲዮን ማህበሩ በተለያዩ አካባቢዎች የጀመራቸው አዳዲስ ፕሮጄክቶች በመንግሥት እንዲደገፉም ጥያቄያቸውን አያይዘው አቅርበዋል።
በተመሳሳይ የቱሬ ሲሚንቶ ፋብሪካ ጥሬ እቃዎችን ጭኖ ወደ ፋብሪካው ለመውሰድ በአንድ መኪና እስከ 100 ብር በሕገ-ወጥ መንገድ ለግለሰቦች እየከፈለ ስለመሆኑ፤ የፋብሪካው ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዚዳይዳን በክሪ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ገልፀዋል።
የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ፤ የተጠቀሱትን ችግሮች ሁሉ ፋብሪካዎቹ ከአስተዳደሩ እና ከማኅበረሰቡ እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነው ሊፈቷቸው እንደሚችሉ አስገንዝቧል፡፡
ከዚህ በዘለለ ግን ፋብሪካዎቹ ለአካባቢው ማኅበረሰብ እያበረከቱ ያለው ሁለገብ አስተዋጽዖ የሚደነቅ መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው ቡድን መሪ የተከበሩ በጋሻው ተክሉ አውስተው፤ አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችል የማስፋፊያ ሥራ ግን በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባው አመላክተዋል።
የድሬደዋ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ደግሞ፤ መስተዳድሩ ለኢንዱስትሪ እና ለፋብሪካዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ስለመሆኑ ገልጸው፤ በአካባቢው ያለውን የማዕድን ሀብት ለማወቅ እና ለመጠቀም የማዕድን ሚኒስቴር ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ለቋሚ ኮሚቴው አባላት አስረድተዋል ሲል ምክር ቤቱ ዘግቧል።
- የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ “የተጋነነ እና ሕገ-ወጥነት የሚስተዋልበትን የሲሚንቶ ገበያ ለማረጋጋት፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል” ሲል አሳሰበ፡፡
ቋሚ ኮሚቴው ይህንን የመስክ ምልከታ ጥቆማ የሰጠው፤ ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ በአካል ተገኝቶ ናሽናል ሲሚንቶ እና ቱሬ ሲሚንቶ ፋብሪካዎችን በአካል ተዘዋውሮ በጎበኘበት ወቅት፤ ከፋብሪካዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ውይይት ነው፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በዚሁ የመስክ ምልከታቸው፤ የናሸናል ሲሚንቶ እና የቱሬ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበሮች፤ አንዱን ከረጢት ሲሚንቶ እስከ 4 መቶ 40 ብር ብቻ እንደሚሸጡ ተረድተዋል። ይሁን እንጂ ከፋብሪካዎቹ በዚሁ ተመን የሚወጡት እነዚሁ ምርቶች፤ እስከ 1 ሺህ 2 መቶ ብር እና ከዚያ በላይ የሚሸጡበት ሁኔታ፣ በባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ርብርብ መፍትሔ ሊበጅለት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ፋብሪካው ጥሬ ዕቃ በሚያገኝበት ቦታ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ እየተደረገ ስለመሆኑም፤ የየፋብሪካው አመራሮች ለቋሚ ኮሚቴው አባላት በተጨማሪነት አስረድተዋል።
የናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ እግዝኤል ብዙአየሁ እንደጠቆሙት፤ ገበያን በማረጋጋት ረገድ መንግስት ክትትል እና ቁጥጥር ሊያደርግ ይገባል፡፡ የዘርፉን የምርት አቅርቦት እና ፍላጎቱን ለማመጣጠን አክሲዮን ማህበሩ በተለያዩ አካባቢዎች የጀመራቸው አዳዲስ ፕሮጄክቶች በመንግሥት እንዲደገፉም ጥያቄያቸውን አያይዘው አቅርበዋል።
በተመሳሳይ የቱሬ ሲሚንቶ ፋብሪካ ጥሬ እቃዎችን ጭኖ ወደ ፋብሪካው ለመውሰድ በአንድ መኪና እስከ 100 ብር በሕገ-ወጥ መንገድ ለግለሰቦች እየከፈለ ስለመሆኑ፤ የፋብሪካው ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዚዳይዳን በክሪ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ገልፀዋል።
የኢንዱስትሪ እና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ፤ የተጠቀሱትን ችግሮች ሁሉ ፋብሪካዎቹ ከአስተዳደሩ እና ከማኅበረሰቡ እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነው ሊፈቷቸው እንደሚችሉ አስገንዝቧል፡፡
ከዚህ በዘለለ ግን ፋብሪካዎቹ ለአካባቢው ማኅበረሰብ እያበረከቱ ያለው ሁለገብ አስተዋጽዖ የሚደነቅ መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው ቡድን መሪ የተከበሩ በጋሻው ተክሉ አውስተው፤ አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችል የማስፋፊያ ሥራ ግን በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባው አመላክተዋል።
የድሬደዋ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ደግሞ፤ መስተዳድሩ ለኢንዱስትሪ እና ለፋብሪካዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ስለመሆኑ ገልጸው፤ በአካባቢው ያለውን የማዕድን ሀብት ለማወቅ እና ለመጠቀም የማዕድን ሚኒስቴር ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ለቋሚ ኮሚቴው አባላት አስረድተዋል ሲል ምክር ቤቱ ዘግቧል።
"ሃገራዊ ምክክሩን ለማሳካት የተረጋጋ ሰላምና አስተማማኝ ደህንነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል"
- አቶ አባተ ኪሾ
****
(ኢ ፕ ድ)
ሃገራዊ ምክክሩን ለማሳካት የተረጋጋ ሰላምና አስተማማኝ ደህንነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የቀድሞ የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አባተ ኪሾ አመለከቱ።
በሃገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ በተገቢው መወጣት አለበትም ብለዋል።
አቶ አባተ ኪሾ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት አስተያየት፤ ሃገራዊ ምክክር ለማካሄድ የታሰበው በሃገሪቱ መቀረፍ ያለበት አሳሳቢ ችግር በመኖሩ ነው። በየጊዜው እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች መንስዔም አለመግባባቶች በመኖራቸው ነው። መንግሥትም በጉዳዩ ዙሪያ ተደጋጋሚ መግለጫ አውጥቷል፤ በአንዳንድ አካባቢዎችም እርምጃ እየወሰደ ይገኛል ብለዋል።
ከሁሉም በላይ ግን አለመግባባቶቹን ለመፍታት አይነተኛ መፍትሄ የሆነውን ሃገራዊ ምክክር ለማካሄድ የተረጋጋ ሰላምና አስተማማኝ ደህንነት መፍጠር የሁሉም ኃላፊነት መሆን እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
መንግሥት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ቀዳሚ ተግባሩ በመሆኑ ሰሞኑን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት በጉዳዩ ዙሪያ ያወጣው መግለጫ የዚሁ አካል....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=71641
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
- አቶ አባተ ኪሾ
****
(ኢ ፕ ድ)
ሃገራዊ ምክክሩን ለማሳካት የተረጋጋ ሰላምና አስተማማኝ ደህንነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የቀድሞ የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አባተ ኪሾ አመለከቱ።
በሃገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ በተገቢው መወጣት አለበትም ብለዋል።
አቶ አባተ ኪሾ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት አስተያየት፤ ሃገራዊ ምክክር ለማካሄድ የታሰበው በሃገሪቱ መቀረፍ ያለበት አሳሳቢ ችግር በመኖሩ ነው። በየጊዜው እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች መንስዔም አለመግባባቶች በመኖራቸው ነው። መንግሥትም በጉዳዩ ዙሪያ ተደጋጋሚ መግለጫ አውጥቷል፤ በአንዳንድ አካባቢዎችም እርምጃ እየወሰደ ይገኛል ብለዋል።
ከሁሉም በላይ ግን አለመግባባቶቹን ለመፍታት አይነተኛ መፍትሄ የሆነውን ሃገራዊ ምክክር ለማካሄድ የተረጋጋ ሰላምና አስተማማኝ ደህንነት መፍጠር የሁሉም ኃላፊነት መሆን እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
መንግሥት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ቀዳሚ ተግባሩ በመሆኑ ሰሞኑን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት በጉዳዩ ዙሪያ ያወጣው መግለጫ የዚሁ አካል....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=71641
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ለትግራይ የሚላከው እርዳታ ለሕዝቡ ሳይሆን ለሕወሓት ታጣቂዎች እየዋለ መሆኑን ትዴፓ ገለጸ
👉 የትግራይ ሕዝብ ሰቆቃ የሚያበቃው ሕወሓታዊ አስተሳሰብ ሲጠፋ ብቻ ነው፣
*****
(ኢ ፕ ድ)
ለትግራይ ሕዝብ የሚላከው እርዳታ ለሕዝቡ ሳይሆን ሕወሓት ራሱ ላደራጃቸው መደቦችና ታጣቂዎች እየዋለ መሆኑን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ገለጸ።
የትግራይ ሕዝብ ሰቆቃ የሚያበቃው ሕወሓታዊ አስተሳሰብ ሲጠፋ ብቻ እንደሆነም ተመላክቷል።
የትግራይ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ በተለይም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል የሚላክ ቢሆንም ለሕዝቡ የሚደርስ እርዳታ የለም። እርዳታው ወደ ትግራይ ክልል ቢገባም ለሕዝቡ እየደረሰ አለመሆኑን ይልቁንም ለሕወሓት ታጣቂዎች እየተሰጠ መሆኑን ፓርቲያቸው ከተለያዩ ምንጮች እንዳረጋገጠ ገልጸዋል።
በሕዝብ ስም መነገድ የሕወሓት የዛሬ ባህሪው ብቻ ሳይሆን ከ1977 ዓ.ም ጀምሮ ያለው ታሪክ እንደሚያስረዳ የገለጹት አቶ ሙሉብርሃን፤ ወደ ትግራይ ክልል የሚገባው የምግብ፣ መድኃኒትና ሌሎች መሰል እርዳታዎች.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=71644
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
👉 የትግራይ ሕዝብ ሰቆቃ የሚያበቃው ሕወሓታዊ አስተሳሰብ ሲጠፋ ብቻ ነው፣
*****
(ኢ ፕ ድ)
ለትግራይ ሕዝብ የሚላከው እርዳታ ለሕዝቡ ሳይሆን ሕወሓት ራሱ ላደራጃቸው መደቦችና ታጣቂዎች እየዋለ መሆኑን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ገለጸ።
የትግራይ ሕዝብ ሰቆቃ የሚያበቃው ሕወሓታዊ አስተሳሰብ ሲጠፋ ብቻ እንደሆነም ተመላክቷል።
የትግራይ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ በተለይም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል የሚላክ ቢሆንም ለሕዝቡ የሚደርስ እርዳታ የለም። እርዳታው ወደ ትግራይ ክልል ቢገባም ለሕዝቡ እየደረሰ አለመሆኑን ይልቁንም ለሕወሓት ታጣቂዎች እየተሰጠ መሆኑን ፓርቲያቸው ከተለያዩ ምንጮች እንዳረጋገጠ ገልጸዋል።
በሕዝብ ስም መነገድ የሕወሓት የዛሬ ባህሪው ብቻ ሳይሆን ከ1977 ዓ.ም ጀምሮ ያለው ታሪክ እንደሚያስረዳ የገለጹት አቶ ሙሉብርሃን፤ ወደ ትግራይ ክልል የሚገባው የምግብ፣ መድኃኒትና ሌሎች መሰል እርዳታዎች.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=71644
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼