ዜና፡ በ #ሸዋሮቢት ከተማ እንድ የፖሊስ አባል ተደገለ፤ ግድያው በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ የተገደሉ የአካባቢ ባላስልጣንና የፀጥታ አካልን ብዛት ወደ አራት ከፍ አድርጎታል
ምክትል ሳጅን ያለለት ደጉ ትላንት ሰኔ 29 ቀን ማታ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 08 ቀበሌ ከምሽቱ 4 ስዓት በስራ ላይ እያሉ ባልታወቁ ግለሰቦች በጥይት መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡
የአሁኑ ግድያ በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ የተገደሉ የአካባቢ ባላስልጣንና የፀጥታ አካልን ብዛት ወደ አራት ከፍ አድርጎታል፡፡
https://rb.gy/5uzd6
ምክትል ሳጅን ያለለት ደጉ ትላንት ሰኔ 29 ቀን ማታ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 08 ቀበሌ ከምሽቱ 4 ስዓት በስራ ላይ እያሉ ባልታወቁ ግለሰቦች በጥይት መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡
የአሁኑ ግድያ በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ የተገደሉ የአካባቢ ባላስልጣንና የፀጥታ አካልን ብዛት ወደ አራት ከፍ አድርጎታል፡፡
https://rb.gy/5uzd6
በ #ትግራይ ክልል የግብር መክፈያ ጊዜ ለሶስት ወር ተራዘመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015- የትግራይ ክልል ግዚያዊ መስተዳድር ካቢኔ ትናንት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል የ2015 በጀት ዓመት ግብር መክፈያ ጊዜ ማራዘም አንዱ ሲሆን በውሳኔው መሰረት በክልሉ ግብር የሚከፈልበት ጊዜ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል።
የንግድ ፈቃድ የሚታደስበት ወቅትም በተመሳሳይ እስከ መስከረም 30 2016 ዓ.ም ተራዝሟል።
በትግራይ በነበረው ጦርነት ምክንያት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ውል ገብተው ግዴታቸውን ያልተወጡ ኮንትራክተሮች ውላቸው እንዲያሳድሱም ውሳኔ መሰጠቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015- የትግራይ ክልል ግዚያዊ መስተዳድር ካቢኔ ትናንት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል የ2015 በጀት ዓመት ግብር መክፈያ ጊዜ ማራዘም አንዱ ሲሆን በውሳኔው መሰረት በክልሉ ግብር የሚከፈልበት ጊዜ እስከ መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል።
የንግድ ፈቃድ የሚታደስበት ወቅትም በተመሳሳይ እስከ መስከረም 30 2016 ዓ.ም ተራዝሟል።
በትግራይ በነበረው ጦርነት ምክንያት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ውል ገብተው ግዴታቸውን ያልተወጡ ኮንትራክተሮች ውላቸው እንዲያሳድሱም ውሳኔ መሰጠቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
ዜና ትንታኔ፡ “የዛፍ አንበጣ የእንስሳ መኖ፣ አትክልት እና ፍራፍሬ ሳይቀር አውድሞ ባዶ ነው አስቀረን፤ ከፌደራልም ይሁን ከለጋሾች የተደረገልን ምንም አይነት ድጋፍ የለም”- የትግራይ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ
በሚሊዮን በየነ
በኢትዮጵያ በዘንድሮ የክረምት ወቅት የዛፍ አንበጣ ስጋት ሊኖር እንደሚችል በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መከላከያ ድርጅት የኢትዮጵያ ቁጥጥር ቅርንጫፍ ለአዲስ ስታንዳርድ አስታወቀ፡፡
በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መከላከያ ድርጅት የኢትዮጵያ ቁጥጥር ቅርንጫፍ ቢሮ ሃላፊ ሒወት ለማ በተለይ ለአዲስ ስታንዳርድ እንዳስታወቁት በኢትዮጵያ የዛፍ አንበጣ ስጋት ሊኖር እንደሚችል ጠቁመው የበረሃ አንበጣ ስጋት ግን የለም ብለዋል።
የትግራይ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የእጽዋት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መብራህቶም ገብረኪዳን ወልዱ በትግራይ የተባይ ወረርሽኝ ፈታኝ መሆኑን ለአዲስ ስታንዳርድ ገልፀዋል፡፡ በክልሉ ተከስቶ የነበረው የዛፍ አንበጣ እና ተምች ያስከተለው ጉዳት ለመግለጽ አስቸጋሪ እንደሆነ ገልጸው፣ ክልሉ ካለበት ወቅታዊ ችግር ጋር ተደማምሮ ሁኔታው ተስፋ አስቆራጭ መሆኑን አመላክተዋል።
https://rb.gy/3kgob
በሚሊዮን በየነ
በኢትዮጵያ በዘንድሮ የክረምት ወቅት የዛፍ አንበጣ ስጋት ሊኖር እንደሚችል በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መከላከያ ድርጅት የኢትዮጵያ ቁጥጥር ቅርንጫፍ ለአዲስ ስታንዳርድ አስታወቀ፡፡
በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መከላከያ ድርጅት የኢትዮጵያ ቁጥጥር ቅርንጫፍ ቢሮ ሃላፊ ሒወት ለማ በተለይ ለአዲስ ስታንዳርድ እንዳስታወቁት በኢትዮጵያ የዛፍ አንበጣ ስጋት ሊኖር እንደሚችል ጠቁመው የበረሃ አንበጣ ስጋት ግን የለም ብለዋል።
የትግራይ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የእጽዋት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መብራህቶም ገብረኪዳን ወልዱ በትግራይ የተባይ ወረርሽኝ ፈታኝ መሆኑን ለአዲስ ስታንዳርድ ገልፀዋል፡፡ በክልሉ ተከስቶ የነበረው የዛፍ አንበጣ እና ተምች ያስከተለው ጉዳት ለመግለጽ አስቸጋሪ እንደሆነ ገልጸው፣ ክልሉ ካለበት ወቅታዊ ችግር ጋር ተደማምሮ ሁኔታው ተስፋ አስቆራጭ መሆኑን አመላክተዋል።
https://rb.gy/3kgob
በ #ሶማሊ ክልል #ጅግጅጋ ከተማ የተነሳው የእሳት አደጋ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ሳይዛመት በቁጥጥር ስር ውሏል
በእሳት አደጋው ሳቢያ #932 ሱቆች ወድመዋል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ የተመራ ልዑክ ከፌዴራል እና ክልል ሃላፊዎች ጋር በመሆን ዛሬ ጠዋት የደረሰውን ውድመት ለመመልከት በቦታው ተገኝተዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት ከጎረቤት #ሶማሊላንድ ዋና ከተማ #ሀርጌሳ ከንቲባ የተመራ የእሳት አደጋ አጥፊ ቡድን ወደ ስፍራው አምርቷል። ባለፈው አመት በሚያዝያ ወር በሀርጌሳ ከተማ #ዋሄን ገበያ ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በደረሰበት ወቅት የሶማሊ ክልል የነፍስ አድን ቡድን ወደ ስፍራው መላኩ ይታወሳል።
አዲሱ ታይዋን ተብሎ በሚጠራው የገበያ ማእከል ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ መንስዔውእስካሁን አልታወቀም፡፡ በእሳት አደጋው ሳቢያ #932 ሱቆች ሲወድሙ የደረሰውን ጉዳት የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ተገልጧል። SRTV_Somali ያጋራው ምስል ከባድ ውድመት መድረሱን ያመላክታል፡፡
በእሳት አደጋው ሳቢያ #932 ሱቆች ወድመዋል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ የተመራ ልዑክ ከፌዴራል እና ክልል ሃላፊዎች ጋር በመሆን ዛሬ ጠዋት የደረሰውን ውድመት ለመመልከት በቦታው ተገኝተዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት ከጎረቤት #ሶማሊላንድ ዋና ከተማ #ሀርጌሳ ከንቲባ የተመራ የእሳት አደጋ አጥፊ ቡድን ወደ ስፍራው አምርቷል። ባለፈው አመት በሚያዝያ ወር በሀርጌሳ ከተማ #ዋሄን ገበያ ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በደረሰበት ወቅት የሶማሊ ክልል የነፍስ አድን ቡድን ወደ ስፍራው መላኩ ይታወሳል።
አዲሱ ታይዋን ተብሎ በሚጠራው የገበያ ማእከል ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ መንስዔውእስካሁን አልታወቀም፡፡ በእሳት አደጋው ሳቢያ #932 ሱቆች ሲወድሙ የደረሰውን ጉዳት የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ተገልጧል። SRTV_Somali ያጋራው ምስል ከባድ ውድመት መድረሱን ያመላክታል፡፡
ዜና፡ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካከል ያሉ የማንነትና የወሰን ውዝግቦች በሕዝበ ውሳኔ እንዲፈቱ እንቅስቃሴ መጀመሩን የአማራ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ
ለ30 ዓመታት የአማራና የትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱባቸው አካባቢዎች ጉዳይ በህዝበ ውሳኔ እንዲፈታና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የአማራ ክልል መንግስት ጥረት እያደረገ መሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬስን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ፡፡
የማንነትና የወሰን ጥያቄ ቢያንስ ከ30 አመታት በኋላ በህዝበ ውሳኔ እንዲፈጣ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ሕገ መንግስት ለማሻሻል ጥረቶች መጀመራቸውን አስታውሰው ጥያቄ ማቅረብ መቀጠላቸውንና በጥሩ ሁኔታ እየሄዱ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ጥያቄዎቻቸው እንዲመለሱም ዝግጁነት ስለሚያስፈልግ ክልሉን ሰላም ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አክለው ገልፀዋል፡፡
አቶ ግዛቸው በነፃነት በመዘዋወር በተመለከተ በአንዳንድ አካባቢ ችግር መኖሩን ጠቅሰው የመንገድ መዘጋት፣ የመታገት አደጋዎች፣ ግድያ፣ ውድመትና ዘረፋ የክልሉን ሰላም በመደፍረስ አሉታዊ ተጽዕኖ እያደረሱ ነው ብለዋል፡፡
https://rb.gy/ccnel
ለ30 ዓመታት የአማራና የትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱባቸው አካባቢዎች ጉዳይ በህዝበ ውሳኔ እንዲፈታና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የአማራ ክልል መንግስት ጥረት እያደረገ መሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬስን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ፡፡
የማንነትና የወሰን ጥያቄ ቢያንስ ከ30 አመታት በኋላ በህዝበ ውሳኔ እንዲፈጣ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ሕገ መንግስት ለማሻሻል ጥረቶች መጀመራቸውን አስታውሰው ጥያቄ ማቅረብ መቀጠላቸውንና በጥሩ ሁኔታ እየሄዱ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ጥያቄዎቻቸው እንዲመለሱም ዝግጁነት ስለሚያስፈልግ ክልሉን ሰላም ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አክለው ገልፀዋል፡፡
አቶ ግዛቸው በነፃነት በመዘዋወር በተመለከተ በአንዳንድ አካባቢ ችግር መኖሩን ጠቅሰው የመንገድ መዘጋት፣ የመታገት አደጋዎች፣ ግድያ፣ ውድመትና ዘረፋ የክልሉን ሰላም በመደፍረስ አሉታዊ ተጽዕኖ እያደረሱ ነው ብለዋል፡፡
https://rb.gy/ccnel
በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን መቐለ ከተማ ገባ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቅዱስ ፓትርያርክ የሚመራ ልዑካን ቡድን በትግራይ ክልል ከሚገኙ ብፁዓን አባቶች ጋር የሰላም ውይይት ለማድረግና የሰብዐዊ ድጋፍ ለማድረስ መቐለ ከተማ መግባቱን የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታወቀ።
ቀደም ሲል የተቋቋመው ኮሚቴው ወደ ክልሉ ከመጓዙ አስቀድሞ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን ወደ መቐለ እንዲጓዝና የሰብዐዊ ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ በክልሉ ከሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ውይይት አድርጎ እንዲመለስ በቋሚ ሲኖዶስ መወሰኑና ይኸው በመቐለ ሊካሔድ የታሰበው መርሐ ግብርም አስቀድሞ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲደርስ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ የልዑካን ቡድን ዛሬ ሐምሌ 3ቀን 2015 ዓ.ም ማለዳ ወደ ክልል ትግራይ መቐለ ከተማ አምርቷል።
ልዑካን ቡድኑ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በመገኘት የሰብዐዊ ድጋፉን የሚያበረክት ሲሆን በክልሉ ጊዜያዊ መንግስት በኩል በሚመቻቸው መሠረት ተፈናቃይ ወገኖችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በመርሐ ግብሩ መሰረትም ቅዱስ ፓትርያርኩና የልዑካን ቡድኑ አባላት በትግራይ ከሚገኙ ብፁዓን አባቶች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።ቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት የትግራይን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቁ ይታወሳል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቅዱስ ፓትርያርክ የሚመራ ልዑካን ቡድን በትግራይ ክልል ከሚገኙ ብፁዓን አባቶች ጋር የሰላም ውይይት ለማድረግና የሰብዐዊ ድጋፍ ለማድረስ መቐለ ከተማ መግባቱን የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታወቀ።
ቀደም ሲል የተቋቋመው ኮሚቴው ወደ ክልሉ ከመጓዙ አስቀድሞ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን ወደ መቐለ እንዲጓዝና የሰብዐዊ ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ በክልሉ ከሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ውይይት አድርጎ እንዲመለስ በቋሚ ሲኖዶስ መወሰኑና ይኸው በመቐለ ሊካሔድ የታሰበው መርሐ ግብርም አስቀድሞ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲደርስ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ የልዑካን ቡድን ዛሬ ሐምሌ 3ቀን 2015 ዓ.ም ማለዳ ወደ ክልል ትግራይ መቐለ ከተማ አምርቷል።
ልዑካን ቡድኑ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በመገኘት የሰብዐዊ ድጋፉን የሚያበረክት ሲሆን በክልሉ ጊዜያዊ መንግስት በኩል በሚመቻቸው መሠረት ተፈናቃይ ወገኖችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በመርሐ ግብሩ መሰረትም ቅዱስ ፓትርያርኩና የልዑካን ቡድኑ አባላት በትግራይ ከሚገኙ ብፁዓን አባቶች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።ቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት የትግራይን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቁ ይታወሳል።
ዜና፡ #ለሱዳን ቀውስ እልባት ለማስገኘት #በአዲስ አበባ የኢጋድ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል፤ #ኤርትራ እንደማትሳተፍ ተገልጿል፤ ተመሳሳይ ጉባኤ #ካይሮ በተናጠል አዘጋጅታለች
በሱዳን የተከሰተውን ቀውስ በዲፕሎማሲ ለመፍታት በአዲስ አበባ የኢጋድ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በጉባኤው ላይ ኤርትራ እንደማትሳተፍ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ገልጸውልኛል ሲሉ የሱዳን ላዕለዋይ ምክር ቤት ምክትል ማሊክ #አጋር መናገራቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ድረገጽ ዘግቧል። የሱዳንን ግጭት ለመፍታት በአለም አቀፍም ይሁን በቀጠናው ሀገራት በኩል የሚቀርቡ ጥረቶች የፖለቲካ #ባዛሮች በመሆናቸው ኤርትራ በባዛሩ የመሳተፍ ፍላጎት የላትም ሲሉ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ነግረውኛል ሲሉ ማሊክ አጋር መናገራቸውን ዘገባው አመላክቷል።
በሌላ ዜና በሳምንቱ አጋማሽ ተመሳሳይ ጉባኤ #ካይሮ በተናጠል ማዘጋጀቷን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
https://rb.gy/8i8zk
በሱዳን የተከሰተውን ቀውስ በዲፕሎማሲ ለመፍታት በአዲስ አበባ የኢጋድ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በጉባኤው ላይ ኤርትራ እንደማትሳተፍ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ገልጸውልኛል ሲሉ የሱዳን ላዕለዋይ ምክር ቤት ምክትል ማሊክ #አጋር መናገራቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ድረገጽ ዘግቧል። የሱዳንን ግጭት ለመፍታት በአለም አቀፍም ይሁን በቀጠናው ሀገራት በኩል የሚቀርቡ ጥረቶች የፖለቲካ #ባዛሮች በመሆናቸው ኤርትራ በባዛሩ የመሳተፍ ፍላጎት የላትም ሲሉ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ነግረውኛል ሲሉ ማሊክ አጋር መናገራቸውን ዘገባው አመላክቷል።
በሌላ ዜና በሳምንቱ አጋማሽ ተመሳሳይ ጉባኤ #ካይሮ በተናጠል ማዘጋጀቷን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
https://rb.gy/8i8zk