#ኢትዮጵያ እና #አሜሪካ ግንኙነታቸውን "ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ" ተስማሙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ረፋድ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከንን ተቀብለው አነጋግረዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ፅህፈት ቤት እንደገለው፣ ውይይታቸው በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ተስማምተዋል።
"ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት አግኝቷል" ያለው ፅህፈት ቤት "በኢኮኖሚው፣ በልማት ጥረቶች፣ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ያሉ ጉዳዮችም ትኩረት ተሰጥቶባቸዋል" በማለት ጨምሮ ገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ረፋድ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከንን ተቀብለው አነጋግረዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ፅህፈት ቤት እንደገለው፣ ውይይታቸው በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ተስማምተዋል።
"ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት አግኝቷል" ያለው ፅህፈት ቤት "በኢኮኖሚው፣ በልማት ጥረቶች፣ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ያሉ ጉዳዮችም ትኩረት ተሰጥቶባቸዋል" በማለት ጨምሮ ገልጿል።
ዜና: የ #ኢትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ በ #ቦረና እና በ #ሞያሌ አካባቢዎች 28 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ
*በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎችም ቀጣይነት እንዲኖራቸው ስልታዊ እና የተቀናጁ መሆን እነዳለባቸው ማህበሩ አሳስቧል፡፡
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ አበራ ቶላ በቦረና ዞን በድርቅ ከፍተኛ ጉዳት በደረሰባቸው አባባቢዎች በሁሉም አቅጣጫ ማለትም በውሀ አቅርቦት፣ የተረፉትን ከብቶች በማከምም ሆነ ህብረተሰቡ ወደ ተለመደ ያኗኗር ዘይቤው እንዲመለስ እና ቀጣይ ህይወቱን እንዲመራ ዘር በማቅረብም ሆነ በሌሎች ማህበራዊ እና ጤናን መሰረት ባደረጉ ድጋፎች በቅንጅት መስራት እነዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም ህብረተሰቡ በማህበራዊ፣በስነልቦናም ሆነ በኢኮኖሚ በመጎዳቱ ከምግብ እና ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ የስነ-ልቦና፣ የጤና እና ወደተለመደ ሕይወቱም በቀላሉ እንዲመለስ ጥብቅ የሆነ ክትትል እንደሚያስፈልገው የኢትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር የወጣት በጎፈቃደኞች ተወካይ የቦርድ አባል ዶ/ር አዲስአለም ሙላት አሳስባለች፡፡
https://amharic.addisstandard.com/ዜና-የትዮጲያ-ቀይ-መስቀል-ማህበር-ባለፉት/?fbclid=IwAR1GqaOjHgImIstr-jBzEr_iL9miF7L4RJPAtbJCTGNISKJO0kqHaCcTZ0k
*በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎችም ቀጣይነት እንዲኖራቸው ስልታዊ እና የተቀናጁ መሆን እነዳለባቸው ማህበሩ አሳስቧል፡፡
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ አበራ ቶላ በቦረና ዞን በድርቅ ከፍተኛ ጉዳት በደረሰባቸው አባባቢዎች በሁሉም አቅጣጫ ማለትም በውሀ አቅርቦት፣ የተረፉትን ከብቶች በማከምም ሆነ ህብረተሰቡ ወደ ተለመደ ያኗኗር ዘይቤው እንዲመለስ እና ቀጣይ ህይወቱን እንዲመራ ዘር በማቅረብም ሆነ በሌሎች ማህበራዊ እና ጤናን መሰረት ባደረጉ ድጋፎች በቅንጅት መስራት እነዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም ህብረተሰቡ በማህበራዊ፣በስነልቦናም ሆነ በኢኮኖሚ በመጎዳቱ ከምግብ እና ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ የስነ-ልቦና፣ የጤና እና ወደተለመደ ሕይወቱም በቀላሉ እንዲመለስ ጥብቅ የሆነ ክትትል እንደሚያስፈልገው የኢትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር የወጣት በጎፈቃደኞች ተወካይ የቦርድ አባል ዶ/ር አዲስአለም ሙላት አሳስባለች፡፡
https://amharic.addisstandard.com/ዜና-የትዮጲያ-ቀይ-መስቀል-ማህበር-ባለፉት/?fbclid=IwAR1GqaOjHgImIstr-jBzEr_iL9miF7L4RJPAtbJCTGNISKJO0kqHaCcTZ0k
Addis Standard
ዜና: የኢትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ በቦረና እና በሞያሌ አካባቢዎች 28 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ
የኢትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ አበራ ቶላ፡፡ ፎቶ፣የትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎችም ቀጣይነት እንዲኖራቸው ስልታዊ እና የተቀናጁ መሆን እነዳለባቸው ማህበሩ አሳስቧል፡፡ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6/ 2015 ዓ.ም - የኢትዮጲያ ቀይ መስቀል ማህበር በድርቅ ክፉኛ ለተጎዱ የቦረና እና የሞያሌ አካባቢዎች ወደ […]
ዜና: #የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለሦስት እና አራት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች ላይ የጣለውን እግድ እንዲያነሳ #ኢሰመኮ ጠየቀ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ የከተማ አስተዳደሩ ባለሦስት እና አራት እግር (ባጃጅ) አነስተኛ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ላይ ያስቀመጠውን ሙሉ እገዳ በማንሳት ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ሊያመቻች ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጠይቋል። በሁሉም የከተማዋ ክፍሎች ላልተወሰነ ጊዜ ገደብ መጣሉ ሕገ-መንግሥታዊ ጥበቃ የተደረገላቸው መብቶች አደጋ ላይ የጣለ እርምጃ ነው ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳስቧል።
ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል እገዳው በከተማዋ ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚ በመሆኑ የባጃጅ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎቹንና ቤተሰባቸውን ብቻ ሳይሆን፣ እጅግ በርካታ ተጠቃሚዎችንም ችግር ላይ እንደጣለ መረዳቱን ያመላከተው የኮሚሽኑ መግለጫ መንግሥት ሰዎች ሥራቸውን እና የመረጡትን መተዳደሪያ ያለአግባብ እንዳያጡ ማድረግን ጨምሮ የመረጡትን እና የተቀበሉትን ሥራ እንዲሠሩ የማስቻል ኃላፊነት አለበት ሲል አሳስቧል።
ኮሚሽኑ እገዳውን ተከትሎ የደረሱትን አቤቱታዎች መሠረት በማድረግ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዎችን ማነጋገሩን በመግለጫው አስታውቆ ኃላፊዎቹ በከተማዋ ወደ #10 ሺህ የሚገመቱ “የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በከተማ አስተዳደሩ የሥራ ፈቃድ ያልተሰጣቸው መሆኑን፣ እንደ አንድ አገልግሎት ሰጪ በከተማዋ አሠራር ሥርዓት ያልተዘረጋላቸው መሆኑን፣ እንዲሁም ሌሎችም ተዛማጅ ችግሮች” መኖራቸውን እንደገለጹለት አመላክቷል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና-የአዲስ-አበባ-ከተማ-አስተዳደር-ባለሦ/?fbclid=IwAR0KaHrFqm5WXn_43hYyN7rNH_d4SEV6M2gmEqnxzfT1HxaafMQoyDSqSqs
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ የከተማ አስተዳደሩ ባለሦስት እና አራት እግር (ባጃጅ) አነስተኛ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ላይ ያስቀመጠውን ሙሉ እገዳ በማንሳት ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ሊያመቻች ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጠይቋል። በሁሉም የከተማዋ ክፍሎች ላልተወሰነ ጊዜ ገደብ መጣሉ ሕገ-መንግሥታዊ ጥበቃ የተደረገላቸው መብቶች አደጋ ላይ የጣለ እርምጃ ነው ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳስቧል።
ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል እገዳው በከተማዋ ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚ በመሆኑ የባጃጅ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎቹንና ቤተሰባቸውን ብቻ ሳይሆን፣ እጅግ በርካታ ተጠቃሚዎችንም ችግር ላይ እንደጣለ መረዳቱን ያመላከተው የኮሚሽኑ መግለጫ መንግሥት ሰዎች ሥራቸውን እና የመረጡትን መተዳደሪያ ያለአግባብ እንዳያጡ ማድረግን ጨምሮ የመረጡትን እና የተቀበሉትን ሥራ እንዲሠሩ የማስቻል ኃላፊነት አለበት ሲል አሳስቧል።
ኮሚሽኑ እገዳውን ተከትሎ የደረሱትን አቤቱታዎች መሠረት በማድረግ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዎችን ማነጋገሩን በመግለጫው አስታውቆ ኃላፊዎቹ በከተማዋ ወደ #10 ሺህ የሚገመቱ “የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በከተማ አስተዳደሩ የሥራ ፈቃድ ያልተሰጣቸው መሆኑን፣ እንደ አንድ አገልግሎት ሰጪ በከተማዋ አሠራር ሥርዓት ያልተዘረጋላቸው መሆኑን፣ እንዲሁም ሌሎችም ተዛማጅ ችግሮች” መኖራቸውን እንደገለጹለት አመላክቷል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና-የአዲስ-አበባ-ከተማ-አስተዳደር-ባለሦ/?fbclid=IwAR0KaHrFqm5WXn_43hYyN7rNH_d4SEV6M2gmEqnxzfT1HxaafMQoyDSqSqs
Addis Standard
ዜና: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለሦስት እና አራት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች ላይ የጣለውን እግድ እንዲያነሳ ኢሰመኮ ጠየቀ
ፎቶ ከፋይል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ የከተማ አስተዳደሩ ባለሦስት እና አራት እግር (ባጃጅ) አነስተኛ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ላይ ያስቀመጠውን ሙሉ እገዳ በማንሳት ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ሊያመቻች ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጠይቋል። በሁሉም የከተማዋ ክፍሎች ላልተወሰነ ጊዜ ገደብ መጣሉ […]
ዜና: #በኢትዮጵያ ጦርነቱ ያደረሰውን ጉዳት እና የሰብአዊ መብት ጥሰት በተመለከተ #ብሊንከን በጥንቃቄ ሲመልሱ በሰላም ስምምነቱ ላይ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7/ 2015 ዓ.ም - ትላንት ረቡዕ መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት #የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጥንቃቄ በተሞላበት፣ ላለማስቀየም ጥረት በታከለበት መንገድ በኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አመታት በተካሄደው ጦርነት የተፈጸመውን ግፍ እና ጥፋት አስመልክተው ምላሽ ሰጥተዋል። ትኩረት ማስቀየሻ በሚመስል መልኩ አጽንኦት ሰጥተው #ከፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት በኋላ ግፉ እና ጥፋቱ መቀነሱ ላይ አተኩረዋል። በተጨማሪም የሰላም ስምምነቱን የፈረሙት ሁለቱም አካላት፣ #ፌደራል መንግስቱ እና #የህወሓት ሀይሎች የተፈጸመውን ሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ያስከተለውን ጉዳት አምነዋል፣ ተቀብለዋል ሲሉ ተደምጠዋል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት #በትግራይ የተፈጸመውን ከጦርነት ጋር የተያያዘ ሰብአዊ መብት ጥሰት የዘር ፍጅት ወይንም ጀኖሳይድ መሆኑን የሚያትተውን በ2021 የተደረሰውን ሪፖርት መደርደሪያው ላይ እንዲቀመጥ እና እንዳይቀርብ አድርጎታል ሲል ብሊንከን ወደ አዲስ አበባ ከመምጣታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ #ፎሬን ፖሊሲ መጽሔት ይፋ አድርጓል። ይህንንም ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ሶስት ዲፕሎማት መስማቱን መጽሔቱ በዘገባው አስታውቋል።
#አዲስ ስታንዳርድ ብሊንከን በአዲስ አበባ #ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ተገኝቶ ይህንኑ ጉዳይ ጠይቋቸው ነበር፤ ለምን ሪፖርቱ ይፋ አልተደረገም? ሲል። ጥያቄውን በቀጥታ ከመመለስ ይልቅ በጦርነቱ ወቅት በንጹሃን ላይ የተፈጸሙ ሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሀገራችው በተደጋጋሚ በግልጽ ስትኮንን እንደነበር እና በሁሉም ጎራ ያሉ ጥቃቱን የፈጸሙ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማቅረቧን አውስተው ይህንን ጉዳይ ከአንድ አመት በፊት እኔ እራሴ ገልጨው ነበር ብለዋል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና-በኢትዮጵያ-ጦርነቱ-ያደረሰውን-ጉዳት/?fbclid=IwAR2Xx9qTDDo7cYc5PX9R8uigJDUUIXSycdPpqNgWVzVOP6Q7U-7JEOd_Eu4
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7/ 2015 ዓ.ም - ትላንት ረቡዕ መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት #የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጥንቃቄ በተሞላበት፣ ላለማስቀየም ጥረት በታከለበት መንገድ በኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አመታት በተካሄደው ጦርነት የተፈጸመውን ግፍ እና ጥፋት አስመልክተው ምላሽ ሰጥተዋል። ትኩረት ማስቀየሻ በሚመስል መልኩ አጽንኦት ሰጥተው #ከፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት በኋላ ግፉ እና ጥፋቱ መቀነሱ ላይ አተኩረዋል። በተጨማሪም የሰላም ስምምነቱን የፈረሙት ሁለቱም አካላት፣ #ፌደራል መንግስቱ እና #የህወሓት ሀይሎች የተፈጸመውን ሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ያስከተለውን ጉዳት አምነዋል፣ ተቀብለዋል ሲሉ ተደምጠዋል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት #በትግራይ የተፈጸመውን ከጦርነት ጋር የተያያዘ ሰብአዊ መብት ጥሰት የዘር ፍጅት ወይንም ጀኖሳይድ መሆኑን የሚያትተውን በ2021 የተደረሰውን ሪፖርት መደርደሪያው ላይ እንዲቀመጥ እና እንዳይቀርብ አድርጎታል ሲል ብሊንከን ወደ አዲስ አበባ ከመምጣታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ #ፎሬን ፖሊሲ መጽሔት ይፋ አድርጓል። ይህንንም ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ሶስት ዲፕሎማት መስማቱን መጽሔቱ በዘገባው አስታውቋል።
#አዲስ ስታንዳርድ ብሊንከን በአዲስ አበባ #ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ተገኝቶ ይህንኑ ጉዳይ ጠይቋቸው ነበር፤ ለምን ሪፖርቱ ይፋ አልተደረገም? ሲል። ጥያቄውን በቀጥታ ከመመለስ ይልቅ በጦርነቱ ወቅት በንጹሃን ላይ የተፈጸሙ ሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሀገራችው በተደጋጋሚ በግልጽ ስትኮንን እንደነበር እና በሁሉም ጎራ ያሉ ጥቃቱን የፈጸሙ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማቅረቧን አውስተው ይህንን ጉዳይ ከአንድ አመት በፊት እኔ እራሴ ገልጨው ነበር ብለዋል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና-በኢትዮጵያ-ጦርነቱ-ያደረሰውን-ጉዳት/?fbclid=IwAR2Xx9qTDDo7cYc5PX9R8uigJDUUIXSycdPpqNgWVzVOP6Q7U-7JEOd_Eu4
Addis Standard
ዜና: በኢትዮጵያ ጦርነቱ ያደረሰውን ጉዳት እና የሰብአዊ መብት ጥሰት በተመለከተ በጥንቃቄ ምላሽ የሰጡት ብሊንከን በሰላም ስምምነቱ ላይ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል
ፎቶ ከብሊንከን የትዊተር ገጽ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7/ 2015 ዓ.ም - ትላንት ረቡዕ መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጥንቃቄ በተሞላበት፣ ላለማስቀየም ጥረት በታከለበት መንገድ በኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አመታት በተካሄደው ጦርነት የተፈጸመውን ግፍ እና ጥፋት አስመልክተው ምላሽ […]
የ #አማራ ባንክ #መርሀባ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱን መጋቢት 9 በይፋ የሚመረቅ መኾኑን ገለጸ
የአማራ ባንክ መርሀባ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱን መጋቢት 9 በይፋ የሚመረቅ መኾኑን ገልጿል።
ባንኩ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት በተለያዩ የአገልግሎት አማራጮች ለደንበኞቹ ቅርብ በመኾን ላይ መኾኑን ተገልጿል። በአፍሪካ መሪ እና ጨዋታ ቀያሪ እንዲሁም ተወዳዳሪ የመኾን አላማን አንግቦ መነሳቱን ባንኩ ገልጿል።
እስካሁን በተጓዘባቸው መንገዶች ከፍተኛ የካፒታል አቅምን በማጎልበት ተወዳዳሪ ለመኾን የሚያስችል ቁመና በመገንባት ላይ ሲሆን ተወዳዳሪ ለመኾንና አላማውን ለማሳካት ቀልጣፋ፣ በሁሉም ተደራሽ ፣ ጊዜውን ያማከለ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል ተብሏል።
በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን በባንክ ወለድ ምክንያት ከባንክ የራቁ ደንበኞችን ፍላጎት ለማርካት በወለድ ከሚሰጡት መደበኛ የባንክ አገልግሎት በኅብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት በማግኘቱ በከፍተኛ ኹኔታ በማስፋት እና በማደግ ላይ እንደሚግርኝ ባንኩ ገልጿል ።
ባንኩ በአሁኑ ጊዜ በሁሉም የመደበኛ የባንክ አገልግሎት በሚሰጡ ከ230 ቅርንጫፎች በላይ በመስኮት በኩል የተሟላ የመርሀባ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት በመስጠት ላይ መገኘቱን ባንኩ አመላክቷል።
እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ድረስ 30 ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጡ ቅርንጫፎችን ለመክፈት በዝግጅት ላይ መኾኑን ባንኩ ገልጿል።
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid02HWzstL2BYijczMBUPFrpka5ovx8PBo9ATYzJhtbvoYqdmZKt5mJdbbmSdp5rGYF1l
የአማራ ባንክ መርሀባ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱን መጋቢት 9 በይፋ የሚመረቅ መኾኑን ገልጿል።
ባንኩ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት በተለያዩ የአገልግሎት አማራጮች ለደንበኞቹ ቅርብ በመኾን ላይ መኾኑን ተገልጿል። በአፍሪካ መሪ እና ጨዋታ ቀያሪ እንዲሁም ተወዳዳሪ የመኾን አላማን አንግቦ መነሳቱን ባንኩ ገልጿል።
እስካሁን በተጓዘባቸው መንገዶች ከፍተኛ የካፒታል አቅምን በማጎልበት ተወዳዳሪ ለመኾን የሚያስችል ቁመና በመገንባት ላይ ሲሆን ተወዳዳሪ ለመኾንና አላማውን ለማሳካት ቀልጣፋ፣ በሁሉም ተደራሽ ፣ ጊዜውን ያማከለ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል ተብሏል።
በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን በባንክ ወለድ ምክንያት ከባንክ የራቁ ደንበኞችን ፍላጎት ለማርካት በወለድ ከሚሰጡት መደበኛ የባንክ አገልግሎት በኅብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት በማግኘቱ በከፍተኛ ኹኔታ በማስፋት እና በማደግ ላይ እንደሚግርኝ ባንኩ ገልጿል ።
ባንኩ በአሁኑ ጊዜ በሁሉም የመደበኛ የባንክ አገልግሎት በሚሰጡ ከ230 ቅርንጫፎች በላይ በመስኮት በኩል የተሟላ የመርሀባ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት በመስጠት ላይ መገኘቱን ባንኩ አመላክቷል።
እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ድረስ 30 ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጡ ቅርንጫፎችን ለመክፈት በዝግጅት ላይ መኾኑን ባንኩ ገልጿል።
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid02HWzstL2BYijczMBUPFrpka5ovx8PBo9ATYzJhtbvoYqdmZKt5mJdbbmSdp5rGYF1l
በህገወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ ከ47 ሺህ ሊትር በላይ ቤንዚን በቁጥጥር ስር ዋለ
መነሻውን #ጅቡቲ ያደረገ የነዳጅ ማመላለሻ ቦቲ ከተመደበለት መዳረሻ ውጪ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያለው 47 ሺህ ሊትር ቤንዚን በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
የአዲስ አበባ #ቃሊቲ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪው ስምሪት ከተሰጠው ቦታ ውጪ ወደ ደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በመጓዝ ላይ እያለ #ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ይህን ህገወጥ ድርጊት የፈጸመው አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የተያዘው ቤንዚንም በነዳጅ አቅራቢው ድርጅት ማደያ ተራግፏል፡፡
የኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ኢ.ፕ.ድ
መነሻውን #ጅቡቲ ያደረገ የነዳጅ ማመላለሻ ቦቲ ከተመደበለት መዳረሻ ውጪ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያለው 47 ሺህ ሊትር ቤንዚን በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
የአዲስ አበባ #ቃሊቲ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪው ስምሪት ከተሰጠው ቦታ ውጪ ወደ ደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በመጓዝ ላይ እያለ #ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ይህን ህገወጥ ድርጊት የፈጸመው አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የተያዘው ቤንዚንም በነዳጅ አቅራቢው ድርጅት ማደያ ተራግፏል፡፡
የኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ኢ.ፕ.ድ
በ #አዲስአበባ የኃይል መቆራረጥ በውሃ ምርት እና ስርጭት ላይ ችግር እንደፈጠረበት የከተማዋ ውኃና ፍሳሽ ባለስልጣን ገለጸ
ከመጋቢት 1 ቀን 2015ዓ.ም. ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ቀናት በባለሥልጣኑ የውሃ ጉድጓዶች እና የግፊት ጣቢያዎች ላይ በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ማጋጠሙን በባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሠርካለም ጌታቸው ተናግረዋል፡፡
ይህም በባለስልጣኑ የውሃ ምርት እና ስርጭት ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን ነው ዳይሬክተሯ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የገለጹት፡፡
በኃይል መቆራረጡ ምክንያት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣3፣ 5፣ 12፣ 13 እና 14፤ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣2፣3፣4፣5፣6 እና 10 እንዲሁም በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2፣3፣4፣5፣6፣9፣10፣11፣12፣13 እና 14 የውሃ አቅርቦቱ ተቋርጧል ነው ያሉት፡፡
እንዲሁም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣9 እና 10፤ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 13፤ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 6 እና ከወረዳ 9 እስከ 11 የውሃ አቅርቦቱ መቋረጡን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 15፤ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 11 እና 12፤ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 እና 5 በከፊል እና ወረዳ 9 በሙሉ እንዲሁም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ምክንያት የውሃ አገልግሎቱ መቋረጡን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid02Zzv31WrbQaDLESbRttmrHHyK3uRjY9WyDcLcGCto85vcAnmfVN5ZM6oWwnT7oKUul
ከመጋቢት 1 ቀን 2015ዓ.ም. ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ቀናት በባለሥልጣኑ የውሃ ጉድጓዶች እና የግፊት ጣቢያዎች ላይ በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ማጋጠሙን በባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሠርካለም ጌታቸው ተናግረዋል፡፡
ይህም በባለስልጣኑ የውሃ ምርት እና ስርጭት ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን ነው ዳይሬክተሯ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የገለጹት፡፡
በኃይል መቆራረጡ ምክንያት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣3፣ 5፣ 12፣ 13 እና 14፤ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣2፣3፣4፣5፣6 እና 10 እንዲሁም በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2፣3፣4፣5፣6፣9፣10፣11፣12፣13 እና 14 የውሃ አቅርቦቱ ተቋርጧል ነው ያሉት፡፡
እንዲሁም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣9 እና 10፤ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 13፤ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 6 እና ከወረዳ 9 እስከ 11 የውሃ አቅርቦቱ መቋረጡን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ከወረዳ 1 እስከ 15፤ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 11 እና 12፤ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 እና 5 በከፊል እና ወረዳ 9 በሙሉ እንዲሁም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ምክንያት የውሃ አገልግሎቱ መቋረጡን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid02Zzv31WrbQaDLESbRttmrHHyK3uRjY9WyDcLcGCto85vcAnmfVN5ZM6oWwnT7oKUul
ዜና፡ #በሱማሌ ክልል የተከሰተው ድርቅ የበርካቶችን ህይወት ቀጥፏል፤ የወረዳው አመራር “ከአቅማቸው በላይ” መሆኑን ቢያምኑም የሟቾችን ብዛት ግን ውድቅ አድርጓል
በመድኃኔ እቁባሚካኤል እና በብሩክ አለሙ
በሶማሌ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ዞኖች አንዱ በሆነው በዳዋ ዞን፣ ከተለያዩ ወረዳዎች ተፈናቅለው በሞያሌ ወረዳ በሚገኙ ሁለት የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች የተጠለሉ ከ18 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተፈናቃዮች ለአዲስ ስታንዳርድ ተናገሩ። ተፈናቃዮቹ ያልተለመዱ ነገሮችን ለመመገብ እየተገደዱ ነው። የወረዳው ኃላፊዎች የችግሩን አሳሳቢነት በማመን “ከአቅማችን በላይ ሆኗል” ብለዋል።
አዲስ ስታንዳርድ በሞያሌ አቅራቢያ መለብ ቀበሌ በሚገኘው ሃርቦር ተፈናቃይ መጠለያ ባደረገው ጉብኝት በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ያገኛቸው አንድ ተፈናቃይ አፋጣኝ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀው በማዕከሉ አካባቢ እሳቸው የሚያውቁት ከስምንት በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተናግሯል።
ቤተሰቦቹን ለመርዳት የ12ኛ ክፍል ትምህርቱን አቋርጦ ከሞያሌ ከተማ ወደ ኤል ጎፋ መጠለያ ጣቢያ የገባው ወጣት አሊ እንደሚናገረው በስፍራው እርዳታ እየደረሰ አይደለም፡፡
https://amharic.addisstandard.com/ዜና፡-በሱማሌ-ክልል-የተከሰተው-ድርቅ-የበ/?fbclid=IwAR0mJCEkrfpl97RPj5SnUkxhhn6hPKNFnD4kimjQHnjJJGZCPexqu2x53qI
በመድኃኔ እቁባሚካኤል እና በብሩክ አለሙ
በሶማሌ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ዞኖች አንዱ በሆነው በዳዋ ዞን፣ ከተለያዩ ወረዳዎች ተፈናቅለው በሞያሌ ወረዳ በሚገኙ ሁለት የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች የተጠለሉ ከ18 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተፈናቃዮች ለአዲስ ስታንዳርድ ተናገሩ። ተፈናቃዮቹ ያልተለመዱ ነገሮችን ለመመገብ እየተገደዱ ነው። የወረዳው ኃላፊዎች የችግሩን አሳሳቢነት በማመን “ከአቅማችን በላይ ሆኗል” ብለዋል።
አዲስ ስታንዳርድ በሞያሌ አቅራቢያ መለብ ቀበሌ በሚገኘው ሃርቦር ተፈናቃይ መጠለያ ባደረገው ጉብኝት በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ያገኛቸው አንድ ተፈናቃይ አፋጣኝ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀው በማዕከሉ አካባቢ እሳቸው የሚያውቁት ከስምንት በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተናግሯል።
ቤተሰቦቹን ለመርዳት የ12ኛ ክፍል ትምህርቱን አቋርጦ ከሞያሌ ከተማ ወደ ኤል ጎፋ መጠለያ ጣቢያ የገባው ወጣት አሊ እንደሚናገረው በስፍራው እርዳታ እየደረሰ አይደለም፡፡
https://amharic.addisstandard.com/ዜና፡-በሱማሌ-ክልል-የተከሰተው-ድርቅ-የበ/?fbclid=IwAR0mJCEkrfpl97RPj5SnUkxhhn6hPKNFnD4kimjQHnjJJGZCPexqu2x53qI
Addis Standard
ዜና፡ በሱማሌ ክልል የተከሰተው ድርቅ የበርካቶችን ህይወት ቀጥፏል፤ የወረዳው አመራር “ከአቅማቸው በላይ” መሆኑን ቢያምኑም የሟቾችን ብዛት ግን ውድቅ አድርጓል
ሞያሌ ወረዳ ኤል ጎፋ መጠለያ በመድኃኔ እቁባሚካኤል @Medihane እና በብሩክ አለሙ @Birukalemu21 ሞያሌ፣ መጋቢት 8/ 2015 ዓ.ም፡- በሶማሌ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ዞኖች አንዱ በሆነው በዳዋ ዞን፣ ከተለያዩ ወረዳዎች ተፈናቅለው በሞያሌ ወረዳ በሚገኙ ሁለት የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች የተጠለሉ ከ18 በላይ ሰዎች መሞታቸውን ተፈናቃዮች […]
በ #አዲስአበባ ከተማ ተቋርጦ የቆየው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀመሮ ይጀመራል
በመዲናዋ ተቋርጦ የቆየው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀመሮ በ138 የስምሪት መሥመሮች እንደሚጀምር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ አሰታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎትን አሰመልክቶ ዛሬ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ቢሮ ሀላፊ አቶ ምትኩ አስማረ እንደተናገሩት፤ በከተማ ውስጥ እየሰሩ ያሉት ሁሉም የባጃጅ አሽከርካሪዎች የትራንስፖርት ቢሮው በሚያወጣቸው መመሪያ መሠረት በ123 ማህበራት ሥር አገልግሎት ይሠጣሉ።
በከተማዋ መደበኛ ትራንስፖርት በማይገኝበት አካባቢዎች ውስጥ ከ 0.9 እስከ 2.45 ኪሎ ሜትሪ ራዲየስ ብቻ በ5 ብር ታሪፍ አገልግሎት እንዲሰጡም ተወስኗል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በስምንት ክፍለ ከተሞች ስር በሚገኙ 123 ማህበራት ስር የሚገኙ 9ሺህ 550 ባጃጅ አሽከርካሪዎች ጊዜያዊ ታፔላ ተሰጥቷቸዋል በማለትም አብራርተዋል።
አቶ ምትኩ እንደሚሉት ከ2001 ጀምሮ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ታርጋቸውን በከተማዋ ያላወጡ ናቸው።
ቢሮው ባለፈው ሳምንት የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎቶቹን ያቋረጠው በተደጋጋሚ የሚከሰቱ አደጋዎችንና ወንጀሎችን ለመከላከል አሠራርና ሕግ በማስፈለጉ መሆኑን ሀላፊው ጨምረው ገልጸዋል።
ፎቶ: አዲስ ፎርቹን
በመዲናዋ ተቋርጦ የቆየው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀመሮ በ138 የስምሪት መሥመሮች እንደሚጀምር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ አሰታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎትን አሰመልክቶ ዛሬ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ቢሮ ሀላፊ አቶ ምትኩ አስማረ እንደተናገሩት፤ በከተማ ውስጥ እየሰሩ ያሉት ሁሉም የባጃጅ አሽከርካሪዎች የትራንስፖርት ቢሮው በሚያወጣቸው መመሪያ መሠረት በ123 ማህበራት ሥር አገልግሎት ይሠጣሉ።
በከተማዋ መደበኛ ትራንስፖርት በማይገኝበት አካባቢዎች ውስጥ ከ 0.9 እስከ 2.45 ኪሎ ሜትሪ ራዲየስ ብቻ በ5 ብር ታሪፍ አገልግሎት እንዲሰጡም ተወስኗል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በስምንት ክፍለ ከተሞች ስር በሚገኙ 123 ማህበራት ስር የሚገኙ 9ሺህ 550 ባጃጅ አሽከርካሪዎች ጊዜያዊ ታፔላ ተሰጥቷቸዋል በማለትም አብራርተዋል።
አቶ ምትኩ እንደሚሉት ከ2001 ጀምሮ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ታርጋቸውን በከተማዋ ያላወጡ ናቸው።
ቢሮው ባለፈው ሳምንት የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎቶቹን ያቋረጠው በተደጋጋሚ የሚከሰቱ አደጋዎችንና ወንጀሎችን ለመከላከል አሠራርና ሕግ በማስፈለጉ መሆኑን ሀላፊው ጨምረው ገልጸዋል።
ፎቶ: አዲስ ፎርቹን
ዜና፡ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳዳርን እንዲመሩ መረጠ
የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮምቴ ትላንት ማምሻውን የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮምቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳን የክልሉ ግዜያዊ አስተዳደር እንዲመሩ መምረጣቸውን ሶስት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።
አቶ ጌታቸው ረዳ ከ41 የማዕከላዊ ኮምቴ አባላት 18 የድምጽ ብልጫ አግኝተው መመረጣቸውን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል።
ነገር ግን የፌደራል መንግስት ይሁኝታ ይሰጠው እንደሆነ ገና የሚታይ ነው።
የተቋቋመው ግዜያዊ አስተዳደር ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ/ም የተመረጠውን የትግራይ ክልላዊ መንግስትን የሚተካ ሲሆን በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ጥቅምት 23 ቀን 2015ዓ/ም ከፌደራል መንግስት ጋር በተደረገው ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ዋና ከሆኑ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የሰላም ስምምነቱ ሰነድ አንቀጽ 10 አካታች ግዜያዊ አስተዳደር መመስረት አንዳለበት ይደነግጋል።
https://amharic.addisstandard.com/%E1%8B%9C%E1%8A%93%E1%8D%A1-%E1%8B%A8%E1%88%85%E1%8B%88%E1%88%93%E1%89%B5-%E1%88%9B%E1%8A%A5%E1%8A%A8%E1%88%8B%E1%8B%8A-%E1%8A%AE%E1%88%9A%E1%89%B4-%E1%8A%A0%E1%89%B6-%E1%8C%8C%E1%89%B3%E1%89%B8/
የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮምቴ ትላንት ማምሻውን የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮምቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳን የክልሉ ግዜያዊ አስተዳደር እንዲመሩ መምረጣቸውን ሶስት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።
አቶ ጌታቸው ረዳ ከ41 የማዕከላዊ ኮምቴ አባላት 18 የድምጽ ብልጫ አግኝተው መመረጣቸውን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል።
ነገር ግን የፌደራል መንግስት ይሁኝታ ይሰጠው እንደሆነ ገና የሚታይ ነው።
የተቋቋመው ግዜያዊ አስተዳደር ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ/ም የተመረጠውን የትግራይ ክልላዊ መንግስትን የሚተካ ሲሆን በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ጥቅምት 23 ቀን 2015ዓ/ም ከፌደራል መንግስት ጋር በተደረገው ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ዋና ከሆኑ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የሰላም ስምምነቱ ሰነድ አንቀጽ 10 አካታች ግዜያዊ አስተዳደር መመስረት አንዳለበት ይደነግጋል።
https://amharic.addisstandard.com/%E1%8B%9C%E1%8A%93%E1%8D%A1-%E1%8B%A8%E1%88%85%E1%8B%88%E1%88%93%E1%89%B5-%E1%88%9B%E1%8A%A5%E1%8A%A8%E1%88%8B%E1%8B%8A-%E1%8A%AE%E1%88%9A%E1%89%B4-%E1%8A%A0%E1%89%B6-%E1%8C%8C%E1%89%B3%E1%89%B8/
Addis Standard
ዜና፡ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳዳርን እንዲመሩ መረጠ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9/ 2015 ዓ.ም:- የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮምቴ ትላንት ማምሻውን የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮምቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳን የክልሉ ግዜያዊ አስተዳደር እንዲመሩ መምረጣቸውን ሶስት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ። አቶ ጌታቸው ረዳ ከ41 የማዕከላዊ ኮምቴ አባላት 18 […]
አገልግሎት ያቆሙ 18 የአዲስ አበባ ቀላል ባቡሮች ወደ አገልግሎት ሊመለሱ ነው
#ቻይና ባቀረበችው የመለዋወጫ ድጋፍ አገልግሎት መስጠት ያቆሙ 18 ባቡሮች ወደ አገልግሎት እንደሚመለሱ የ #አዲስአበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት ድርጅት አስታወቀ፡፡
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ሙሉ ቀን አሰፋ እንደገለጹት፤ ቻይና የአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር የመለዋወጫ ድጋፍ በማድረጓ አገልግሎት መስጠት ያቆሙ 18 ባቡሮችን ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡሮች በመለዋወጫ እጥረት፣ በኃይል መቆራረጥና በተለያዩ ችግሮች ሥራ ሲያቆሙ መለዋወጫቸው ከውጭ ሃገራት ተገዝቶ የሚገባ በመሆኑ ለተወሰኑ ጊዜያት መዘግየት ተፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል።
የኃይል መቆራረጥ ችግሮች እንዳይከሰቱ እንዲሁም በጥራት ጉድለት ምክንያት ለረጅም ጊዜ የቆዩ ኬብሎችን የመቀየር ሥራ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ጋር በመሆን እየተሠራ መሆኑን ኢንጂነር ሙሉቀን ጠቁመዋል፡፡
እንደ ኢንጂነር ሙሉቀን ገለጻ፤ ለባቡር የሚውለውን የኃይል ማቀባበያ ሲስተሞችን በየጊዜው መፈተሽ እንዲሁም የባቡር ሀዲዶችን ንቅለ ተከላ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሚሠሩት ባቡሮች አማካኝነት በርካታ ሕዝብ በአዲስ አበባ የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኘ ነው፡፡ አሁን ላይ በመዲናዋ ያሉት ባቡሮች በቀን 60ሺ እንዲሁም በዓመት 41 ሚሊዮን ሰዎችን ያጓጉዛሉ፡፡
ከፍተኛ የባቡር ትራንስፖርት ፍላጎት የሚስተዋልበት መስመር ከሃያት ተነስቶ ጦር ኃይሎች የሚደርሰው መስመር መሆኑን ገልጸው፤...
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid023mDioYbqL6rSBQjzRAi3S9sCMeZZCkEjdF3qvCQkTF4YxCEPK482GJTyGMvi3Qd6l
#ቻይና ባቀረበችው የመለዋወጫ ድጋፍ አገልግሎት መስጠት ያቆሙ 18 ባቡሮች ወደ አገልግሎት እንደሚመለሱ የ #አዲስአበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት ድርጅት አስታወቀ፡፡
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ሙሉ ቀን አሰፋ እንደገለጹት፤ ቻይና የአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር የመለዋወጫ ድጋፍ በማድረጓ አገልግሎት መስጠት ያቆሙ 18 ባቡሮችን ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡሮች በመለዋወጫ እጥረት፣ በኃይል መቆራረጥና በተለያዩ ችግሮች ሥራ ሲያቆሙ መለዋወጫቸው ከውጭ ሃገራት ተገዝቶ የሚገባ በመሆኑ ለተወሰኑ ጊዜያት መዘግየት ተፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል።
የኃይል መቆራረጥ ችግሮች እንዳይከሰቱ እንዲሁም በጥራት ጉድለት ምክንያት ለረጅም ጊዜ የቆዩ ኬብሎችን የመቀየር ሥራ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ጋር በመሆን እየተሠራ መሆኑን ኢንጂነር ሙሉቀን ጠቁመዋል፡፡
እንደ ኢንጂነር ሙሉቀን ገለጻ፤ ለባቡር የሚውለውን የኃይል ማቀባበያ ሲስተሞችን በየጊዜው መፈተሽ እንዲሁም የባቡር ሀዲዶችን ንቅለ ተከላ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሚሠሩት ባቡሮች አማካኝነት በርካታ ሕዝብ በአዲስ አበባ የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኘ ነው፡፡ አሁን ላይ በመዲናዋ ያሉት ባቡሮች በቀን 60ሺ እንዲሁም በዓመት 41 ሚሊዮን ሰዎችን ያጓጉዛሉ፡፡
ከፍተኛ የባቡር ትራንስፖርት ፍላጎት የሚስተዋልበት መስመር ከሃያት ተነስቶ ጦር ኃይሎች የሚደርሰው መስመር መሆኑን ገልጸው፤...
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid023mDioYbqL6rSBQjzRAi3S9sCMeZZCkEjdF3qvCQkTF4YxCEPK482GJTyGMvi3Qd6l
ሰሞኑን የጣለው ከባድ ዝናብ #አዲስአበባ ካሏት 137 መጋቢ መስመሮች ውስጥ በ50ዎቹ ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን የመዲናዋ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ
ሰሞኑን የጣለው ከባድ ዝናብ በ50 ከፍተኛ የሃይል መስመሮች ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ሰሞኑን በመዲናዋ የተከሰተው የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ ምክንያት የተፈጠረ መሆኑን የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ገበየው ልካሳ ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተከሰተውን የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ አስመልክቶ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ የሰጡት ዋና ስራ አስፈፃሚው መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም በጣለው ከባድ ዝናብ ብቻ መዲናዋ ካሏት 137 መጋቢ መስመሮች ውስጥ በ50ዎቹ ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
ችግሩን ለመፍታትም የሃይል አቅርቦት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ ትራንስፎርመሮችን የመቀየርና አስቸኳይ ጥገና እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በፕሮጀክቶች ምክንያት በእቅድ ይቋረጥ የነበረው ሃይል እንዲቆም ተደርጓልም ብለዋል።
ከዝናቡ በተጨማሪ የመሰረተ ልማት ስራዎች ግንባታና በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈፀም ስርቆትና መሰል ድርጊቶች ለሃይል መቆራረጡ ምክንያት መሆናቸውን ያስታወቁት ዋና ስራ አስፈጻሚው ለተፈጠረው የሃይል አቅርቦት መቆራረጥ የከተማዋን ነዋሪዎች ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡
አ. ኤም ኤን
ሰሞኑን የጣለው ከባድ ዝናብ በ50 ከፍተኛ የሃይል መስመሮች ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ሰሞኑን በመዲናዋ የተከሰተው የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ ምክንያት የተፈጠረ መሆኑን የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ገበየው ልካሳ ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተከሰተውን የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ አስመልክቶ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ የሰጡት ዋና ስራ አስፈፃሚው መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም በጣለው ከባድ ዝናብ ብቻ መዲናዋ ካሏት 137 መጋቢ መስመሮች ውስጥ በ50ዎቹ ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
ችግሩን ለመፍታትም የሃይል አቅርቦት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ ትራንስፎርመሮችን የመቀየርና አስቸኳይ ጥገና እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በፕሮጀክቶች ምክንያት በእቅድ ይቋረጥ የነበረው ሃይል እንዲቆም ተደርጓልም ብለዋል።
ከዝናቡ በተጨማሪ የመሰረተ ልማት ስራዎች ግንባታና በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈፀም ስርቆትና መሰል ድርጊቶች ለሃይል መቆራረጡ ምክንያት መሆናቸውን ያስታወቁት ዋና ስራ አስፈጻሚው ለተፈጠረው የሃይል አቅርቦት መቆራረጥ የከተማዋን ነዋሪዎች ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡
አ. ኤም ኤን
#ኢትዮጵያ- ታዋቂው የአካባቢ ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር ከዚህ አለም በሞት ተለዩ
ታዋቂው የአካባቢ ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሄር በ83 አመታቸው ዛሬ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን ቤተሰቦችና ወዳጆቻቸው አስታወቁ።
የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር ተወልደ በብዝሃ ህይወት፣ በማህበረሰብ (የገበሬዎች መብት) ላይ ያከናወኗቸውን ጠቃሚ ምርምሮች እና ቁጥጥር ካልተደረገላቸው የዘረመል ምህንድስና ሰብሎች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ባደረጉት ከፍተኛ ትግል ለዓለም የሚጠቅሙ ሥራዎችን ሰርተዋል።
የ “አማራጭ የኖቤል ሽልማት” እና “የምድራችን ጀግና” ተሸላሚ የሆኑት ዶ/ር ተወልደ የሶስት ሴት ልጆች አባት ነበሩ።
ታዋቂው የአካባቢ ሳይንቲስት እና ተመራማሪ ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሄር በ83 አመታቸው ዛሬ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን ቤተሰቦችና ወዳጆቻቸው አስታወቁ።
የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር ተወልደ በብዝሃ ህይወት፣ በማህበረሰብ (የገበሬዎች መብት) ላይ ያከናወኗቸውን ጠቃሚ ምርምሮች እና ቁጥጥር ካልተደረገላቸው የዘረመል ምህንድስና ሰብሎች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ባደረጉት ከፍተኛ ትግል ለዓለም የሚጠቅሙ ሥራዎችን ሰርተዋል።
የ “አማራጭ የኖቤል ሽልማት” እና “የምድራችን ጀግና” ተሸላሚ የሆኑት ዶ/ር ተወልደ የሶስት ሴት ልጆች አባት ነበሩ።
ዜና፡ #አሜሪካ #የኢትዮጵያ፣ #የኤርትራ እና #የአማራ ሃይሎች በትግራዩ ጦርነት “በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል” መፈፀማቸውን ገለፀች፤ ሁሉም ሀይሎች ደግሞ “የጦር ወንጀል” ፈፅመዋል ብላለች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12/ 2015 ዓ.ም፡– አሜሪካ የ2022 አመት በአለም ላይ የታዩ የሰብአዊ መብት ጉዳዮቹን በተመለከተ በትላንትናው ዕለት ይፋ በተደረገችበት ሪፖርት የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የአማራ ሃይሎች #በትግራዩ ጦርነት “በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል” መፈፀማቸውን አስታወቀች፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በትግራይ ተጀምሮ ለሁለት አመት በዘለቀው እና ወደ አማራ እና #አፋር በተስፋፋው ጦርነት የትግራይ ሀይሎችን ጨምሮ ሁሉም ሀይሎች “የጦር ወንጀል” ፈጽመዋል ስትል ገልፃለች።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንቶኒ ብሊንከን ሪፖርቱን ይፋ ሲያደርጉ “ከነዚህ ወነጀሎች ውስጥ አብዛኛዎቹ ድንገት ወይም በጦርነት የተከሰቱ ብቻ ሳይሆኑ ታስቦ እና ሆን ተብሎ የተፈፀሙ ናቸው” ብለዋል፡፡
መስራቤታቸው ህጎችን እና እውነታውን በጥንቃቄ ካስተዋለ በኋላ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሃይሎች፣ የኤርትራ መከላከያ ሃይሎች፣ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሃይሎች እና የአማራ ሃይሎች በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በነበረው ጦርነት የጦር ወንጀሎችን መፈጸሙን በተመለከተ ድምዳሜ ላይ ደርሰናል ሲሉ አስታውቀዋል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና፡-አሜሪካ-የኢትዮጵያ፣-የኤርትራ-እና/?fbclid=IwAR1LwZhGPHPe2HytwPwS-W6xEzn5A4gykwUmejQEAmZd_OpndLWC-xgSHJ0
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12/ 2015 ዓ.ም፡– አሜሪካ የ2022 አመት በአለም ላይ የታዩ የሰብአዊ መብት ጉዳዮቹን በተመለከተ በትላንትናው ዕለት ይፋ በተደረገችበት ሪፖርት የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የአማራ ሃይሎች #በትግራዩ ጦርነት “በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል” መፈፀማቸውን አስታወቀች፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በትግራይ ተጀምሮ ለሁለት አመት በዘለቀው እና ወደ አማራ እና #አፋር በተስፋፋው ጦርነት የትግራይ ሀይሎችን ጨምሮ ሁሉም ሀይሎች “የጦር ወንጀል” ፈጽመዋል ስትል ገልፃለች።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንቶኒ ብሊንከን ሪፖርቱን ይፋ ሲያደርጉ “ከነዚህ ወነጀሎች ውስጥ አብዛኛዎቹ ድንገት ወይም በጦርነት የተከሰቱ ብቻ ሳይሆኑ ታስቦ እና ሆን ተብሎ የተፈፀሙ ናቸው” ብለዋል፡፡
መስራቤታቸው ህጎችን እና እውነታውን በጥንቃቄ ካስተዋለ በኋላ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሃይሎች፣ የኤርትራ መከላከያ ሃይሎች፣ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሃይሎች እና የአማራ ሃይሎች በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በነበረው ጦርነት የጦር ወንጀሎችን መፈጸሙን በተመለከተ ድምዳሜ ላይ ደርሰናል ሲሉ አስታውቀዋል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና፡-አሜሪካ-የኢትዮጵያ፣-የኤርትራ-እና/?fbclid=IwAR1LwZhGPHPe2HytwPwS-W6xEzn5A4gykwUmejQEAmZd_OpndLWC-xgSHJ0
Addis Standard
ዜና፡ አሜሪካ የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የአማራ ሃይሎች በትግራዩ ጦርነት “በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል” መፈፀማቸውን ገለፀች፤ ሁሉም ተፋላሚ ሀይሎች “የጦር ወንጀል” ፈፅመዋል ብላለች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12/ 2015 ዓ.ም፡– አሜሪካ የ2022 አመት በአለም ላይ የታዩ የሰብአዊ መብት ጉዳዮቹን በተመለከተ በትላንትናው ዕለት ይፋ በተደረገችበት ሪፖርት የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የአማራ ሃይሎች በትግራዩ ጦርነት “በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል” መፈፀማቸውን አስታወቀች፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በትግራይ ተጀምሮ ለሁለት አመት በዘለቀው እና ወደ አማራ እና […]
ዜና፡ ኢትዮጵያ የአሜሪካ መንግስት ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ያወጣውን መግለጫ እንደማትቀበለው አስታወቀች፤ ግዜውን ያልጠበቀ፣ አባባሽ እና አግላይ ሲል ኮንኗል
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በትግራይ ተጀምሮ ወደ አማራ እና አፋር ክልል የተዛመተውን ጦርነት አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት እንደማይቀበለው አስታወቀ።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በጦርነቱ ከፍተኛ ወንጀል ተፈጽሟል ማለቱን እንደማይቀበለው ያስታወቀው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ ግዜውን ያልጠበቀ፣ አባባሽ እና አግላይ ሲል ኮንኗል። ሪፖርቱ አንድን ወገን ላይ በማነጣጠር አላግባብ የወነጀለ ነው ሲል ተችቷል።
አስገድዶ መድፈር፣ ጾታዊ ጥቃት መሰል ወንጀሎች ተፈጽመው እያለ ግልጽነት በሌለው ምክንያት የአሜሪካን መንግስት መግለጫ አንድን ወገን በተለዩ ወንጀሎች ላይ ተጠያቂ ላለማድረግ ያለመ ነው ሲል ገልጿል።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አማራጮችን ለመለየት ብሔራዊ ምክክር ለመጀመር በተዘጋጀችበት ወቅት ላይ የወጣ በመሆኑም መግለጫው ወቅቱን ያልጠበቀ ነው ሲል ኮንኗል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና፡-ኢትዮጵያ-የአሜሪካ-መንግስት-ውጭ-ጉ/?fbclid=IwAR0oy1OuggeRt4uUS3NbPTpcYPAm5yHUozPt09sV5-zlojred3ktEaaOXRs
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በትግራይ ተጀምሮ ወደ አማራ እና አፋር ክልል የተዛመተውን ጦርነት አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት እንደማይቀበለው አስታወቀ።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በጦርነቱ ከፍተኛ ወንጀል ተፈጽሟል ማለቱን እንደማይቀበለው ያስታወቀው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ ግዜውን ያልጠበቀ፣ አባባሽ እና አግላይ ሲል ኮንኗል። ሪፖርቱ አንድን ወገን ላይ በማነጣጠር አላግባብ የወነጀለ ነው ሲል ተችቷል።
አስገድዶ መድፈር፣ ጾታዊ ጥቃት መሰል ወንጀሎች ተፈጽመው እያለ ግልጽነት በሌለው ምክንያት የአሜሪካን መንግስት መግለጫ አንድን ወገን በተለዩ ወንጀሎች ላይ ተጠያቂ ላለማድረግ ያለመ ነው ሲል ገልጿል።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አማራጮችን ለመለየት ብሔራዊ ምክክር ለመጀመር በተዘጋጀችበት ወቅት ላይ የወጣ በመሆኑም መግለጫው ወቅቱን ያልጠበቀ ነው ሲል ኮንኗል።
https://amharic.addisstandard.com/ዜና፡-ኢትዮጵያ-የአሜሪካ-መንግስት-ውጭ-ጉ/?fbclid=IwAR0oy1OuggeRt4uUS3NbPTpcYPAm5yHUozPt09sV5-zlojred3ktEaaOXRs
Addis Standard
ዜና፡ ኢትዮጵያ የአሜሪካ መንግስት ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ያወጣውን መግለጫ እንደማትቀበለው አስታወቀች፤ ግዜውን ያልጠበቀ፣ አባባሽ እና አግላይ ሲል ኮንኗል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12/ 2015 ዓ.ም፡– የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በትግራይ ተጀምሮ ወደ አማራ እና አፋር ክልል የተዛመተውን ጦርነት አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት እንደማይቀበለው አስታወቀ። የአሜሪካ ውጭጉዳይ መስሪያ ቤት በጦርነቱ ከፍተኛ ወንጀል ተፈጽሟል ማለቱን እንደማይቀበለው ያስታወቀው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር […]
ሰሞኑን በሞግዚቷ የተሰረቀችው የ2 ዓመት ሕጻን ሶሊያና ዳንኤል በ #ሱሉልታ መገኘቷን ፖሊስ ገለጸ
ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ሕጻን ሶሊያና ዳንኤል ከብሄራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር በተደረገ ክትትል በሱሉልታ ክፍለ ከተማ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ሕጻን ሶሊያና ሳሪስ አዲስ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሐሙስ መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ረፋድ ላይ ቤዛ በቀለ በተባለችው የቤት ሰራተኛቸው ተሰርቃ ስለመወሰዷ በተለያዩ ማሕበራዊ ትስስር ገፆች መረጃው ሲሰራጭ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ በሕጻኗ ወላጆች የቀረበለትን አቤቱታ ተቀብሎ ከብሄራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀትና ወደተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞችና አካባቢዎች በመሄድ ጭምር አስፈላጊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል፡፡
በዚህም ቤዛ በቀለ ዛሬ ሱሉልታ ክፍለ ከተማ ወሰርቢ ወረዳ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሕጻን ሶሊያና ዳንኤልን ደብቃ በተቀመጠችበት በቁጥጥር ስር መዋሏን ነው ፖሊስ ያሳወቀው፡፡
ተጠርጣሪዋ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ፥ 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ መሰወሯን ተናራለች፡፡
በወንጀሉ ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል፡፡
ኤፍ ቢ ሲ
ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ሕጻን ሶሊያና ዳንኤል ከብሄራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር በተደረገ ክትትል በሱሉልታ ክፍለ ከተማ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ሕጻን ሶሊያና ሳሪስ አዲስ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሐሙስ መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ረፋድ ላይ ቤዛ በቀለ በተባለችው የቤት ሰራተኛቸው ተሰርቃ ስለመወሰዷ በተለያዩ ማሕበራዊ ትስስር ገፆች መረጃው ሲሰራጭ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ በሕጻኗ ወላጆች የቀረበለትን አቤቱታ ተቀብሎ ከብሄራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀትና ወደተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞችና አካባቢዎች በመሄድ ጭምር አስፈላጊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል፡፡
በዚህም ቤዛ በቀለ ዛሬ ሱሉልታ ክፍለ ከተማ ወሰርቢ ወረዳ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሕጻን ሶሊያና ዳንኤልን ደብቃ በተቀመጠችበት በቁጥጥር ስር መዋሏን ነው ፖሊስ ያሳወቀው፡፡
ተጠርጣሪዋ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ፥ 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ መሰወሯን ተናራለች፡፡
በወንጀሉ ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል፡፡
ኤፍ ቢ ሲ
ዜና፡ #የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ብፁዕ አቡነ #አረጋዊ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13/ 2015 ዓ.ም - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የብፁዕ ወቅዱስ #ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተገለጸ። ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ ከሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ እንደነበሩ ተጠቁሟል።
ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቢቆዩም ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል ሲሉ #የቤተክርስቲያኗ መገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13/ 2015 ዓ.ም - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የብፁዕ ወቅዱስ #ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተገለጸ። ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ ከሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ እንደነበሩ ተጠቁሟል።
ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቢቆዩም ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል ሲሉ #የቤተክርስቲያኗ መገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።