በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተካፋይ የነበሩ የትግራይ እግርኳስ ክለቦችን ከመክሰም ለመታደግ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ሊካሄድ ነው
*********************
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው መቀለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲና ስሁል ሽረ ከኢዋይ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ለ60 ቀን የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ይፋ አድርገዋል።
ክለቦቹን ለመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ፕሮግራሞች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብሩ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በሚገኙበት መክፈቻውን አዲስ አበባ መዝጊያውን መቀሌ በማድረግ ይካሄዳል ተብሏል።
በፉአድ እድሪስ
*********************
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው መቀለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲና ስሁል ሽረ ከኢዋይ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ለ60 ቀን የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ይፋ አድርገዋል።
ክለቦቹን ለመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ፕሮግራሞች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብሩ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በሚገኙበት መክፈቻውን አዲስ አበባ መዝጊያውን መቀሌ በማድረግ ይካሄዳል ተብሏል።
በፉአድ እድሪስ
👍34👏24❤11👎10
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 75.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ
*****************************
ኢትዮ ቴሌኮም የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በተመለከተ ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ነው።
ተቋሙ በ2015 በጀት ዓመት 75.8 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልፀዋል።
ተቋሙ 18.7 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ተነስቷል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0E4zmQq9ju1SRKgH7YzFiB8ggcg15PKpErhccggqJCvk3ReeModN1tmmSHZKmxeCvl
*****************************
ኢትዮ ቴሌኮም የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በተመለከተ ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ነው።
ተቋሙ በ2015 በጀት ዓመት 75.8 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልፀዋል።
ተቋሙ 18.7 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ተነስቷል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0E4zmQq9ju1SRKgH7YzFiB8ggcg15PKpErhccggqJCvk3ReeModN1tmmSHZKmxeCvl
👍56👏16👎14❤5
በአውሮፓ የተከሰተው ከፍተኛ የሙቀት መጠን አስጊ ደረጃ ደርሷል
***********************
በተለይ በደቡባዊ አውሮፓ በቀጣይ ሳምንታት የሙቀት መጠኑ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ ዘግቧል።
የጣሊያኗ ደሴት ሳርዲኒያ እስከ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ የደረሰ ሲሆን፤ በቀጣይ 10 ቀናት ከፍተኛ ሙቀት ሊከሰት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ እየተሰጠ ነው።
ስፔን በተመሳሳይ ተከታታይ የሆነ የሙቀት ማዕበል የገጠማት ሲሆን፤ በተለይ በደቡባዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሙቀት መጠኑ 44 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ደርሷል።
በተጨማሪ፥ በስፔኗ ደሴት ላፓልማ እና በግሪክ የሰደድ እሳት ተከስቷል።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ የሙቀት መጠኑ 49 ዲግሪ ሴንቲግሬድ መድረሱም ነው የተገለፀው።
የሙቀት መጠኑ መጨመር በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው ጠቋሚ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ማህበር አሳስቧል።
***********************
በተለይ በደቡባዊ አውሮፓ በቀጣይ ሳምንታት የሙቀት መጠኑ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ ዘግቧል።
የጣሊያኗ ደሴት ሳርዲኒያ እስከ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ የደረሰ ሲሆን፤ በቀጣይ 10 ቀናት ከፍተኛ ሙቀት ሊከሰት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ እየተሰጠ ነው።
ስፔን በተመሳሳይ ተከታታይ የሆነ የሙቀት ማዕበል የገጠማት ሲሆን፤ በተለይ በደቡባዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሙቀት መጠኑ 44 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ደርሷል።
በተጨማሪ፥ በስፔኗ ደሴት ላፓልማ እና በግሪክ የሰደድ እሳት ተከስቷል።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ የሙቀት መጠኑ 49 ዲግሪ ሴንቲግሬድ መድረሱም ነው የተገለፀው።
የሙቀት መጠኑ መጨመር በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው ጠቋሚ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ማህበር አሳስቧል።
👍62👎8👏6❤5
በሀገሪቱ በቂ የሆነ የስኳር መድሀኒት ስርጭት እና መጠባበቂያ አለ - የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት
**********************************************
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የስኳር ህሙማን መድሀኒት በተለይም “Humulin70/30” የተባለው የመድሃኒት ዓይነት በቀላሉ ለማግኘት መቸገራቸውን ሲገልጹ ተስተውሏል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢቢሲ ሳይበር የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ሰለሞን ንጉሴን አነጋግሯል።
አቶ ሰለሞን ተቋሙ በግዢ የሚያቀርባቸው ህይወት አድን እና መሰረታዊ መድሃኒቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከውጭ እንደሚያስገባ ገልጸው፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ መሰናክሎች የአቅርቦት መቆራረጥን እንደሚፈጥሩ ጠቁመዋል።
ነገር ግን ተቋሙ ዜጎች እድሜ ልክ የሚወስዷቸው መድሃኒቶችን ቅድሚያ በመስጠት የማቅረብ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ባለፉት 2 ዓመታት ምንም አይነት የስኳር መድሃኒት አቅርቦት ችግር እንዳልገጠመ ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0t55HjqaAQpiAnZvgZYiv6gazoDWwfeatPQmxnPE5Pk8c263fBxZWNYdzNgcf4V5Fl
**********************************************
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የስኳር ህሙማን መድሀኒት በተለይም “Humulin70/30” የተባለው የመድሃኒት ዓይነት በቀላሉ ለማግኘት መቸገራቸውን ሲገልጹ ተስተውሏል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢቢሲ ሳይበር የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ሰለሞን ንጉሴን አነጋግሯል።
አቶ ሰለሞን ተቋሙ በግዢ የሚያቀርባቸው ህይወት አድን እና መሰረታዊ መድሃኒቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከውጭ እንደሚያስገባ ገልጸው፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ መሰናክሎች የአቅርቦት መቆራረጥን እንደሚፈጥሩ ጠቁመዋል።
ነገር ግን ተቋሙ ዜጎች እድሜ ልክ የሚወስዷቸው መድሃኒቶችን ቅድሚያ በመስጠት የማቅረብ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ባለፉት 2 ዓመታት ምንም አይነት የስኳር መድሃኒት አቅርቦት ችግር እንዳልገጠመ ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0t55HjqaAQpiAnZvgZYiv6gazoDWwfeatPQmxnPE5Pk8c263fBxZWNYdzNgcf4V5Fl
👍74👎18❤15
ከ20 በላይ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው
***********
በአገሪቱ የሚገኙ ከ20 በላይ ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በማስመረቅ ላይ ይገኛሉ።
በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መካከል አዲስ አበባ፣ ወለጋ፣ ደብረብርሃን፣ አርባምንጭ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ እና ሰመራ ዩኒቨርስቲዎች ይገኙበታል፡፡
***********
በአገሪቱ የሚገኙ ከ20 በላይ ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በማስመረቅ ላይ ይገኛሉ።
በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መካከል አዲስ አበባ፣ ወለጋ፣ ደብረብርሃን፣ አርባምንጭ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ እና ሰመራ ዩኒቨርስቲዎች ይገኙበታል፡፡
👍82❤16👎8👏2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው
*******************
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ73ኛ ጊዜ ተማሪዎችን እያስመረቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 868 ተማሪዎቹን በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
በምረቃ መርሃግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨም ሌሎች የስራ ኃላፊዎች እና እንግዶች ተገኝተዋል።
በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት ከሚመረቁ ተማሪዎች መካከል 35 በመቶ ሴቶች ናቸው።
ዩኒቨርስቲው በ18 ካምፓሶቹ በ276 የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02A2dbK9sRryJqcR7tzP1r41jFLg16BV8kpfvF26XXgA91PbujcbhSwc7AwqZ6abm9l
*******************
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ73ኛ ጊዜ ተማሪዎችን እያስመረቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 868 ተማሪዎቹን በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
በምረቃ መርሃግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨም ሌሎች የስራ ኃላፊዎች እና እንግዶች ተገኝተዋል።
በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት ከሚመረቁ ተማሪዎች መካከል 35 በመቶ ሴቶች ናቸው።
ዩኒቨርስቲው በ18 ካምፓሶቹ በ276 የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02A2dbK9sRryJqcR7tzP1r41jFLg16BV8kpfvF26XXgA91PbujcbhSwc7AwqZ6abm9l
👍39❤10👎8👏5
የጅማ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ያስመረቃቸው መንትዮች
****************************
የጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል።
ከተመራቂዎችም መካከል በጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሶስት የተለያዩ መንትዮች ተመርቀዋል።
ተመራቂ ሜላት ደቻሳ በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ የተመረቀች ሲሆን መንትያዋ ሜሮን ደቻሳ በአርክቴክቸር የትምህርት ዘርፍ መመረቅ ችላለች።
የጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መረጃ እንደሚያመለክተው፣ እዩኤል ብዙአየሁ እና ኢዩአኪ ብዙአየሁ የተባሉ መንትዮች በኮምፒዩተር ሳይንስ የተመረቁ ተማሪዎች ናቸው።
በተመሳሳይ፣ አሊይ በዳሶ እና አማን በዳሶ በሲቪል ምህንድስና መመረቃቸውን የጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መረጃ ያመለክታል።
****************************
የጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል።
ከተመራቂዎችም መካከል በጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሶስት የተለያዩ መንትዮች ተመርቀዋል።
ተመራቂ ሜላት ደቻሳ በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ የተመረቀች ሲሆን መንትያዋ ሜሮን ደቻሳ በአርክቴክቸር የትምህርት ዘርፍ መመረቅ ችላለች።
የጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መረጃ እንደሚያመለክተው፣ እዩኤል ብዙአየሁ እና ኢዩአኪ ብዙአየሁ የተባሉ መንትዮች በኮምፒዩተር ሳይንስ የተመረቁ ተማሪዎች ናቸው።
በተመሳሳይ፣ አሊይ በዳሶ እና አማን በዳሶ በሲቪል ምህንድስና መመረቃቸውን የጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መረጃ ያመለክታል።
👍81❤30👎8👏5
ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው(ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ተሰጣት
*******************
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው(ጂጂ) የክብር ዶክትሬት በዛሬው ዕለት ሰጥቷታል።
የክብር ዶክተሬቱን በወላጅ እናቷ በወ/ሮ ተናኜ አማካኝነት ተቀብላለች።
ድምፃዊት፣ ገጣሚ፣ የዜማ ደራሲ እና ተዋናይት የሆነችው ሁለገቧ አርቲስት ጂጂ፣ የሀገሯን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነጥበብ የአዊን ህዝብ ቋንቋ እና ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ ነው የክብር ዶክትሬቱ የተበረከተላት።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።
*******************
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው(ጂጂ) የክብር ዶክትሬት በዛሬው ዕለት ሰጥቷታል።
የክብር ዶክተሬቱን በወላጅ እናቷ በወ/ሮ ተናኜ አማካኝነት ተቀብላለች።
ድምፃዊት፣ ገጣሚ፣ የዜማ ደራሲ እና ተዋናይት የሆነችው ሁለገቧ አርቲስት ጂጂ፣ የሀገሯን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነጥበብ የአዊን ህዝብ ቋንቋ እና ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ ነው የክብር ዶክትሬቱ የተበረከተላት።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።
👍86❤21👎9
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአቶ ቢኒያም በለጠ እና አርቲስት ደበበ እሸቱ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ
**********************************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተሰማሩበት መስክ አገርንና ህዝብን በቀናነት ላገለገሉት ለአቶ ቢኒያም በለጠ እና አርቲስት ደበበ እሸቱ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል።
ዩኒቨርሲቲው ለመቄዶኒያ በጐ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢኒያም በለጠ ላከናወኗቸው የበጎ አድራጎ ስራዎች የክብር ዶክትሬት በዛሬው እለት የሰጠ ሲሆን፣ አቶ ቢኒያም በሰው ልጆች ደህንነት ለሀገር የማይታካ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በመድረኩ ተገልጿል።
የክብር ዶክትሬት የተሰጣቸው አርቲስት ደበበ እሸቱም የህይወቱ ጥሪ በሆነው የኪነ ጥበብ ዘርፍ ለአገር ትልቅ ውለታ መዋሉ ለዚህ ክብር እንዳበቃው ተነግሯል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ ፣ በማታና በርቀት ትምህርት መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 642 የቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ ተማሪዎችን በሚሊኒየም አዳራሽ እያስመረቀ ነው።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ እንግዶችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
**********************************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተሰማሩበት መስክ አገርንና ህዝብን በቀናነት ላገለገሉት ለአቶ ቢኒያም በለጠ እና አርቲስት ደበበ እሸቱ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል።
ዩኒቨርሲቲው ለመቄዶኒያ በጐ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢኒያም በለጠ ላከናወኗቸው የበጎ አድራጎ ስራዎች የክብር ዶክትሬት በዛሬው እለት የሰጠ ሲሆን፣ አቶ ቢኒያም በሰው ልጆች ደህንነት ለሀገር የማይታካ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በመድረኩ ተገልጿል።
የክብር ዶክትሬት የተሰጣቸው አርቲስት ደበበ እሸቱም የህይወቱ ጥሪ በሆነው የኪነ ጥበብ ዘርፍ ለአገር ትልቅ ውለታ መዋሉ ለዚህ ክብር እንዳበቃው ተነግሯል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ ፣ በማታና በርቀት ትምህርት መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 642 የቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ ተማሪዎችን በሚሊኒየም አዳራሽ እያስመረቀ ነው።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ እንግዶችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
👍104❤35👎13👏8
54 ኮርሶችን A+ ያገኘው ተመራቂ ተማሪ የወርቅ ሜዳሊያውን ለእናቱ አበረከተ
**********************************
54 ኮርሶችን A+ ያገኘው ተመራቂ ተማሪ "ለእኔ ሳይሆን ስለእኔ ብዙ ለከፈለችው ወላጅ እናቴ" ይሁንልኝ በማለት ሜዳልያውን እንደተቀበለ ወደ እናቱ ሮጦ በመሄድ አጥልቆላታል።
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነው ተመራቂ ተማሪ ዳግም ተስፋዬ ይህን አስደናቂ ተግባር ፈጸሟል።
ተመራቂው በዕፅዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከወሰዳቸው 64 ኮርሶች 54ቱን ኮርሶች A+ በማምጣት ተሸላሚ ሆኗል።
በወንደሰን ሞላ
**********************************
54 ኮርሶችን A+ ያገኘው ተመራቂ ተማሪ "ለእኔ ሳይሆን ስለእኔ ብዙ ለከፈለችው ወላጅ እናቴ" ይሁንልኝ በማለት ሜዳልያውን እንደተቀበለ ወደ እናቱ ሮጦ በመሄድ አጥልቆላታል።
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነው ተመራቂ ተማሪ ዳግም ተስፋዬ ይህን አስደናቂ ተግባር ፈጸሟል።
ተመራቂው በዕፅዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከወሰዳቸው 64 ኮርሶች 54ቱን ኮርሶች A+ በማምጣት ተሸላሚ ሆኗል።
በወንደሰን ሞላ
👍284❤84👏45👎9