በሕገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ የነበረ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ወርቅ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተያዘ
**********************
በሕገ- ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ የነበረ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ወርቅ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪው 1 ኪሎ ግራም ወርቅ በሻንጣ ውስጥ ደብቆ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በሕገ-ወጥ መንገድ ከሀገር በማስወጣት ላይ እንዳለ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ፍተሻ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እያተጣራበት እንደሚገኝ ታውቋል።
የተያዘው ሕገ-ወጥ ወርቅም በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ በኤግዚቢትነት ተይዞ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል።
**********************
በሕገ- ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ የነበረ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ወርቅ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ተጠርጣሪው 1 ኪሎ ግራም ወርቅ በሻንጣ ውስጥ ደብቆ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በሕገ-ወጥ መንገድ ከሀገር በማስወጣት ላይ እንዳለ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ፍተሻ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እያተጣራበት እንደሚገኝ ታውቋል።
የተያዘው ሕገ-ወጥ ወርቅም በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ በኤግዚቢትነት ተይዞ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል።
👍59❤4👏4
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሸበሌይ ሪዞርት ግንባታ ስፍራን ጎበኙ
*************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት ከ‘ገበታለትውልድ’ የልማት ቁልፍ ስፍራዎች አንዱ ሆኖ በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የሸበሌይ ሪዞርት ግንባታ ስፍራ ጎብኝተዋል።
ከጂግጂጋ ከተማ 29 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 385 ሄክታር በሚሸፍን ስፍራ ላይ የሚገነባው ኘሮጀክት የጂግጂጋ ከተማ እና አካባቢውን ወደ ግምባር ቀደም የቱሪዝም መዳረሻነት የሚለውጠው የቱሪዝም ስራ አንድ አካል ነው።
ይህ ስራ ኢትዮጵያ የያዘችውን የዘላቂ ቱሪዝም ስራ እና የኢኮኖሚ እድገት መንገድ አጉልቶ የሚያሳይ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
*************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት ከ‘ገበታለትውልድ’ የልማት ቁልፍ ስፍራዎች አንዱ ሆኖ በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የሸበሌይ ሪዞርት ግንባታ ስፍራ ጎብኝተዋል።
ከጂግጂጋ ከተማ 29 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 385 ሄክታር በሚሸፍን ስፍራ ላይ የሚገነባው ኘሮጀክት የጂግጂጋ ከተማ እና አካባቢውን ወደ ግምባር ቀደም የቱሪዝም መዳረሻነት የሚለውጠው የቱሪዝም ስራ አንድ አካል ነው።
ይህ ስራ ኢትዮጵያ የያዘችውን የዘላቂ ቱሪዝም ስራ እና የኢኮኖሚ እድገት መንገድ አጉልቶ የሚያሳይ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍77❤19👏4👎3
የመስቃንና ማረቆ ወንድማማች ሕዝቦች የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም እየተካሔደ ነው
***********************
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስቃን እና ማረቆ ወንድማማች ህዝቦች የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም በኢንሴኖ ከተማ እየተካሔደ ነው።
በመስቃን እና ማረቆ ወንድማማች ሕዝቦች የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የብሔረሰቦች ም/ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የመስቃን ቤተ ጉራጌ እና የማረቆ ብሔረሰብ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመስቃን እና የማረቆ ወንድማማች ሕዝቦች ለዘመናት ያቆዩትን የጋራ እሴት በጽኑ መሰረት ላይ ለመገንባት ያለመ የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም ዛሬ በመካሔድ ላይ መሆኑን ከክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሪ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
***********************
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስቃን እና ማረቆ ወንድማማች ህዝቦች የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም በኢንሴኖ ከተማ እየተካሔደ ነው።
በመስቃን እና ማረቆ ወንድማማች ሕዝቦች የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የብሔረሰቦች ም/ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የመስቃን ቤተ ጉራጌ እና የማረቆ ብሔረሰብ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመስቃን እና የማረቆ ወንድማማች ሕዝቦች ለዘመናት ያቆዩትን የጋራ እሴት በጽኑ መሰረት ላይ ለመገንባት ያለመ የእርቅ ማጽኛ ፕሮግራም ዛሬ በመካሔድ ላይ መሆኑን ከክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሪ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍35❤4
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በባሕር ዳር ከተማ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን የግንባታ ሂደት ተዘዋውረው ተመለከቱ
************************
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ የፌዴራል መንግሥት ልዑክ ከትናንት ጀምሮ በክልሉ የልማት ሥራዎች ዙሪያ ከክልሉ መንግሥት አመራሮች ጋር እየመከረ ነው።
ከጠዋት ጀምሮ ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እንዲሁም የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ የሚገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የአዲሱን የዓባይ ድልድይ የግንባታ ሂደት የተመለከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው ብሔራዊ ባንክ የሚያስገነባውን ሕንጻም በቦታው ተገኝተው አስጀምረዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎቹ የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታን መመልከታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
************************
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ የፌዴራል መንግሥት ልዑክ ከትናንት ጀምሮ በክልሉ የልማት ሥራዎች ዙሪያ ከክልሉ መንግሥት አመራሮች ጋር እየመከረ ነው።
ከጠዋት ጀምሮ ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እንዲሁም የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ የሚገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የአዲሱን የዓባይ ድልድይ የግንባታ ሂደት የተመለከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው ብሔራዊ ባንክ የሚያስገነባውን ሕንጻም በቦታው ተገኝተው አስጀምረዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎቹ የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታን መመልከታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
👍32❤14👏1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሶማሊ ክልል 2ኛው ዙር የጂግጂጋ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትን ጎበኙ
**************************
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ እና ከሌሎች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በዛሬው ዕለት 2ኛው ዙር የጂግጂጋ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
**************************
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ እና ከሌሎች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በዛሬው ዕለት 2ኛው ዙር የጂግጂጋ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
❤32👍26👏7