የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ከአስቶን ቪላ፤ ሻምፒዮኑ ማን ሲቲ ከብራይተን ዛሬ ምሽት የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ተጠባቂ ናቸው
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር የሊጉ መሪ ሊቨርፑል በሜዳው ምሽት 5 ሰዓት ከአስቶን ቪላ ጋር ይጫወታል።
በፕሪሚየር ሊጉ 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቸስተር ሲቲ ከሻምፒዮንስ ሊግ ሽንፈት በኋላ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ብራይተን አልቢዮን ጋር ዛሬ ምሽት 2:30 የሚጫወት ይሆናል።
ሲቲ በሻምፒዮንስ ሊጉ ባለፈው ማክሰኞ በስፖርቲንግ ሊዝበን ከደረሰበት ሽንፈት ለማገገም ከጉዳት የተመለሰውን የኬቨን ዴብራይን አገልግሎት እንደሚያገኝ ይጠበቃል።
በሲቲ በኩል ተከላከዩ ጆን ስቶንስ፣ ጃክ ግሪሊሽ፣ ኦስካር ቦብ እና ሩበን ዲያዝ በጉዳት ምክንያት በዛሬው ጨዋታ አይገቡም ተብሏል።
ብራይተን አልቢዮን ከሲቲ ጋር ባደረጋቸው 14 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ማሸነፍ ችሏል።
በ10 ጨዋታዎች በሰበሰበው 25 ነጥብ ፕሪሚየር ሊጉን እየመራ ያለው ሊቨርፑል፣ በሊጉ በ18 ነጥብ 6ኛ ጀረጃ ላይ ከሚገኘው አስቶን ቪላ ጋር በአንፊልድ ምሽት 5፡00 ሰዓት ይጫወታል።
የሊቨርፑል አሰልጣኝነትን ከክሎፕ የተረከቡት አሰልጣኝ አርና ስሎት በሊጉ ባደረጓቸው 16 ጨዋታዎች በ14ቱ በማሸነፍ ምርጥ ጅማሮ ካላቸው አሰልጣኞች መካካል ተጠቃሽ ናቸው።
በሊቨርፑል በኩል አሊሰን ዲያጎ ጆታ፣ ሃርቪ ኤሊዬት እና ፌዴሪኮ ቺዛ በጉዳት፤ አሌክሲስ ማካሊስተር በሁለት ቢጫ ቅጣት በዛሬው ጨዋታ እንደማይሰለፉ ቢቢሲ ዘግቧል።
ሊቨርፑል ሊጉን በ25 ነጥብ እየመራ፤ ሲቲ በ23 ነጥብ በሁለተኛነት እየተከተለ መሆኑ የዛሬዎቹን ጨዋታዎች በስፖርቱ አፍቃሪዎች ዘንድ ተጠባቂ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።
በላሉ ኢታላ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር የሊጉ መሪ ሊቨርፑል በሜዳው ምሽት 5 ሰዓት ከአስቶን ቪላ ጋር ይጫወታል።
በፕሪሚየር ሊጉ 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቸስተር ሲቲ ከሻምፒዮንስ ሊግ ሽንፈት በኋላ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ብራይተን አልቢዮን ጋር ዛሬ ምሽት 2:30 የሚጫወት ይሆናል።
ሲቲ በሻምፒዮንስ ሊጉ ባለፈው ማክሰኞ በስፖርቲንግ ሊዝበን ከደረሰበት ሽንፈት ለማገገም ከጉዳት የተመለሰውን የኬቨን ዴብራይን አገልግሎት እንደሚያገኝ ይጠበቃል።
በሲቲ በኩል ተከላከዩ ጆን ስቶንስ፣ ጃክ ግሪሊሽ፣ ኦስካር ቦብ እና ሩበን ዲያዝ በጉዳት ምክንያት በዛሬው ጨዋታ አይገቡም ተብሏል።
ብራይተን አልቢዮን ከሲቲ ጋር ባደረጋቸው 14 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ማሸነፍ ችሏል።
በ10 ጨዋታዎች በሰበሰበው 25 ነጥብ ፕሪሚየር ሊጉን እየመራ ያለው ሊቨርፑል፣ በሊጉ በ18 ነጥብ 6ኛ ጀረጃ ላይ ከሚገኘው አስቶን ቪላ ጋር በአንፊልድ ምሽት 5፡00 ሰዓት ይጫወታል።
የሊቨርፑል አሰልጣኝነትን ከክሎፕ የተረከቡት አሰልጣኝ አርና ስሎት በሊጉ ባደረጓቸው 16 ጨዋታዎች በ14ቱ በማሸነፍ ምርጥ ጅማሮ ካላቸው አሰልጣኞች መካካል ተጠቃሽ ናቸው።
በሊቨርፑል በኩል አሊሰን ዲያጎ ጆታ፣ ሃርቪ ኤሊዬት እና ፌዴሪኮ ቺዛ በጉዳት፤ አሌክሲስ ማካሊስተር በሁለት ቢጫ ቅጣት በዛሬው ጨዋታ እንደማይሰለፉ ቢቢሲ ዘግቧል።
ሊቨርፑል ሊጉን በ25 ነጥብ እየመራ፤ ሲቲ በ23 ነጥብ በሁለተኛነት እየተከተለ መሆኑ የዛሬዎቹን ጨዋታዎች በስፖርቱ አፍቃሪዎች ዘንድ ተጠባቂ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።
በላሉ ኢታላ
👍17
ኢትዮ ቴሌኮም በቢሾፍቱ የ5ጂ ሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት አስጀመረ
***************
ኢትዮ ቴሌኮም በቢሾፍቱ ከተማ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጨረሻው ፈጣን የሆነውን የአምስተኛ ትውልድ (5ጂ) ሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት አስጀምሯል።
በቢሾፍቱ ከተማ የቱሪዝም ዘርፉን ወደላቀ ደረጃ ለማሻገር ያስችላል የተባለው የ5ጂ አገልግሎቱን የቢሾፍቱ ከተማና የኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራሮች በይፋ አስጀምረዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህወት ታምሩ የ5ጂ አገልግሎት በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ከተማዋ በቱሪዝም፣ በንግድና በሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ ዕድገት ለማምጣት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማዋ የ5ጂ አገልግሎት መጀመር ስማርት ቢሾፍቱን ለመገንባት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል።
የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አቶ አለማየሁ አሰፋ፥ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጨረሻው ፈጣን የሆነው የ5ጂ አገልግሎት በከተማዋ መጀመር የቢሮ ስራዎችን ለማቀላጠፍ፣ ለተገልጋዩ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት፣ ስማርት ሲቲን ለመገንባት፣ የቢሾፍቱን የቱሪስት መስህብነት አቅም ለማሳደግና በርካታ አገልግሎቶችን ለማከናወን የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል።
130 ዓመታት ለህዝቡ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ኢትዮ ቴሌኮም ዓለማችን የደረሰችበትን የ5ጂ ሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት በቀጣይ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማስጀመር እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።
በሐምራዊት ብርሃኑ
***************
ኢትዮ ቴሌኮም በቢሾፍቱ ከተማ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጨረሻው ፈጣን የሆነውን የአምስተኛ ትውልድ (5ጂ) ሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት አስጀምሯል።
በቢሾፍቱ ከተማ የቱሪዝም ዘርፉን ወደላቀ ደረጃ ለማሻገር ያስችላል የተባለው የ5ጂ አገልግሎቱን የቢሾፍቱ ከተማና የኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራሮች በይፋ አስጀምረዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህወት ታምሩ የ5ጂ አገልግሎት በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ከተማዋ በቱሪዝም፣ በንግድና በሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ ዕድገት ለማምጣት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማዋ የ5ጂ አገልግሎት መጀመር ስማርት ቢሾፍቱን ለመገንባት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል።
የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አቶ አለማየሁ አሰፋ፥ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጨረሻው ፈጣን የሆነው የ5ጂ አገልግሎት በከተማዋ መጀመር የቢሮ ስራዎችን ለማቀላጠፍ፣ ለተገልጋዩ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት፣ ስማርት ሲቲን ለመገንባት፣ የቢሾፍቱን የቱሪስት መስህብነት አቅም ለማሳደግና በርካታ አገልግሎቶችን ለማከናወን የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል።
130 ዓመታት ለህዝቡ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ኢትዮ ቴሌኮም ዓለማችን የደረሰችበትን የ5ጂ ሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት በቀጣይ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማስጀመር እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።
በሐምራዊት ብርሃኑ
👍32❤4👏4
አቶ እንዳሻው ጣሰው በዱባይ ለሀላባ ስታዲየም ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አስጀመሩ
**************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ዱባይ በመገኘት ለሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አስጀምረዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ በተባበሩት አረብ ኢምሬት የሀላባ ማህበረሰብ አባላት፣ የልማት አጋሮች እንዲሁም የክልሉና የሀላባ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።
**************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ዱባይ በመገኘት ለሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አስጀምረዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ በተባበሩት አረብ ኢምሬት የሀላባ ማህበረሰብ አባላት፣ የልማት አጋሮች እንዲሁም የክልሉና የሀላባ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።
👍27❤4
በትግራይ ክልል የትምህርት ዘርፉ ዳግም እንዲያንሰራራ በሚደረገው ጥረት የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል፦ አቶ ጌታቸው ረዳ
**********
መቐለ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማጠናከር በሚያደርገው ጥረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ አስታወቁ።
መቐለ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ-ግብር በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸው 2729 ዕጩ ተማሪዎች ለ30ኛ ጊዜ አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ቀን ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል 1950 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 22 በሦስተኛ ዲግሪ እና 664 በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆኑ፤ ቀሪዎቹ (93) የሕክምና ዶክተሮች ናቸው።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02SkU5yZyHTkH5eRKCRcBptWKL9FGyEy4LaBmPnswH8gdxuJfoENjcqPtZ9GSorssul
**********
መቐለ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማጠናከር በሚያደርገው ጥረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ አስታወቁ።
መቐለ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ-ግብር በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸው 2729 ዕጩ ተማሪዎች ለ30ኛ ጊዜ አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ቀን ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል 1950 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 22 በሦስተኛ ዲግሪ እና 664 በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆኑ፤ ቀሪዎቹ (93) የሕክምና ዶክተሮች ናቸው።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02SkU5yZyHTkH5eRKCRcBptWKL9FGyEy4LaBmPnswH8gdxuJfoENjcqPtZ9GSorssul
👍31❤1
ሻምፒዮኑ ማንቸስተር ሲቲ በብራይተን አልቢዮን 2ለ1 ተሸነፈ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከሜዳው ውጭ ብራይተን አልቢዮንን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ 2ለ1 ተሸንፏል።
ማንቸስተር ሲቲ ኮቫቲች በግሩም ሁኔታ ያቀበለውን ኳስ በመቀበል ሃላንድ በ23ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ እስከ 78ኛው ደቂቃ ድረስ 1ለ0 መምራት ችሎ ነበር።
ሆኖም ለብራይተን አልቢዮን በ2ኛው መደበኛ የጨዋታ ክፍ ጊዜ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ፔድሮ በ78ኛው ደቂቃ የአቻነቷን ግብ አስቆጠረ።
ከ5 ደቂቃ በኋላ በ83ኛው ደቂቃ ደግሞ ኦሪሌ 2ኛዋን ግብ በማስቆጠር ብራይተኖች ሲቲን በሜዳቸው 2ለ1 ማሸነፍ ችለዋል።
ብራይተን በ11 ጨዋታ አሁን በሊጉ ያለውን ደረጃ ከፍ ማድረግ ችሏል።
ሲቲ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ማሸነፍ ባለመቻሉ የሊጉ መሪ መሆን የሚችልበትን ዕድል አምክኗል።
ሊጉን በ25 ነጥብ እየመራ ያለው ሊቨር ፑል ዛሬ ማታ 5 ሰዓት በሜዳው አስቶን ቪላን ይገጥማል።
በላሉ ኢታላ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከሜዳው ውጭ ብራይተን አልቢዮንን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ 2ለ1 ተሸንፏል።
ማንቸስተር ሲቲ ኮቫቲች በግሩም ሁኔታ ያቀበለውን ኳስ በመቀበል ሃላንድ በ23ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ እስከ 78ኛው ደቂቃ ድረስ 1ለ0 መምራት ችሎ ነበር።
ሆኖም ለብራይተን አልቢዮን በ2ኛው መደበኛ የጨዋታ ክፍ ጊዜ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ፔድሮ በ78ኛው ደቂቃ የአቻነቷን ግብ አስቆጠረ።
ከ5 ደቂቃ በኋላ በ83ኛው ደቂቃ ደግሞ ኦሪሌ 2ኛዋን ግብ በማስቆጠር ብራይተኖች ሲቲን በሜዳቸው 2ለ1 ማሸነፍ ችለዋል።
ብራይተን በ11 ጨዋታ አሁን በሊጉ ያለውን ደረጃ ከፍ ማድረግ ችሏል።
ሲቲ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ማሸነፍ ባለመቻሉ የሊጉ መሪ መሆን የሚችልበትን ዕድል አምክኗል።
ሊጉን በ25 ነጥብ እየመራ ያለው ሊቨር ፑል ዛሬ ማታ 5 ሰዓት በሜዳው አስቶን ቪላን ይገጥማል።
በላሉ ኢታላ
👍37👏6❤5