አንጋፋው ጊታሪስት ሰላም ስዩም የተሳተፈበት "አፍሮ ናይል" የተሰኘ አልበም ተለቀቀ
አንጋፋው ጊታሪስት ሰላም ስዩም የተሳተፈበት "አፍሮ ናይል" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም አርብ ሐምሌ 5 2016 ዓ.ም "AfroNile" በተሰኘ የዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮች እንደደረሰ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተመልክቷል።
ሙዚቀኛ ዳዊት ብርሃነ እና ጊታሪስት ሰላም ስዩም የተጣምሩበት ይህ አልበም በርካታ ድምጻዊያንን አሳትፏል።
በዚህ "አፍሮ ናይል" በተሰኘው የሙዚቃ አልበም ላይ ድምጻዊኑ ዲባኩሉ ታፈሰ ፣ ሚኪ ሀሴት፣ ሊያ ግርማ፤ጌጥሽ ተስፋዬ በፊውቸርንግ ተሳትፈዋል።
ኤቨንት አዲስ ድረገፅ እንደተመለከተው ከሆነ በዚህ አልበም ላይ አፍሪካ ዩኒቲ፣ ናፍቆት፣የደስታ እንባ፣አይ ፍቅር ፣ዜም ቲዩን ሪይስ የተሰኙ አምስት ሙዚቃዎች ተካተውበታል።
የሮሀ እና የአይቤክስ ባንድ መስራች የሆነው ጊታሪስት ሰላም ስዩም ከረጅም በኃላ በሙዚቃ አልበም ላይ ተሳትፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው ጊታሪስት ሰላም ስዩም የተሳተፈበት "አፍሮ ናይል" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም አርብ ሐምሌ 5 2016 ዓ.ም "AfroNile" በተሰኘ የዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮች እንደደረሰ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተመልክቷል።
ሙዚቀኛ ዳዊት ብርሃነ እና ጊታሪስት ሰላም ስዩም የተጣምሩበት ይህ አልበም በርካታ ድምጻዊያንን አሳትፏል።
በዚህ "አፍሮ ናይል" በተሰኘው የሙዚቃ አልበም ላይ ድምጻዊኑ ዲባኩሉ ታፈሰ ፣ ሚኪ ሀሴት፣ ሊያ ግርማ፤ጌጥሽ ተስፋዬ በፊውቸርንግ ተሳትፈዋል።
ኤቨንት አዲስ ድረገፅ እንደተመለከተው ከሆነ በዚህ አልበም ላይ አፍሪካ ዩኒቲ፣ ናፍቆት፣የደስታ እንባ፣አይ ፍቅር ፣ዜም ቲዩን ሪይስ የተሰኙ አምስት ሙዚቃዎች ተካተውበታል።
የሮሀ እና የአይቤክስ ባንድ መስራች የሆነው ጊታሪስት ሰላም ስዩም ከረጅም በኃላ በሙዚቃ አልበም ላይ ተሳትፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"በዓሉ ግርማ: ቤርሙዳ" ተውኔት ተቋረጠ
በውድነህ ክፍሌ ተደርሶ በተሻለ አሰፍ የተዘጋጀውና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ የመጣው "በዓሉ ግርማ ቤርሙዳ" ተውኔት ከሐሙስ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም ጀምሮ "በአንድ ተዋናይ መቅረት" ምክንያት እንደተቋረጠ ኤቨንት ድረገፅ ሰምቷል።
በተውኔቱ ላይ ተሳታፊ የሆነ ባለሞያዎች ተደጋጋሚ መቅረት እና በሁለቱ ቴአትር ቤቶች ማለትም በሀገርፍቅር እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤቶች መካከል ያለው የተግባቦት እና አሰራር ችግር ምክንያት "በዓሉ ግርማ: ቤርሙዳ" ተውኔት ሙሉበሙሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መቋረጡን ድረገጻችን ሰምቷል።
የተውኔቱ አዘጋጅ ወድነህ ክፍሌ በማህበራዊ ትስስር ገፁ"በዓሉ ግርማ - ቤርሙዳ" ቴአትር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አይታይም ቆሟል።" ማለቱን ኤቨንት ድረገፅ ተመልክቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በውድነህ ክፍሌ ተደርሶ በተሻለ አሰፍ የተዘጋጀውና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ የመጣው "በዓሉ ግርማ ቤርሙዳ" ተውኔት ከሐሙስ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም ጀምሮ "በአንድ ተዋናይ መቅረት" ምክንያት እንደተቋረጠ ኤቨንት ድረገፅ ሰምቷል።
በተውኔቱ ላይ ተሳታፊ የሆነ ባለሞያዎች ተደጋጋሚ መቅረት እና በሁለቱ ቴአትር ቤቶች ማለትም በሀገርፍቅር እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤቶች መካከል ያለው የተግባቦት እና አሰራር ችግር ምክንያት "በዓሉ ግርማ: ቤርሙዳ" ተውኔት ሙሉበሙሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መቋረጡን ድረገጻችን ሰምቷል።
የተውኔቱ አዘጋጅ ወድነህ ክፍሌ በማህበራዊ ትስስር ገፁ"በዓሉ ግርማ - ቤርሙዳ" ቴአትር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አይታይም ቆሟል።" ማለቱን ኤቨንት ድረገፅ ተመልክቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ አሜሪካ ገባ
ተዋናይ አማኑኤል ሐብታሙ ከእስር ከተለቀቀ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሀገር ውጪ በመሔድ በአሁኑ ሰዓት አሜሪካን እንደገባ ከፊልም ባለሞያው ያሬድ ሹመት ማህበራዊ ትስስር ገፁ ተመልክተናል።
አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ “አሸባሪ መረጃዎችን በማጋራት የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት የሚያውክ ተግባር ፈጽመዋል” በሚል ለወራት ታስሮ እንደነበርና ከሳምንታት በፊት በ50ሺ ብር ዋስ ከእስር እንደተፈታ ይታወሳል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ተዋናይ አማኑኤል ሐብታሙ ከእስር ከተለቀቀ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሀገር ውጪ በመሔድ በአሁኑ ሰዓት አሜሪካን እንደገባ ከፊልም ባለሞያው ያሬድ ሹመት ማህበራዊ ትስስር ገፁ ተመልክተናል።
አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ “አሸባሪ መረጃዎችን በማጋራት የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት የሚያውክ ተግባር ፈጽመዋል” በሚል ለወራት ታስሮ እንደነበርና ከሳምንታት በፊት በ50ሺ ብር ዋስ ከእስር እንደተፈታ ይታወሳል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ዛሬ በኢትዮጵያ ቡክ ፎረም "በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራሮች ቆይታዬ" መጽሐፍ ላይ ውይይት ይካሄዳል
በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ወንድማማቾቹ አንቷንና ሚሼል ዳባዲን የጉዞ ማስታወሻ በሆነው"በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራሮች ቆይታዬ" መጽሐፍ ዙሪያ የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም አሰናኞችና ተሳታፊዎች ዛሬ ሐምሌ 7 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 እስከ 4:00 ውይይት ያደርጋሉ።
https://www.clubhouse.com/invite/XXycJVX7rAdj98OD3qAZ84pN8QeoT2J3jgL:yv5cdmqgNlhRRw54x1RomHaxaiexQBx-WOguphY4hFE
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ወንድማማቾቹ አንቷንና ሚሼል ዳባዲን የጉዞ ማስታወሻ በሆነው"በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራሮች ቆይታዬ" መጽሐፍ ዙሪያ የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም አሰናኞችና ተሳታፊዎች ዛሬ ሐምሌ 7 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 እስከ 4:00 ውይይት ያደርጋሉ።
https://www.clubhouse.com/invite/XXycJVX7rAdj98OD3qAZ84pN8QeoT2J3jgL:yv5cdmqgNlhRRw54x1RomHaxaiexQBx-WOguphY4hFE
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ራኬብ አለማየሁ አዲስ የቲቪ ዝግጅት ልትጀምር ነው
የቀድሞዋ "የእሁድን በኢቢኤስ" ፕሮግራም አቅራቢ ራኬብ አለማየሁ "ራኪ በዚህ ሳምንት" የተሰኘ የቴሌቪዥን ፕርግራም በአባይ ቴሌቪዥን ከቅዳሜ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ጀምሮ ማቅረብ ልትጀምር እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
"ራኪ በዚህ ሳምንት" በሳይኮሎጂ ፣ በፍቅርና በማሕበራዊ ሕይወት አንደምታ አልፎም በጤና፣ በስነምግብ፣ በፋሽን፣ በውበት ነክ እና በተለያዩ የህይወት ዘይቤዎች እንግዶችን በመጋበዝ የሚቀረብ ፕርግራም ነው ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የቀድሞዋ "የእሁድን በኢቢኤስ" ፕሮግራም አቅራቢ ራኬብ አለማየሁ "ራኪ በዚህ ሳምንት" የተሰኘ የቴሌቪዥን ፕርግራም በአባይ ቴሌቪዥን ከቅዳሜ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ጀምሮ ማቅረብ ልትጀምር እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
"ራኪ በዚህ ሳምንት" በሳይኮሎጂ ፣ በፍቅርና በማሕበራዊ ሕይወት አንደምታ አልፎም በጤና፣ በስነምግብ፣ በፋሽን፣ በውበት ነክ እና በተለያዩ የህይወት ዘይቤዎች እንግዶችን በመጋበዝ የሚቀረብ ፕርግራም ነው ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በተሻለ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ
ተዋናይ፣ ደራሲ፣ ዳይሬክተር እና የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢው ነፃነት ወርቅነህ ለህክምና ወደ ሀገረ ህንድ መሄዱን የሚገልጽ ማስታወሻ በግል የፌስቡክ ገፁ ማጋራቱ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ በርካታ ወዳጆቹ ፣ የሙያ አጋሮቹ እና አድናቂዎች ለአርቲስቱ መልካም ምኞታቸውን ሲገልፁ ነበር።
ገሚሶቹ ደግሞ አርቲስቱ ላይ ያጋጠመው የጤና እክል የከፋ ይሆናል የሚል ስጋታቸውን ጭምር ሲገልፁ እንደነበር ይታወሳል።
ያም ሆኖ ግን አርቲስቱ ጉዳዩን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባጋራው መልዕክቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በተጨማሪም መልካም ምኞታቸውን ለተመኙለት ምስጋናውን በማቅረብ በጥቂት ቀናት ውስጥ የህክምና ክትትሉን አገባዶ ወደ ሀገር ቤት እንደሚመለስ ተናግሯል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ተዋናይ፣ ደራሲ፣ ዳይሬክተር እና የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢው ነፃነት ወርቅነህ ለህክምና ወደ ሀገረ ህንድ መሄዱን የሚገልጽ ማስታወሻ በግል የፌስቡክ ገፁ ማጋራቱ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ በርካታ ወዳጆቹ ፣ የሙያ አጋሮቹ እና አድናቂዎች ለአርቲስቱ መልካም ምኞታቸውን ሲገልፁ ነበር።
ገሚሶቹ ደግሞ አርቲስቱ ላይ ያጋጠመው የጤና እክል የከፋ ይሆናል የሚል ስጋታቸውን ጭምር ሲገልፁ እንደነበር ይታወሳል።
ያም ሆኖ ግን አርቲስቱ ጉዳዩን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባጋራው መልዕክቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በተጨማሪም መልካም ምኞታቸውን ለተመኙለት ምስጋናውን በማቅረብ በጥቂት ቀናት ውስጥ የህክምና ክትትሉን አገባዶ ወደ ሀገር ቤት እንደሚመለስ ተናግሯል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማኀበር
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ሐምሌ 6 2016 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ በሦስት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በጉባኤውም ያለፈው ሁለት ዓመት የሥራ ክንውን እና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ግምገማ ተደርጎበታል።
ላለፉት ሁለት ዓመታት ማኅበሩን በፕሬዝዳንትነት ያገለገለው ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ባለበት የሥራ መደራረብ ምክንያት ማኅበሩን ተተኪዎች እንዲመሩት በመጠየቁ በጠቅላላ ጉባኤው በክብር ተሸኝቷል።
በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት በሥራ ላይ ያሉት የሥራ አስፈጻሚ አባላት የቆይታ ጊዜያቸው ስለተጠናቀቀ የተጓደሉትን ጨምሮ እንደ አዲስ የዘጠኝ የሥራ አስፈጻሚ አባላት ምርጫ ተካሂዷል። በዚህም መሰረት ሶስት ነባር ሥራ አስፈጻሚዎችና ስምንት አዳዲስ አባላት በእጩነት ቀርበው ምርጫ ተደርጓል። በጉባኤው ለምርጫ ከቀረቡ እጩዎች መካከል ዘጠኝ ሥራ አስፈጻሚዎች በጠቅላላ ጉባዔው በድምፅ ምርጫ ተመርጠዋል።
በጠቅላላ ጉባዔው ሥራ አስፈጻሚ ሆነው የተመጡት እታገኘሁ መኮነን፣ ትብለፅ ተስፋዬ፣ ሲሳይ ሳህሉ፣ሳሙኤል አባተ፣ ዳግማዊት ግርማ፣ዳዊት ታደሰ፣መርሻ ጥሩነህ፣ማናዬ እውነቱ፣ዳዊት አስታጥቄ ናቸው።
ከተመረጡት ዘጠኝ ሥራ አስፈጻሚዎች መካከል በተደገው የፕሬዝዳንት የምርጫ ውድድር ጋዜጠኛ እታገኘሁ መኮነን አብላጫ ድምጽ በማግኘት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሆና ተመርጣለች፡፡
አዲሱ ሥራ አስፈጻሚ የማኅበሩን ጠንካራጰ ጎኖች በማስቀጠልና ከአባላት ጋር በመተባበር ለጋዜጠኞች መብት መከበር እና ለኢትዮጵያ ሚዲያ አጠቃላይ ዕድገትና ነፃነት እንደሚሰራ ቃል ገብቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ሐምሌ 6 2016 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ በሦስት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በጉባኤውም ያለፈው ሁለት ዓመት የሥራ ክንውን እና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ግምገማ ተደርጎበታል።
ላለፉት ሁለት ዓመታት ማኅበሩን በፕሬዝዳንትነት ያገለገለው ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ባለበት የሥራ መደራረብ ምክንያት ማኅበሩን ተተኪዎች እንዲመሩት በመጠየቁ በጠቅላላ ጉባኤው በክብር ተሸኝቷል።
በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት በሥራ ላይ ያሉት የሥራ አስፈጻሚ አባላት የቆይታ ጊዜያቸው ስለተጠናቀቀ የተጓደሉትን ጨምሮ እንደ አዲስ የዘጠኝ የሥራ አስፈጻሚ አባላት ምርጫ ተካሂዷል። በዚህም መሰረት ሶስት ነባር ሥራ አስፈጻሚዎችና ስምንት አዳዲስ አባላት በእጩነት ቀርበው ምርጫ ተደርጓል። በጉባኤው ለምርጫ ከቀረቡ እጩዎች መካከል ዘጠኝ ሥራ አስፈጻሚዎች በጠቅላላ ጉባዔው በድምፅ ምርጫ ተመርጠዋል።
በጠቅላላ ጉባዔው ሥራ አስፈጻሚ ሆነው የተመጡት እታገኘሁ መኮነን፣ ትብለፅ ተስፋዬ፣ ሲሳይ ሳህሉ፣ሳሙኤል አባተ፣ ዳግማዊት ግርማ፣ዳዊት ታደሰ፣መርሻ ጥሩነህ፣ማናዬ እውነቱ፣ዳዊት አስታጥቄ ናቸው።
ከተመረጡት ዘጠኝ ሥራ አስፈጻሚዎች መካከል በተደገው የፕሬዝዳንት የምርጫ ውድድር ጋዜጠኛ እታገኘሁ መኮነን አብላጫ ድምጽ በማግኘት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሆና ተመርጣለች፡፡
አዲሱ ሥራ አስፈጻሚ የማኅበሩን ጠንካራጰ ጎኖች በማስቀጠልና ከአባላት ጋር በመተባበር ለጋዜጠኞች መብት መከበር እና ለኢትዮጵያ ሚዲያ አጠቃላይ ዕድገትና ነፃነት እንደሚሰራ ቃል ገብቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
9ኛው የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሞያዎች ዓመታዊ ጉባኤ ተካሄደ።
9ኛው የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሞያዎች ዓመታዊ ጉባኤ ከሐምሌ 6 እስከ 7 ቀን በኃይሌ ግራንድ ሆቴል አዲስ አበባ ተካሄደ።
ለተከታታይ ሁለት ቀናት በተካሄደው በዚህ ጉባኤ የልብ ሕክምና አገልግሎትን በሀገሪቱ ለማስፋት የተሰሩ ልዩ ልዩ ሥራዎች ለማኅበሩ አባላት እና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች ገለጻ ተደርጓል። ከዚህም ባሻገር በመስኩ የተሰማሩ የሀገር ውስጥ እና የውጪ ሃገር ተቋማት ምርቶቻቸውን እና አገልግሎቶቻቸውን ለተሳታፊዎች ለ ዕይታ አቅርበዋል። በልብ ሕክምና ዘርፍ የተሰሩ ልዩ ልዩ ጥናቶች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ከፈለኝ ደጀኔ የልብ ሕክምና ባለሞያተኞች ማኅበር ባለፉት ጊዜያት ማኅበሩ እና የልብ ሕክምና አገልግሎቶች እንዲጠናከሩ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፤ የልብ ሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት እየጨመረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ማኅበሩ የልብ ሕክምና አገልግሎት እንዲጠናከር ከልብ ሕሙማን ማኅብር እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሞያተኞች ማኅበር በመስኩ የተሰማሩ ከ300 በላይ አባላት በመላው ሀገራችን ክፍል ያሉት ሲሆን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የልብ ሕክምና አገልግሎት አስጣጥን ለማሻሻል በርካታ ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
9ኛው የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሞያዎች ዓመታዊ ጉባኤ ከሐምሌ 6 እስከ 7 ቀን በኃይሌ ግራንድ ሆቴል አዲስ አበባ ተካሄደ።
ለተከታታይ ሁለት ቀናት በተካሄደው በዚህ ጉባኤ የልብ ሕክምና አገልግሎትን በሀገሪቱ ለማስፋት የተሰሩ ልዩ ልዩ ሥራዎች ለማኅበሩ አባላት እና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች ገለጻ ተደርጓል። ከዚህም ባሻገር በመስኩ የተሰማሩ የሀገር ውስጥ እና የውጪ ሃገር ተቋማት ምርቶቻቸውን እና አገልግሎቶቻቸውን ለተሳታፊዎች ለ ዕይታ አቅርበዋል። በልብ ሕክምና ዘርፍ የተሰሩ ልዩ ልዩ ጥናቶች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ከፈለኝ ደጀኔ የልብ ሕክምና ባለሞያተኞች ማኅበር ባለፉት ጊዜያት ማኅበሩ እና የልብ ሕክምና አገልግሎቶች እንዲጠናከሩ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፤ የልብ ሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት እየጨመረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ማኅበሩ የልብ ሕክምና አገልግሎት እንዲጠናከር ከልብ ሕሙማን ማኅብር እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ባለሞያተኞች ማኅበር በመስኩ የተሰማሩ ከ300 በላይ አባላት በመላው ሀገራችን ክፍል ያሉት ሲሆን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የልብ ሕክምና አገልግሎት አስጣጥን ለማሻሻል በርካታ ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ዕውቁ ደራሲ እና ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ የተዘከረበት መርሃ ግብር ተካሄደ
አብሮ አደግ በፍቅር የመረዳጃ ማሕበር ያዘጋጀው የዕውቁ ደራሲ እና ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ የተዘከረበት መርሃ ግብር በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል። በዚህ መርሃ ግብር የገነነ ስራዎች እና ሕይወት በዝርዝር መዘከሩ ተነግሯል።
መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የማሕበሩ ሰብሳቢ አቶ ቤዛው ሹምዬ ማሕበሩ ባለፉት አስር ዓመታት ስላደረጋቸው ዕንቅስቃሴ አትተዋል። አክለውም "ያለፉትን በመዘከር፣ የሰሩትን በማክበር ተተኪዎችን እንፍጠር!" በሚል መሪ ቃል ስለተዘጋጀው ይህ መርሃ ግብር በዝርዝር አብራርተዋል።
የገነነ መኩሪያ የሕይወት ታሪክ በንባብ የቀረበ ሲሆን፣ በሕይወት ዘመኑ ያበረከታቸው የተለያዩ ስራዎች በመታሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ ተዘክረዋል። ከገነነ መኩሪያ "ኢሕአፓ እና ስፖርት" መጽሐፍ የተቀነጨበ ስራ ለዕድምተኞች በትረካ ቀርቧል።
በተጨማሪም፣ ለቀድሞ የእግርኳስ ተጨዋቾች ተካ ገለታ፣ ግርማ አበበ፣ እና ጌቱ መልካ፤ ለቀድሞ ቦክሰኛ ደረጀ ደሱ እና ለድምጻውያኑ ጎሳዬ ተስፋዬ እና አብዱ ኪያር፣ ለሁለገቡ የኪነ ጥበብ ሰው ዳዊት አፈወርቅ፣ ለተዋናይ ተሰማ ገለቱ፣ ለኬሮግራፈር ዳንኤል ደሳለኝ፣ ለጋዜጠኛ እንግዱ ወልዴ እና ለሕግ ባለሞያዋ ሰናይት ፍስሐ (ፕ/ር) ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ እና የገነነ መኩሪያ ባለቤት ወይዘሮ አስቴር አየለ ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመርሃ ግብሩ ላይ ታድመዋል።
አብሮ አደግ በፍቅር የመረዳጃ ማሕበር የተመሰረተበትን አስረኛ ዓመት በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ተከብሯል።
መረጃው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ነው።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አብሮ አደግ በፍቅር የመረዳጃ ማሕበር ያዘጋጀው የዕውቁ ደራሲ እና ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ የተዘከረበት መርሃ ግብር በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል። በዚህ መርሃ ግብር የገነነ ስራዎች እና ሕይወት በዝርዝር መዘከሩ ተነግሯል።
መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የማሕበሩ ሰብሳቢ አቶ ቤዛው ሹምዬ ማሕበሩ ባለፉት አስር ዓመታት ስላደረጋቸው ዕንቅስቃሴ አትተዋል። አክለውም "ያለፉትን በመዘከር፣ የሰሩትን በማክበር ተተኪዎችን እንፍጠር!" በሚል መሪ ቃል ስለተዘጋጀው ይህ መርሃ ግብር በዝርዝር አብራርተዋል።
የገነነ መኩሪያ የሕይወት ታሪክ በንባብ የቀረበ ሲሆን፣ በሕይወት ዘመኑ ያበረከታቸው የተለያዩ ስራዎች በመታሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ ተዘክረዋል። ከገነነ መኩሪያ "ኢሕአፓ እና ስፖርት" መጽሐፍ የተቀነጨበ ስራ ለዕድምተኞች በትረካ ቀርቧል።
በተጨማሪም፣ ለቀድሞ የእግርኳስ ተጨዋቾች ተካ ገለታ፣ ግርማ አበበ፣ እና ጌቱ መልካ፤ ለቀድሞ ቦክሰኛ ደረጀ ደሱ እና ለድምጻውያኑ ጎሳዬ ተስፋዬ እና አብዱ ኪያር፣ ለሁለገቡ የኪነ ጥበብ ሰው ዳዊት አፈወርቅ፣ ለተዋናይ ተሰማ ገለቱ፣ ለኬሮግራፈር ዳንኤል ደሳለኝ፣ ለጋዜጠኛ እንግዱ ወልዴ እና ለሕግ ባለሞያዋ ሰናይት ፍስሐ (ፕ/ር) ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ እና የገነነ መኩሪያ ባለቤት ወይዘሮ አስቴር አየለ ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመርሃ ግብሩ ላይ ታድመዋል።
አብሮ አደግ በፍቅር የመረዳጃ ማሕበር የተመሰረተበትን አስረኛ ዓመት በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ተከብሯል።
መረጃው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ነው።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"የሚስቶቼ ባሎች"ተውኔት ነገ ይሰናበታል
በደራሲ አበባየሁ ታደሰ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ማርያም እና ይገረም ደጀኔ የተዘጋጀው " የሚስቶቼ ባሎች " ተውኔት ነገ ረቡዕ ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ከዓለም ሲኒማ መድረክ በክብር እንደሚሰናበት ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ሰምቷል።
በሐምሌት መልቲሚዲያ የቀረበው"የሚስቶቼ ባሎች " ተውኔት ላይ ይገረም ደጀኔ፣ ሸዊት ከበደ ፣የምስራች ግርማ ፣ ብሩክ ምናሴና ሔኖክ ብርሃኑ በተዋናይነት ተሳትፈዋል።
ቴአትሩ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር፣ በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ እንዲሁም በሀገርፍቅር ቴአትር አዳራሽ ለእይታ ቀርቦ የነበረ ሲሆን ከዓመታት በኃላ ባሳለፍነው ዓመት ሰኔ 21 2015 ዓ.ም ነበር ወደ መድረክ የተመለሰው።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲ አበባየሁ ታደሰ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ማርያም እና ይገረም ደጀኔ የተዘጋጀው " የሚስቶቼ ባሎች " ተውኔት ነገ ረቡዕ ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ከዓለም ሲኒማ መድረክ በክብር እንደሚሰናበት ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ሰምቷል።
በሐምሌት መልቲሚዲያ የቀረበው"የሚስቶቼ ባሎች " ተውኔት ላይ ይገረም ደጀኔ፣ ሸዊት ከበደ ፣የምስራች ግርማ ፣ ብሩክ ምናሴና ሔኖክ ብርሃኑ በተዋናይነት ተሳትፈዋል።
ቴአትሩ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር፣ በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ እንዲሁም በሀገርፍቅር ቴአትር አዳራሽ ለእይታ ቀርቦ የነበረ ሲሆን ከዓመታት በኃላ ባሳለፍነው ዓመት ሰኔ 21 2015 ዓ.ም ነበር ወደ መድረክ የተመለሰው።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ተንኳሾቹ" መጽሐፍ ለንባብ በቃ
ነዋሪነቱን በደቡብ ኮሪያ ያደረገው ጋዜጠኛ ዳዊት ንጉሡ ረታ (ዳ ን ረ ) ለራሱ ሁለተኛ የሆነው መፅሃፉን " ተንኳሾቹ " በሚል ርዕስ ለህትመት አብቅቷል።
" ተንኳሾቹ " መፅሃፍ 310 ገፆች ያሉትና ሃያ አንጋፋና ወጣት አዋቂዎችንና ታዋቂዎችን በእንግድነት ጋብዞ ለአንባቢያን ኮርኳሪ ሃሳቦቻቸውን እንዲያካፍሉ ያስቻለበት መፅሃፉ እንደሆነ ዳዊት ንጉሡ ለዝግጅት ክፍላችን ተናግሯል።
ከዚህ ቀደም "በ97 እና ሌሎች ታሪኮች" በሚል የመጀመሪያ መፅሃፉን ያቀረበልን ዳዊት ሁለተኛ መፅሃፉ ተንኳሾቹን በአገር ውስጥ በብር አራት መቶ ሃምሳ ብቻ ለአንባቢያን እንዳቀረበ ገልፆልናል።
መጽሃፉ የመጀመሪያ ዙር ውስን ቁጥር ህትመቱ በደቡብ ኮሪያ የተከናወነ ሲሆን ለአገር ቤት አንባቢያን ደግሞ በአገር ውስጥ ለማሳተም ከአሳታሚዎችና አከፋፋዮች ጋር ውይይት በማድረግ ሂደት ላይ እንዳለም ጨምሮ ተናግሯል።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ነዋሪነቱን በደቡብ ኮሪያ ያደረገው ጋዜጠኛ ዳዊት ንጉሡ ረታ (ዳ ን ረ ) ለራሱ ሁለተኛ የሆነው መፅሃፉን " ተንኳሾቹ " በሚል ርዕስ ለህትመት አብቅቷል።
" ተንኳሾቹ " መፅሃፍ 310 ገፆች ያሉትና ሃያ አንጋፋና ወጣት አዋቂዎችንና ታዋቂዎችን በእንግድነት ጋብዞ ለአንባቢያን ኮርኳሪ ሃሳቦቻቸውን እንዲያካፍሉ ያስቻለበት መፅሃፉ እንደሆነ ዳዊት ንጉሡ ለዝግጅት ክፍላችን ተናግሯል።
ከዚህ ቀደም "በ97 እና ሌሎች ታሪኮች" በሚል የመጀመሪያ መፅሃፉን ያቀረበልን ዳዊት ሁለተኛ መፅሃፉ ተንኳሾቹን በአገር ውስጥ በብር አራት መቶ ሃምሳ ብቻ ለአንባቢያን እንዳቀረበ ገልፆልናል።
መጽሃፉ የመጀመሪያ ዙር ውስን ቁጥር ህትመቱ በደቡብ ኮሪያ የተከናወነ ሲሆን ለአገር ቤት አንባቢያን ደግሞ በአገር ውስጥ ለማሳተም ከአሳታሚዎችና አከፋፋዮች ጋር ውይይት በማድረግ ሂደት ላይ እንዳለም ጨምሮ ተናግሯል።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"የማያረጅ ውበት" የሥዕል አውደርዕይ ተከፈተ
የሠዓሊ እንዳልካቸው ተፈራ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "የማያረጅ ውበት" የሥዕል አውደርዕይ ትላንት ረቡዕ ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም ጀምሮ ካዛንቺስ በሚገኘው ፈንድቃ የባህል ማዕከል ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
ይህ የሥዕል አወድርዕይ እስከ ሐምሌ 24 2016 ዓ.ም እንደሚቆይ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የሠዓሊ እንዳልካቸው ተፈራ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "የማያረጅ ውበት" የሥዕል አውደርዕይ ትላንት ረቡዕ ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም ጀምሮ ካዛንቺስ በሚገኘው ፈንድቃ የባህል ማዕከል ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
ይህ የሥዕል አወድርዕይ እስከ ሐምሌ 24 2016 ዓ.ም እንደሚቆይ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በእረፍት ቀንዎ ቴአትር ይመለከቱ !
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 የፍቅር ካቴና
ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍 "እሳት ወይ አበባ"
ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 የፍቅር ካቴና
ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍 "እሳት ወይ አበባ"
ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የሙዚቃ አቀናባሪው ያምሉ ሞላና ወጣቷ ድምጻዊት መና ወረደ በጋራ የሰሩት ግሚስ አልበም ተለቀቀ
"አዲስ ቀለም" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠውና የሙዚቃ አቀናባሪው ያምሉ ሞላ እና ወጣቷ ድምጻዊት መና ወረደ የተጣምሩበት ግሚስ(EP) የሙዚቃ አልበም በስፖቲፋይ የሙዚቃ መተግበሪያ በኩል ለአድማጮች ተለቋል።
"አዲስ ቀለም" ግሚስ አልበም በውስጡ ምንድነው ፣ ኤሌክትሪክ፣ ማዕዘን፣ተው ተው፣አንድ ሰሞን የተሰኙ አምስት ሙዚቃዎችን የያዘ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተመልክቷል።
የግሚስ አልበሙ ግጥም ፣ ዜማ፣ እንዲሁም ከሙዚቃው ቅንብር እስከ ማስተሪንጉ ድረስ በያምሉ ሞላ ተሰርቷል።
በተጨማሪም በከበሮ አገረሰላም ሻፊ ፣ በመሰንቆ ሀዲንቆ፣በክራራ ፋሲካ ኃይሉ ተሳትፈዋል።
በአልበሙ ከተካተቱ ሙዚቃዎች ውስጥ "ተው ተው" የተሰኘው ሙዚቃ የበርካታ የአገራችን ሴቶች ሕይወት (የቤተሰብ ኃላፊነትን) የሚዳሰስ ሙዚቃ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከሙዚቀኛ ያምሉ ሞላ ሰምቷል።
ዛሬ ማለዳ በስፖቲፋይ የሙዚቃ መተግበሪያ የተለቀቀው አልበሙ አመሸሻ ላይ በዩቲዩብ በኩልም ይለቀቃል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"አዲስ ቀለም" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠውና የሙዚቃ አቀናባሪው ያምሉ ሞላ እና ወጣቷ ድምጻዊት መና ወረደ የተጣምሩበት ግሚስ(EP) የሙዚቃ አልበም በስፖቲፋይ የሙዚቃ መተግበሪያ በኩል ለአድማጮች ተለቋል።
"አዲስ ቀለም" ግሚስ አልበም በውስጡ ምንድነው ፣ ኤሌክትሪክ፣ ማዕዘን፣ተው ተው፣አንድ ሰሞን የተሰኙ አምስት ሙዚቃዎችን የያዘ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተመልክቷል።
የግሚስ አልበሙ ግጥም ፣ ዜማ፣ እንዲሁም ከሙዚቃው ቅንብር እስከ ማስተሪንጉ ድረስ በያምሉ ሞላ ተሰርቷል።
በተጨማሪም በከበሮ አገረሰላም ሻፊ ፣ በመሰንቆ ሀዲንቆ፣በክራራ ፋሲካ ኃይሉ ተሳትፈዋል።
በአልበሙ ከተካተቱ ሙዚቃዎች ውስጥ "ተው ተው" የተሰኘው ሙዚቃ የበርካታ የአገራችን ሴቶች ሕይወት (የቤተሰብ ኃላፊነትን) የሚዳሰስ ሙዚቃ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከሙዚቀኛ ያምሉ ሞላ ሰምቷል።
ዛሬ ማለዳ በስፖቲፋይ የሙዚቃ መተግበሪያ የተለቀቀው አልበሙ አመሸሻ ላይ በዩቲዩብ በኩልም ይለቀቃል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📍 የሥነጽሑፍ ውይይት
በአዳም ረታ መጻሕፍት ላይ ውይይት
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) የሚዘጋጅው " የወር ወንበር" መሰናዶ ላይ በዚህ ወር በደራሲ አዳም ረታ መጻሕፍት ላይ ያተኮር "አዳም ከአለፍ አገደም" የአዳም ረታ ሥራዎች ጥቂት ምልከታ" በሚል ርዕስ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 በወመዘክር አዳራሽ ሥነጽሑፋዊ ውይይት ይካሄዳል።
በዚህ ሥነጽሐፋዊ ውይይት ላይ አቶ ይኩኖአምላክ መዝገቡ መነሻ ሀሳብ ያቀርባሉ ተብሏል።
በዝግጅቱ ላይ የሚገኙ ከሆነ ይህንን ቅፅ https://bit.ly/3S45QS2 ይሙሉ ተብለዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአዳም ረታ መጻሕፍት ላይ ውይይት
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) የሚዘጋጅው " የወር ወንበር" መሰናዶ ላይ በዚህ ወር በደራሲ አዳም ረታ መጻሕፍት ላይ ያተኮር "አዳም ከአለፍ አገደም" የአዳም ረታ ሥራዎች ጥቂት ምልከታ" በሚል ርዕስ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 በወመዘክር አዳራሽ ሥነጽሑፋዊ ውይይት ይካሄዳል።
በዚህ ሥነጽሐፋዊ ውይይት ላይ አቶ ይኩኖአምላክ መዝገቡ መነሻ ሀሳብ ያቀርባሉ ተብሏል።
በዝግጅቱ ላይ የሚገኙ ከሆነ ይህንን ቅፅ https://bit.ly/3S45QS2 ይሙሉ ተብለዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📍የሥነጽሑፍ ውይይት
በ"ግርባብ ያ ደግ ሰው" መጽሐፍ ላይ ውይይት
በደራሲ ፍቃዱ አየልኝ "ግርባብ ያ ደግ ሰው" መጽሐፍ ላይ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 አራት ኪሎ በሚገኙ ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ውይይት ይካሄዳል።
በዕለቱም በመጽሐፉ ላይ ሥነጽሑፍ ዳሰሳ እና ውይይት ይደረጋል ተብሏል።
አወያይ: ዮናስ ታረቀኝ
ዳሰሳ አቅራቢዎች: ምግባር ሲራጅና ዮሴፍ ይድነቃቸው
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በ"ግርባብ ያ ደግ ሰው" መጽሐፍ ላይ ውይይት
በደራሲ ፍቃዱ አየልኝ "ግርባብ ያ ደግ ሰው" መጽሐፍ ላይ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 አራት ኪሎ በሚገኙ ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ውይይት ይካሄዳል።
በዕለቱም በመጽሐፉ ላይ ሥነጽሑፍ ዳሰሳ እና ውይይት ይደረጋል ተብሏል።
አወያይ: ዮናስ ታረቀኝ
ዳሰሳ አቅራቢዎች: ምግባር ሲራጅና ዮሴፍ ይድነቃቸው
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ኦሎምፒክ "ኮንሰርት ለሁለተኛ ጊዜ ተራዝሟል
አንጋፋ እና ወጣት ድምጻዊያን የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርቡበታል በሚል ሲተዋወቅ የቆየው እና ዛሬ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ይካሄዳል የተባለው "ኦሎምፒክ 2024" የተሰኘ ኮንሰርት ለሁለተኛ ጊዜ ተራዝሟል።
ይህ ኮንሰርት ሐምሌ 6 2016 ዓ.ም ይካሄዳል ከተባለ በኃላ ወደዛሬ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም እንደተራዘመ ይታወሳል።
ምናልባትም ኮንሰርቱ ሙሉበሙሉ ሊሰርዝ የሚችልበት እድል ሊኖር እንደሚችል ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከውስጥ ምንጮች ሰምቷል።
ይህ የሙዚቃ ኮንሰርት ሌብል ዋን ኢንተርቴይመንት እና ላላ ፕሮዳክሽን በመተባበር ያዘጋጁት ነው።
የኮንሰርቱም ዋንኛ ዓላማ የፓሪስ ኦሎምፒክ ተሳታፊ አትሌቶችን ለመደገፍ የተዘጋጀ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋ እና ወጣት ድምጻዊያን የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርቡበታል በሚል ሲተዋወቅ የቆየው እና ዛሬ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ ይካሄዳል የተባለው "ኦሎምፒክ 2024" የተሰኘ ኮንሰርት ለሁለተኛ ጊዜ ተራዝሟል።
ይህ ኮንሰርት ሐምሌ 6 2016 ዓ.ም ይካሄዳል ከተባለ በኃላ ወደዛሬ ሐምሌ 13 2016 ዓ.ም እንደተራዘመ ይታወሳል።
ምናልባትም ኮንሰርቱ ሙሉበሙሉ ሊሰርዝ የሚችልበት እድል ሊኖር እንደሚችል ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከውስጥ ምንጮች ሰምቷል።
ይህ የሙዚቃ ኮንሰርት ሌብል ዋን ኢንተርቴይመንት እና ላላ ፕሮዳክሽን በመተባበር ያዘጋጁት ነው።
የኮንሰርቱም ዋንኛ ዓላማ የፓሪስ ኦሎምፒክ ተሳታፊ አትሌቶችን ለመደገፍ የተዘጋጀ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1