📌የሮፍናን ኑሪ "ፔሌ" ሙዚቃ ቪዲዮ ተለቀቀ
የሮፍናን ኑሪ ዘጠኝ የሙዚቃ አልበም ውስጥ ከተካተቱ የሙዚቃ ስራዎች "ፔሌ" ለተሰኘው ሙዚቃ የተሰራው የሙዚቃ ቪዲዮ በሙዚቀኛው የዩቲዩብ ቻናል እንደተለቀቀ ኤቨንት አዲስ ተመልክቷል።
የሙዚቃ ቪዲዮው በኪሩቤል ጥበቡ ዳይሬክት የተደረገ ሲሆን የሙዚቃው ግጥምና ዜማ እንዲሁም ቅንብር በሮፍናን ኑሪ ተሰርቷል።
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ ስለሙዚቃ ቪዲዮው በማህበራዊ ትስስር ገፁ"የአዲስ አመት ስጦታ ይሁን" ብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የሮፍናን ኑሪ ዘጠኝ የሙዚቃ አልበም ውስጥ ከተካተቱ የሙዚቃ ስራዎች "ፔሌ" ለተሰኘው ሙዚቃ የተሰራው የሙዚቃ ቪዲዮ በሙዚቀኛው የዩቲዩብ ቻናል እንደተለቀቀ ኤቨንት አዲስ ተመልክቷል።
የሙዚቃ ቪዲዮው በኪሩቤል ጥበቡ ዳይሬክት የተደረገ ሲሆን የሙዚቃው ግጥምና ዜማ እንዲሁም ቅንብር በሮፍናን ኑሪ ተሰርቷል።
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ ስለሙዚቃ ቪዲዮው በማህበራዊ ትስስር ገፁ"የአዲስ አመት ስጦታ ይሁን" ብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ፍቅር እስከ መቃብር" ድራማ ተለቀቀ
የደራሲ ሀዲስ አለማየሁ ዘመን አይሽሬ መጽሐፍ የሆነው"ፍቅር እስከ መቃብር" መጽሐፍ ወደ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ተቀይሮ ዛሬ መስከረም 1 2017 ዓ.ም በቴለቪዥን መታየት የሚጀምር ሲሆን አስቀድሞ ትላንት ሌሊት በኢቢሲ ይፋዊ የዩቲዩብ ቻናል ተለቋል።
ተከታታይ ድራማው ከዩቲዩብ በተጨማሪም ዛሬ
በኢቢሲ ዜና ቻናል ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እና በመዝናኛ ቻናል ደግሞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ ይተላለፋል፡፡ እንዲሁም በድጋሚ ምሽት ከዜና በኋላ በሁለቱም ቻናሎች እንደሚተላለፍ ኤቨንት አዲስ ድረገጽ ከጣቢያው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
"የፍቅር እስከ መቃብር" የልብ ወለድ መጽሐፍን ‘ሰው መሆን ፊልም ፕሮዳክሽን’ ወደ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በመቀየር በአራት ምዕራፍ፣ በ48 ክፍሎችና በአማካይ 45 ደቂቃ ርዝማኔ እንዲኖረው ሆኖ እንዲሰራ ስምምነት ከኢቢሲ ማድረጋቸው አይዘነጋም።
በተጨማሪም ውሉ ላይ ‘ሰው መሆን ፊልም ፕሮዳክሽን’ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ የድራማውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ማለትም (ከክፍል1-12) የተጠናቀቁ ሥራዎችን እንዲሁም በቀጣይ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ (48 ክፍሎች) አጠናቅቆ ለማስረከብ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የደራሲ ሀዲስ አለማየሁ ዘመን አይሽሬ መጽሐፍ የሆነው"ፍቅር እስከ መቃብር" መጽሐፍ ወደ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ተቀይሮ ዛሬ መስከረም 1 2017 ዓ.ም በቴለቪዥን መታየት የሚጀምር ሲሆን አስቀድሞ ትላንት ሌሊት በኢቢሲ ይፋዊ የዩቲዩብ ቻናል ተለቋል።
ተከታታይ ድራማው ከዩቲዩብ በተጨማሪም ዛሬ
በኢቢሲ ዜና ቻናል ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እና በመዝናኛ ቻናል ደግሞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ ይተላለፋል፡፡ እንዲሁም በድጋሚ ምሽት ከዜና በኋላ በሁለቱም ቻናሎች እንደሚተላለፍ ኤቨንት አዲስ ድረገጽ ከጣቢያው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
"የፍቅር እስከ መቃብር" የልብ ወለድ መጽሐፍን ‘ሰው መሆን ፊልም ፕሮዳክሽን’ ወደ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በመቀየር በአራት ምዕራፍ፣ በ48 ክፍሎችና በአማካይ 45 ደቂቃ ርዝማኔ እንዲኖረው ሆኖ እንዲሰራ ስምምነት ከኢቢሲ ማድረጋቸው አይዘነጋም።
በተጨማሪም ውሉ ላይ ‘ሰው መሆን ፊልም ፕሮዳክሽን’ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ የድራማውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ማለትም (ከክፍል1-12) የተጠናቀቁ ሥራዎችን እንዲሁም በቀጣይ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ (48 ክፍሎች) አጠናቅቆ ለማስረከብ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በእረፍት ቀንዎ ቴአትር ይመለከቱ !
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 የፍቅር ካቴና
ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍 "እሳት ወይ አበባ"
ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 የፍቅር ካቴና
ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍 "እሳት ወይ አበባ"
ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌“አቴቴ አያና ሐዎታ” ዘጋቢ ፊልም ሊመረቅ ነው
በኑቢያ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው “አቴቴ አያና ሐዎታ” የተሰኘ የእናቶች(አቴቴ)ዘጋቢ ፊልም መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ይመረቃል።
ዘጋቢ ፊልሙ በገዳ ሥርዓት እና በኦሮሞ ማህበረሰብ ውስጥ ሴቶች ሚና ያላቸውን ልዩ ወጎች፣ ፍልስፍናዎች እና ታሪካዊ ፋይዳዎች በጥልቀት ያሳያል የተባለ ሲሆን የሲንቄን ሥርአትና የልጃገረዶች ወዮማ ሥርአትን የሚያብራራና የሚገልጽ እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ ፊልሙ መስራት ሁለት ዓመት የወሰደ ሲሆን በፊልሙ ላይም በኦሮሞ ታሪክ ከፍተኛ ምርምርና ጥናቶችን ያደረጉ ምሁራን የተሳተፉበት ሲሆን ስራው ዓለማቀፋዊ እንዲሆን በጥራት የተሰራ ነው ተብሏል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የእናቶች (አቴቴ) ዘጋቢ ፊልም ታሪኩን ከማስተዋወቅ ባለፈ በገዳ ሥርዓት ውስጥ ሴቶች እና እናቶች ያላቸውን ልዩ ስፍራ አጉልቶ የሚያሳይ እንደሆነ ተነግሯል።
በኑቢያ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበ ዘጋቢ ፊልሙ በሮብሰን ዋቤ ፕሮዲዩሰር እና ዳይሬክተርነት የተሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
በአጠቃላይ ይህንን ዶክሜንተሪ ሰርቶ ለመጨረስ አራት ሚሊዮን ብር ፈጅቷል ተብሏል።
የዘጋቢ ፊልሙ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ ታዋቂ አርቲስቶች፣ አባ ገዳዎች፣ የሲንቄ እናቶች፣ የኦሮሞ ስራ ፈጣሪዎች እና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት የፊታችን መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት በሸራተን አዲስ ሆቴል ይመረቃል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በኑቢያ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው “አቴቴ አያና ሐዎታ” የተሰኘ የእናቶች(አቴቴ)ዘጋቢ ፊልም መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ይመረቃል።
ዘጋቢ ፊልሙ በገዳ ሥርዓት እና በኦሮሞ ማህበረሰብ ውስጥ ሴቶች ሚና ያላቸውን ልዩ ወጎች፣ ፍልስፍናዎች እና ታሪካዊ ፋይዳዎች በጥልቀት ያሳያል የተባለ ሲሆን የሲንቄን ሥርአትና የልጃገረዶች ወዮማ ሥርአትን የሚያብራራና የሚገልጽ እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ ፊልሙ መስራት ሁለት ዓመት የወሰደ ሲሆን በፊልሙ ላይም በኦሮሞ ታሪክ ከፍተኛ ምርምርና ጥናቶችን ያደረጉ ምሁራን የተሳተፉበት ሲሆን ስራው ዓለማቀፋዊ እንዲሆን በጥራት የተሰራ ነው ተብሏል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የእናቶች (አቴቴ) ዘጋቢ ፊልም ታሪኩን ከማስተዋወቅ ባለፈ በገዳ ሥርዓት ውስጥ ሴቶች እና እናቶች ያላቸውን ልዩ ስፍራ አጉልቶ የሚያሳይ እንደሆነ ተነግሯል።
በኑቢያ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበ ዘጋቢ ፊልሙ በሮብሰን ዋቤ ፕሮዲዩሰር እና ዳይሬክተርነት የተሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
በአጠቃላይ ይህንን ዶክሜንተሪ ሰርቶ ለመጨረስ አራት ሚሊዮን ብር ፈጅቷል ተብሏል።
የዘጋቢ ፊልሙ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ ታዋቂ አርቲስቶች፣ አባ ገዳዎች፣ የሲንቄ እናቶች፣ የኦሮሞ ስራ ፈጣሪዎች እና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት የፊታችን መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት በሸራተን አዲስ ሆቴል ይመረቃል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የድምፃዊ ንዋይ ደበበ እና የአይዳ ሐሰን ወንድ ልጅ የሆነው ሰላም ንዋይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
በጋብቻ ተሳስረው አሜሪካን አገር ለረጅም አመት የኖሩት ንዋይ ደበበና አይዳ ሀሰን ከቅርብ ዓመታት በፊት በይፋ መለያየታቸውን ቢገልፁም እንደቤተሰብ ብዙም አልተራራቁም።
በትዳር ሕይወታቸው ፅናት ንዋይ የተባለች ሴት ልጅና ሰላም ነዋይ የተባለ ወንድ ልጅ በጋራ ያፈሩት ንዋይና አይዳ ልጆቻቸውን ያሳደጉት ቨርጂንያ ውስጥ ሲሆን፣ ሰላም ከጊዜ በኋላ በገጠመው የጤናእክል የተነሳ ሕክምና ሲከታተል ቆይቷል።
በተለይ የኩላሊት ኢንፌክሽን ተጠቂ በነበረበት ሰዓት አንድ ኩላሊት እናቱ አይዳ ሰጥታው ንቅለ ተከላ ማድረጉ ይታወሳል።
ከልጅነቱ ጀምሮ ተጨዋች፣ ሳቂታ እና ቀልድ የሚወድ ተወዳጅ ልጅ ነበር ትምህርቱን ተከታትሎ ያጠናቀቀው እዚያው አሜሪካን አገር ሲሆን፣ ሲበዛ አዛኝ ልብ የነበረውና ሰዎችን መርዳት የሚያስደስተው ሰላም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ንዋይ ደበበ ዛሬ ማታ ወደ አሜሪካን ይጓዛል ተብሏል።
©️መረጃው የሁሉአዲስ ነው
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በጋብቻ ተሳስረው አሜሪካን አገር ለረጅም አመት የኖሩት ንዋይ ደበበና አይዳ ሀሰን ከቅርብ ዓመታት በፊት በይፋ መለያየታቸውን ቢገልፁም እንደቤተሰብ ብዙም አልተራራቁም።
በትዳር ሕይወታቸው ፅናት ንዋይ የተባለች ሴት ልጅና ሰላም ነዋይ የተባለ ወንድ ልጅ በጋራ ያፈሩት ንዋይና አይዳ ልጆቻቸውን ያሳደጉት ቨርጂንያ ውስጥ ሲሆን፣ ሰላም ከጊዜ በኋላ በገጠመው የጤናእክል የተነሳ ሕክምና ሲከታተል ቆይቷል።
በተለይ የኩላሊት ኢንፌክሽን ተጠቂ በነበረበት ሰዓት አንድ ኩላሊት እናቱ አይዳ ሰጥታው ንቅለ ተከላ ማድረጉ ይታወሳል።
ከልጅነቱ ጀምሮ ተጨዋች፣ ሳቂታ እና ቀልድ የሚወድ ተወዳጅ ልጅ ነበር ትምህርቱን ተከታትሎ ያጠናቀቀው እዚያው አሜሪካን አገር ሲሆን፣ ሲበዛ አዛኝ ልብ የነበረውና ሰዎችን መርዳት የሚያስደስተው ሰላም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ንዋይ ደበበ ዛሬ ማታ ወደ አሜሪካን ይጓዛል ተብሏል።
©️መረጃው የሁሉአዲስ ነው
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
🙏1
📌"ፍቅር እስከ መቃብር" ድራማ በቅርብ ቀን በመደበኛው ስርጭት በኢቲቪ መዝናኛ መተላለፍ ይጀምራል ተብሏል።
በቀናት ልዩነት በተከታታይ እስከ ክፍል አራት ድረስ ሲተላለፍ የቆየው "ፍቅር እስከ መቃብር" ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በቅርብ ቀን በመደበኛው ስርጭት በዋናነት በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል መተላለፍ እንደሚጀምር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከጣቢያው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቴሌቪዥን ጣቢያው የሚከተለውን ብሏል"የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የተመልካቹን ፍላጎት ለማርካት የትዝታችንን ምልክት የንባብ ልምምዳችን በኩር የስነጽሑፍ ሥራዎች ቁንጮ የሆውን የክቡር ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ታላቁን የፈጠራ ሥራ ‹‹ ፍቅር እስከ መቃብር ›› መፅሐፍን ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ ወደ ፊልም በመቀየር እንድትመለከቱት የአዲስ ዓመት ስጦታ በማድረግ አበርክቷል።
ይኸም ስጦታ ከመስከረም 1-5 2017 ዓ.ም የፊልሙን አራት ክፍሎች በETV ዜና ቻናል፣ በETV መዝናኛ ቻናል ፣ በEBC World የYOU TUBE ገፅ እና በፌስ ቡክ ቲክቶክ እና ኹሉም ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ለክቡራን ተመልካቾቻቸን ቀርቧል።
በቀጣይም ከጥቂት ቀናት በኋላ የ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› ፊልም ሁሉም ክፍሎች በዋናነት በETV መዝናኛ ቻናል መተላለፍ ይጀምራሉ።
የፍቅር እስከመቃብርን ትረካ በኢትዮጵያ ራድዮ በወጋየሁ ንጋቱ ተከታትላችሁ ትዝታ የተጋራችሁ አድማጮቻችን ታላቁ ስራ በታላቅ የፊልም ጥበብ ተገልጦ በመደበኛነት እንድትከታተሉን የዘመን ትዝታም እንድትጋሩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዛችኋለን "።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በቀናት ልዩነት በተከታታይ እስከ ክፍል አራት ድረስ ሲተላለፍ የቆየው "ፍቅር እስከ መቃብር" ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በቅርብ ቀን በመደበኛው ስርጭት በዋናነት በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል መተላለፍ እንደሚጀምር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከጣቢያው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቴሌቪዥን ጣቢያው የሚከተለውን ብሏል"የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የተመልካቹን ፍላጎት ለማርካት የትዝታችንን ምልክት የንባብ ልምምዳችን በኩር የስነጽሑፍ ሥራዎች ቁንጮ የሆውን የክቡር ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ታላቁን የፈጠራ ሥራ ‹‹ ፍቅር እስከ መቃብር ›› መፅሐፍን ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ ወደ ፊልም በመቀየር እንድትመለከቱት የአዲስ ዓመት ስጦታ በማድረግ አበርክቷል።
ይኸም ስጦታ ከመስከረም 1-5 2017 ዓ.ም የፊልሙን አራት ክፍሎች በETV ዜና ቻናል፣ በETV መዝናኛ ቻናል ፣ በEBC World የYOU TUBE ገፅ እና በፌስ ቡክ ቲክቶክ እና ኹሉም ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ለክቡራን ተመልካቾቻቸን ቀርቧል።
በቀጣይም ከጥቂት ቀናት በኋላ የ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› ፊልም ሁሉም ክፍሎች በዋናነት በETV መዝናኛ ቻናል መተላለፍ ይጀምራሉ።
የፍቅር እስከመቃብርን ትረካ በኢትዮጵያ ራድዮ በወጋየሁ ንጋቱ ተከታትላችሁ ትዝታ የተጋራችሁ አድማጮቻችን ታላቁ ስራ በታላቅ የፊልም ጥበብ ተገልጦ በመደበኛነት እንድትከታተሉን የዘመን ትዝታም እንድትጋሩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዛችኋለን "።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ሦስተኛው ዓይን" የሥዕል አውደርዕይ ተከፈተ
የሠዓሊ መሐሪ ተሾመ "ሦስተኛው ዓይን: The third eye" የሥዕል አውደርዕይ ባሳለፍነው ቅዳሜ መስከረም 4 2017 ዓ.ም ቦሌ አትላስ አካባቢ በሚገኘው አናፎራ የጥበብ ማዕከል ውስጥ ለእይታ በቅቷል። ይህ የሥዕል አውደርዕይ ከአንድ ወር በላይ በእይታ ይቆያል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የሠዓሊ መሐሪ ተሾመ "ሦስተኛው ዓይን: The third eye" የሥዕል አውደርዕይ ባሳለፍነው ቅዳሜ መስከረም 4 2017 ዓ.ም ቦሌ አትላስ አካባቢ በሚገኘው አናፎራ የጥበብ ማዕከል ውስጥ ለእይታ በቅቷል። ይህ የሥዕል አውደርዕይ ከአንድ ወር በላይ በእይታ ይቆያል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የመዓዛ ወርቁ አዲስ ድራማ ሊጀምር ነው
ከዚህ ቀደም "ወፌ ቆመች" እና "ደርሶ መልስ" በተሰኙ የሬድዮ እና ቴሌቪዥን ድራማዎችን ጨምሮ በበርካታ የሬድዮና ቴሌቪዥን ድራማዎች የምናውቃት ደራሲ መዓዛ ወርቁ "አላውቅም አናውቅም" የተሰኘ የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ በቅርቡ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከደራሲዋ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተከታታይ ድራማው ከሐሙስ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዲኤስትቪ አቦል ቻናል 465 ላይ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ከዚህ ቀደም "ወፌ ቆመች" እና "ደርሶ መልስ" በተሰኙ የሬድዮ እና ቴሌቪዥን ድራማዎችን ጨምሮ በበርካታ የሬድዮና ቴሌቪዥን ድራማዎች የምናውቃት ደራሲ መዓዛ ወርቁ "አላውቅም አናውቅም" የተሰኘ የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ በቅርቡ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከደራሲዋ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተከታታይ ድራማው ከሐሙስ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዲኤስትቪ አቦል ቻናል 465 ላይ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የዓለም የቱሪዝም ቀን በኢትዮጵያ !
የዓለም የቱሪዝም ቀን ከዛሬ መስከረም 7 እስከ መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስት ቀናት በኢትዮጵያ ይከበራል።
የተለያዩ የኢጋድ አባል ሀገራት፣ ክልሎችና የቱሪዝም ተዋንያን የሚሳተፉበት "Origins travel market" የተሰኘ አውደርዕይ እንደሚካሄድ ጠቅሷል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ቀኑን በማስመልከት መስከረም 7 2017 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ኹነት ማዘጋጀቱን ገልጿል።
በሁነት ዝግጅቱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት ይፋ እንደሚሆንም አመልክቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የዓለም የቱሪዝም ቀን ከዛሬ መስከረም 7 እስከ መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስት ቀናት በኢትዮጵያ ይከበራል።
የተለያዩ የኢጋድ አባል ሀገራት፣ ክልሎችና የቱሪዝም ተዋንያን የሚሳተፉበት "Origins travel market" የተሰኘ አውደርዕይ እንደሚካሄድ ጠቅሷል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ቀኑን በማስመልከት መስከረም 7 2017 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ኹነት ማዘጋጀቱን ገልጿል።
በሁነት ዝግጅቱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት ይፋ እንደሚሆንም አመልክቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ሠዓሊ ወንድወሰን ከበደ አፍሪካ መድረክ!
ሠዓሊ ወንድወሰን ከበደ የአፍሪካ የዘንድሮ 2024 ለፋሽን እና የጥበብ ሽልማት እውቅና ከሚያገኙ100 አፍሪካውያን ምርጥ ጥበበኞች አንዱ ሆኖ ተሰይሟል።
ይህ የሽልማት ዝግጅት ዘንድሮው ህዳር ወር ላይ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሠዓሊ ወንድወሰን ከበደ የአፍሪካ የዘንድሮ 2024 ለፋሽን እና የጥበብ ሽልማት እውቅና ከሚያገኙ100 አፍሪካውያን ምርጥ ጥበበኞች አንዱ ሆኖ ተሰይሟል።
ይህ የሽልማት ዝግጅት ዘንድሮው ህዳር ወር ላይ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ ከሀገር ተሰደዱ
ከሶስት ወራት በፊት ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ፤ ሀገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ሁለቱ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ በመንግስት የጸጥታ አባላት በተሰጣቸው “ለህይወታቸው የሚያሰጋ” “ማስጠንቀቂያ” እና ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሚደረግባቸው “ክትትል” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
ጋዜጠኛ በላይ እና በቃሉ 11 ቀናት የፈጀ “አስቸጋሪ ጉዞ” በማድረግ ከሀገር የወጡት፤ ባለፈው ሳምንት ሰኞ ጳጉሜ 4፤ 2016 መሆኑን አስረድተዋል። ሆኖም ጋዜጠኞቹ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ሀገር፤ “ከደህንነት ስጋት” ጋር በተያያዘ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ሁለቱ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገው የነበረው፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ባበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ነበር።
“አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው በቃሉ፤ ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አንድ ቀን በኋላ በቁጥጥር ስር ውሏል። ጋዜጠኛው በዚያው ዓመት ነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ተወስዶ ለዘጠኝ ወራት በእስር ላይ ቆይቷል።
እንደ በቃሉ ሁሉ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታስሮ የነበረው ጋዜጠኛ በላይ፤ “በየቀኑ በህይወት የመቆየት እና ያለመቆየት እድላችን ሁልጊዜ ጠባብ እንደሆነ እያሰብን ነው ያን ሁሉ ጊዜ የቆየነው” ሲል ይገልጻል። “ኢትዮ ኒውስ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ፤ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ላይ የቆየው ለሰባት ወራት ነው።
©️መረጀው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ከሶስት ወራት በፊት ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ፤ ሀገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ሁለቱ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ በመንግስት የጸጥታ አባላት በተሰጣቸው “ለህይወታቸው የሚያሰጋ” “ማስጠንቀቂያ” እና ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሚደረግባቸው “ክትትል” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
ጋዜጠኛ በላይ እና በቃሉ 11 ቀናት የፈጀ “አስቸጋሪ ጉዞ” በማድረግ ከሀገር የወጡት፤ ባለፈው ሳምንት ሰኞ ጳጉሜ 4፤ 2016 መሆኑን አስረድተዋል። ሆኖም ጋዜጠኞቹ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ሀገር፤ “ከደህንነት ስጋት” ጋር በተያያዘ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ሁለቱ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገው የነበረው፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ባበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ነበር።
“አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው በቃሉ፤ ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አንድ ቀን በኋላ በቁጥጥር ስር ውሏል። ጋዜጠኛው በዚያው ዓመት ነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ተወስዶ ለዘጠኝ ወራት በእስር ላይ ቆይቷል።
እንደ በቃሉ ሁሉ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታስሮ የነበረው ጋዜጠኛ በላይ፤ “በየቀኑ በህይወት የመቆየት እና ያለመቆየት እድላችን ሁልጊዜ ጠባብ እንደሆነ እያሰብን ነው ያን ሁሉ ጊዜ የቆየነው” ሲል ይገልጻል። “ኢትዮ ኒውስ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ፤ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ላይ የቆየው ለሰባት ወራት ነው።
©️መረጀው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌 የድምፃዊ አንዷለም ጎሳ"አያንቱ" አልበም
የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ "አያንቱ" የተሰኘው የአፋን ኦሮሞ የሙዚቃ አልበም መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ዩቲዩብን ጨምሮ በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል ተብሏል።
"አያንቱ" የሙዚቃ አልበም በውስጡ 16 ሙዚቃዎችን ያካተተ ሲሆን፣ 16ቱ የሙዚቃ ስራዎች የሀገራችንን የተለያዩ የሙዚቃ ስልቶችን ተጠቅመው የቀረቡ ናቸው።
አልበሙ በርካታ ሙዚቀኞችን እና ባለሙያዎችን አሳትፏል ከእነዚህም መካከል ኤፍሬም ብርቅነህ፣ ሚኪ ጃኖ፣ እዮብ ባልቻ፣ አንተነ (አቡዝ) እና ኤንዲ ቤተ ዜማ በሙዚቃ ቅንብር ተሳትፈዋል።
እንዲሁም በታዋቂው የሙዚቃ ባለሙያ አበጋዝ ሾይታ ማስተር ተደርጓል።
በግጥም እና ዜማ ዘርፍ ላሊሳ ኢንድሪስ፣ አቦማ ማርጋ ፣ አርቲስት አቢራሂም መሀመድ፣ ሞቲ አባ ዳሌ እና ፋጤ አኒያ፣ ናሆም መኩሪያ፣ ኢፊረም ብርቅነህ፣ ዘርዓ ብሩክ እና ኢሳያስ ተሳትፈዋል።
አርቲስት አንዱአለም ጎሳ የሙዚቃ አልበም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከ6 አመታት በላይ ፈጅቶበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ "አያንቱ" የተሰኘው የአፋን ኦሮሞ የሙዚቃ አልበም መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ዩቲዩብን ጨምሮ በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል ተብሏል።
"አያንቱ" የሙዚቃ አልበም በውስጡ 16 ሙዚቃዎችን ያካተተ ሲሆን፣ 16ቱ የሙዚቃ ስራዎች የሀገራችንን የተለያዩ የሙዚቃ ስልቶችን ተጠቅመው የቀረቡ ናቸው።
አልበሙ በርካታ ሙዚቀኞችን እና ባለሙያዎችን አሳትፏል ከእነዚህም መካከል ኤፍሬም ብርቅነህ፣ ሚኪ ጃኖ፣ እዮብ ባልቻ፣ አንተነ (አቡዝ) እና ኤንዲ ቤተ ዜማ በሙዚቃ ቅንብር ተሳትፈዋል።
እንዲሁም በታዋቂው የሙዚቃ ባለሙያ አበጋዝ ሾይታ ማስተር ተደርጓል።
በግጥም እና ዜማ ዘርፍ ላሊሳ ኢንድሪስ፣ አቦማ ማርጋ ፣ አርቲስት አቢራሂም መሀመድ፣ ሞቲ አባ ዳሌ እና ፋጤ አኒያ፣ ናሆም መኩሪያ፣ ኢፊረም ብርቅነህ፣ ዘርዓ ብሩክ እና ኢሳያስ ተሳትፈዋል።
አርቲስት አንዱአለም ጎሳ የሙዚቃ አልበም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከ6 አመታት በላይ ፈጅቶበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የአንጋፋው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃ/ማርያም ማስታወሻ ዝግጅት የፊታችን እሁድ በወመዘክር ይካሄዳል።
የዛሬ 30 ዓመት ህይወቱ ያለፈው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም በሙያ ባልደረቦቹ የማስታወሻ ዝግጅት ሊደረግለት ነው፡፡
የፊታችን እሁድ መስከረም 12 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ በሚከናወነው በዚህ ዝግጅት፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባልደረቦች ይታደማሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡
በማስታወሻ ዝግጅቱ ላይ፣ ስለ ጌታቸው ምስክርነት የሚሰጡት ጋዜጠኛ ሚሊዮን ተረፈ ፤ ጋዜጠኛ ዋጋዬ በቀለ እና ጋዜጠኛ ታዬ በላቸው ሲሆኑ በተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን የተዘጋጀ የ20 ደቂቃ የድምጽ ዘጋቢ ሥራም እንደሚደመጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የማስታወሻ ዝግጅቱ ሀሳብ አመንጪ እና አዘጋጅ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ሲሆን በዕለቱም ጋዜጠኝነትን የሚያጠኑ ተማሪዎች በመሰናዶው ላይ ይገኛሉ፡፡
አንጋፋው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬድዮ በጠቅላላው ከ 24 ዓመታት በላይ ያገለገለ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ በተለይም በዜና አቀራረብ እና አንባቢነት ለብዙዎች አርአያ የሆነም የሚከበር ጋዜጠኛ ነበር፡፡
የሚድያ ሰው ጌታቸው ኃይለማርያም፣ አሁን በአንጋፋነታቸው እውቅና የተቸራቸውን እንደ ነጋሽ መሀመድ፣ አለምነህ ዋሴ፣ ንግስት ሰልፉ እና ብርቱካን ሀረገወይንን የመሰሉ ባለሙያዎች ለሙያዊ ብቃት እንዲደርሱ በማሰልጠን እና ልምዱን በማካፈል የበኩሉን የተወጣ ባለሙያ ነበር፡፡ ዜና ፋይል የተሰኘውን ፎርማት ለመጀመረያ ጊዜ እንዳስተዋወቀ እና እንደፈጠረ የሚነገርለት ይህ ሰው በብስራተ ወልጌል የሬድዮ ጣቢያም ሙያዊ አደራውን ሲወጣ ነበር፡፡
©️መረጃው የተወዳጅ ሚዲያ ነው
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የዛሬ 30 ዓመት ህይወቱ ያለፈው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም በሙያ ባልደረቦቹ የማስታወሻ ዝግጅት ሊደረግለት ነው፡፡
የፊታችን እሁድ መስከረም 12 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ በሚከናወነው በዚህ ዝግጅት፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባልደረቦች ይታደማሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡
በማስታወሻ ዝግጅቱ ላይ፣ ስለ ጌታቸው ምስክርነት የሚሰጡት ጋዜጠኛ ሚሊዮን ተረፈ ፤ ጋዜጠኛ ዋጋዬ በቀለ እና ጋዜጠኛ ታዬ በላቸው ሲሆኑ በተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን የተዘጋጀ የ20 ደቂቃ የድምጽ ዘጋቢ ሥራም እንደሚደመጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የማስታወሻ ዝግጅቱ ሀሳብ አመንጪ እና አዘጋጅ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ሲሆን በዕለቱም ጋዜጠኝነትን የሚያጠኑ ተማሪዎች በመሰናዶው ላይ ይገኛሉ፡፡
አንጋፋው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬድዮ በጠቅላላው ከ 24 ዓመታት በላይ ያገለገለ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ በተለይም በዜና አቀራረብ እና አንባቢነት ለብዙዎች አርአያ የሆነም የሚከበር ጋዜጠኛ ነበር፡፡
የሚድያ ሰው ጌታቸው ኃይለማርያም፣ አሁን በአንጋፋነታቸው እውቅና የተቸራቸውን እንደ ነጋሽ መሀመድ፣ አለምነህ ዋሴ፣ ንግስት ሰልፉ እና ብርቱካን ሀረገወይንን የመሰሉ ባለሙያዎች ለሙያዊ ብቃት እንዲደርሱ በማሰልጠን እና ልምዱን በማካፈል የበኩሉን የተወጣ ባለሙያ ነበር፡፡ ዜና ፋይል የተሰኘውን ፎርማት ለመጀመረያ ጊዜ እንዳስተዋወቀ እና እንደፈጠረ የሚነገርለት ይህ ሰው በብስራተ ወልጌል የሬድዮ ጣቢያም ሙያዊ አደራውን ሲወጣ ነበር፡፡
©️መረጃው የተወዳጅ ሚዲያ ነው
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ድምፃዊት አስቴር አወቀ፣ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ እና ሌሎች ሶስት ሴት ኢትዮጵያዊያኖች በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ሊሸለሙ ነው።
በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን የሚያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር ተሸላሚዎች ታውቀዋል። ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ሥነስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዜያት ተካሂዷል።
ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች አምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን ለማክበርና እውቅና ለመስጠት ዝግጅቱ ተጠናቋል፤ የዚህ አመት ተሸላሚዎች በሙሉ ሴቶች ናቸው። በስነ ጥበብ ዘርፍ ዝነኛዋ ድምፃዊት አስቴር አወቀና አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ በስፖርቱ ዘርፍ የማራቶንና የ5000 ሜትር የአለማችን ክብረወሰን ባለቤቶች ትዕግስት አሰፋና ጉዳፍ ፀጋዬ እንዲሁም በቢዝነስ ዘርፍ ርብቃ ሀይሌ ተሸላሚዎች ይሆናሉ።
በዕለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረጋላቸው በርካታ እንግዶች ይገኛሉ፤ ተሸላሚዎቹ ከግዛቶቹና ከተማዎቹ ተወካዮች የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከትላቸዋል።
በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ስራ የሚውል የሙዚቃ ዝግጅት በወጣቷ ድምፃዊት ራሄል ጌቱና በታዋቂው መሳሪያ ተጫዋች ሰላም ስዩም የሚቀርብ ይሆናል።
የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት ይካሄዳል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን የሚያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር ተሸላሚዎች ታውቀዋል። ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ሥነስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዜያት ተካሂዷል።
ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች አምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን ለማክበርና እውቅና ለመስጠት ዝግጅቱ ተጠናቋል፤ የዚህ አመት ተሸላሚዎች በሙሉ ሴቶች ናቸው። በስነ ጥበብ ዘርፍ ዝነኛዋ ድምፃዊት አስቴር አወቀና አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ በስፖርቱ ዘርፍ የማራቶንና የ5000 ሜትር የአለማችን ክብረወሰን ባለቤቶች ትዕግስት አሰፋና ጉዳፍ ፀጋዬ እንዲሁም በቢዝነስ ዘርፍ ርብቃ ሀይሌ ተሸላሚዎች ይሆናሉ።
በዕለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረጋላቸው በርካታ እንግዶች ይገኛሉ፤ ተሸላሚዎቹ ከግዛቶቹና ከተማዎቹ ተወካዮች የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከትላቸዋል።
በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ስራ የሚውል የሙዚቃ ዝግጅት በወጣቷ ድምፃዊት ራሄል ጌቱና በታዋቂው መሳሪያ ተጫዋች ሰላም ስዩም የሚቀርብ ይሆናል።
የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት ይካሄዳል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"እሺ አትለኝም ወይ" ሙዚቃ ነገ ይለቀቃል
የድምጻዊት ማህሌት ወንድሙ "እሺ አትለኝም ወይ" የተሰኘ አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሰዋሰው መተግበሪያ በኩል ለአድማጮች ይደርሳል። በዚህ ሙዚቃ ላይ በግጥም ወንድወሰን ይሁብ ፣ በዜማ ምህረትአብ ደስታ፣ሙዚቃ ቅንብር ፋኑ ጊዲቦ ተሳትፉበታል።
ድምጻዊት ማህሌት ከዚህ ቀደም "አምባሰል" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ለአድማጮች ማድረሷ አይዘነጋም።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊት ማህሌት ወንድሙ "እሺ አትለኝም ወይ" የተሰኘ አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሰዋሰው መተግበሪያ በኩል ለአድማጮች ይደርሳል። በዚህ ሙዚቃ ላይ በግጥም ወንድወሰን ይሁብ ፣ በዜማ ምህረትአብ ደስታ፣ሙዚቃ ቅንብር ፋኑ ጊዲቦ ተሳትፉበታል።
ድምጻዊት ማህሌት ከዚህ ቀደም "አምባሰል" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ለአድማጮች ማድረሷ አይዘነጋም።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌 የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ትዝታ" የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ይለቀቃል
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ትዝታ" የተሰኘው የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ይለቀቃል።
ሙዚቃው ላይ በግጥም ወንደሰን ይሁብ፣በዜማ አንተነህ ወራሽ፣ በቅንብር አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ተሳትፈውበታል።የሙዚቃው ቪዲዮው ዳይሬክተር ኤዲተር እመቤት ካሣ ነች።ይህ የሙዚቃ ስራ "ማያዬ" ከተሰኘው የሙዚቃ አልበም ውስጥ የተካተተ ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ትዝታ" የተሰኘው የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ይለቀቃል።
ሙዚቃው ላይ በግጥም ወንደሰን ይሁብ፣በዜማ አንተነህ ወራሽ፣ በቅንብር አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ተሳትፈውበታል።የሙዚቃው ቪዲዮው ዳይሬክተር ኤዲተር እመቤት ካሣ ነች።ይህ የሙዚቃ ስራ "ማያዬ" ከተሰኘው የሙዚቃ አልበም ውስጥ የተካተተ ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌አርቲስት አዜብ ከግማሽ ቀን እስር በኃላ ተፈታለች
ሰሞኑን አርቲስት አዜብ ወርቁ "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት!" የሚል ጽሁፍ በማህበራዊ ሚዲያዋ ካጋራች በኋላ ጽሁፉ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርና በኋላም ከማህበራዊ ገጿ ጽሁፉን ማንሳቷን ማስታወቋ ይታወሳል።
በዚህ ጽሑፍ መነሻ ይሁን በሌላ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት አርቲስት አዜብ ወርቁ ዛሬ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ለግማሽ ቀን ያህል ታስራ እንደነበር ተሰምቷል።
ዛሬ በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜው ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ መለቀቋን ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሰሞኑን አርቲስት አዜብ ወርቁ "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት!" የሚል ጽሁፍ በማህበራዊ ሚዲያዋ ካጋራች በኋላ ጽሁፉ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርና በኋላም ከማህበራዊ ገጿ ጽሁፉን ማንሳቷን ማስታወቋ ይታወሳል።
በዚህ ጽሑፍ መነሻ ይሁን በሌላ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት አርቲስት አዜብ ወርቁ ዛሬ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ለግማሽ ቀን ያህል ታስራ እንደነበር ተሰምቷል።
ዛሬ በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜው ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ መለቀቋን ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ጉርሻና ቅምሻ" መጽሐፍ እሁድ ይመረቃል
በደራሲና ገጣሚ ማትያስ ከተማ የተፃፈዉ "ጉርሻና ቅምሻ" የተሰኘ አዲስ መፅሃፍ የሀገራችን ደራሲዎችና የኪነጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት እሁድ መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዝክር) አዳራሽ ውስጥ ይመረቃል።
በዕለቱም ደራሲ አበራ ለማ፣ ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ፣ፀሐፊተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደረሲ አበረ አዳሙ ፣ጋዜጠኛ ግሩም ተበጀ፣ አዲስ ዘገየ፣ ቤተማርያም ተሾመ እና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲና ገጣሚ ማትያስ ከተማ የተፃፈዉ "ጉርሻና ቅምሻ" የተሰኘ አዲስ መፅሃፍ የሀገራችን ደራሲዎችና የኪነጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት እሁድ መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዝክር) አዳራሽ ውስጥ ይመረቃል።
በዕለቱም ደራሲ አበራ ለማ፣ ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ፣ፀሐፊተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደረሲ አበረ አዳሙ ፣ጋዜጠኛ ግሩም ተበጀ፣ አዲስ ዘገየ፣ ቤተማርያም ተሾመ እና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ ፊልሞች በአውሮፓ ለእይታ ሊቀርቡ ነው።
በሐበሻቪው አዘጋጅነት በለንደን ለ5ተኛ ጊዜ እንዲሁም በማልታ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእይታ ይቀርባሉ ተብሏል።
ለእይታ ከሚቀርቡ ፊልሞች ውስጥ አፊኒ፣አባይ ወይስ ቬጋስ፣ዝምታዬ ፣ላምባዲና የተሰኙ ፊልሞች እንደሚገኙበት ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
አምስተኛው የፊልም ፌስቲቫል በለንደን እና የመጀመሪያው ፊልም ፌስቲቫል በማልታ ሊካሄድ ነው ።በዓመት አንድ ጊዜ በለንደን ፊልም ፌስቲቫል ዝግጅት ይደረጋል። ዘንድሮም ለ5ኛ ጊዜ ይህው ሁነት ይቀጥላል።
ለመጀመሪያ ጊዜም በደሴታማዋ ሀገር ማልታ የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ይካሄዳል።
ከሰሞኑ ቀንም ማልታ 60ኛ የነፃነት በዓሏን እያከበርች ትገኛለች። ሐበሻ ቪው ዝግጅቶችን አሰናድቷል።
ይህንንም ዝግጅት አስመልክቶ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በሀያት ሪጀንሲ የሽኝት መርሐግብር ተካሂዷል።
"ሐበሻ ቪው" በውጪ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ከኢትዮጵያ ሥነጥበብ ፣ ኪነጥበብ ፣ክውን ጥበባት ጋር የሚያገናኙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በሐበሻቪው አዘጋጅነት በለንደን ለ5ተኛ ጊዜ እንዲሁም በማልታ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእይታ ይቀርባሉ ተብሏል።
ለእይታ ከሚቀርቡ ፊልሞች ውስጥ አፊኒ፣አባይ ወይስ ቬጋስ፣ዝምታዬ ፣ላምባዲና የተሰኙ ፊልሞች እንደሚገኙበት ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
አምስተኛው የፊልም ፌስቲቫል በለንደን እና የመጀመሪያው ፊልም ፌስቲቫል በማልታ ሊካሄድ ነው ።በዓመት አንድ ጊዜ በለንደን ፊልም ፌስቲቫል ዝግጅት ይደረጋል። ዘንድሮም ለ5ኛ ጊዜ ይህው ሁነት ይቀጥላል።
ለመጀመሪያ ጊዜም በደሴታማዋ ሀገር ማልታ የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ይካሄዳል።
ከሰሞኑ ቀንም ማልታ 60ኛ የነፃነት በዓሏን እያከበርች ትገኛለች። ሐበሻ ቪው ዝግጅቶችን አሰናድቷል።
ይህንንም ዝግጅት አስመልክቶ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በሀያት ሪጀንሲ የሽኝት መርሐግብር ተካሂዷል።
"ሐበሻ ቪው" በውጪ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ከኢትዮጵያ ሥነጥበብ ፣ ኪነጥበብ ፣ክውን ጥበባት ጋር የሚያገናኙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አፍሪካን እናክብር" ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው
የ2024 "አፍሪካን እናክብር" ወይም "አፍሪካን እናክብር" ፌስቲቫል ከጥቅምት 27 እስከ ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚከበር አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
አፍሪካ ያላትን ባህል፣ ሥነ ጥበብ፣ ቅርስ፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም የቢዝነስ ሀብቶቿን ለዓለም ለማስተዋወቅ ፌስቲቫሉ ጠቀሜታ እንዳለው ነው የተገለፀው።
በተጨማሪም የአፍሪካ ሴቶች እና ወጣቶች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ እና እንዲገኙ ዕድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል።
የተለያዩ ሥራ ፈጣሪ ባለቤቶችም ስራዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ያስችላል ተብሏል።
ፈስቲቫሉ ከፈረንጆቹ 2021 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዚህኛው ዓመት ለማክበር በጋራ እንደሚሰራ ታውቋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኤምባሲዎች በአዘጋጅነት ተሳትፈውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የ2024 "አፍሪካን እናክብር" ወይም "አፍሪካን እናክብር" ፌስቲቫል ከጥቅምት 27 እስከ ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚከበር አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
አፍሪካ ያላትን ባህል፣ ሥነ ጥበብ፣ ቅርስ፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም የቢዝነስ ሀብቶቿን ለዓለም ለማስተዋወቅ ፌስቲቫሉ ጠቀሜታ እንዳለው ነው የተገለፀው።
በተጨማሪም የአፍሪካ ሴቶች እና ወጣቶች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ እና እንዲገኙ ዕድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል።
የተለያዩ ሥራ ፈጣሪ ባለቤቶችም ስራዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ያስችላል ተብሏል።
ፈስቲቫሉ ከፈረንጆቹ 2021 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዚህኛው ዓመት ለማክበር በጋራ እንደሚሰራ ታውቋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኤምባሲዎች በአዘጋጅነት ተሳትፈውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አዳብና ፌስቲቫል" ለ3ኛ ጊዜ ሊካሄድ ነው
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "አዳብና ፌስቲቫል" ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስተኛ ጊዜ በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ በተለያዩ መርሐግብሮች እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ይህ ፌስቲቫል በዋናነትም በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ኬላ ከተማ መስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም በአደባባይ በትልቅ ፕሮግራም እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
በአዳብና ፌስቲቫል ከ30 እስከ 100 ሺህ ጎብኚዎችን የሚጠበቁ ሲሆን በ50 እናቶች የተዘጋጀ 100 ኪሎ ክትፎንና 100 ኪሎ የክትፎ ቅቤ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ለማስፈር ስራዎች እየተሰራ እንደሆነ ተነግሯል።
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማኅበር አዳብና የጉራጌ የልጃገረዶችና ወንድ ወጣቶች ባህላዊ ጨዋታ መተጫጫ ፌስቲቫል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) እንዲመዘገብ ለማድረግ እየሠራ ይገኛል።
የአዳብና ባህል የልጃገረዶችና ወጣት ወንዶች ጨዋታና መተጫጫ ስነስርዓት ሲሆን ባህሉ በጥናት በተረጋገጠ መረጃ መሰረት 800 ዓመታት በፊት በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ አካባቢ ለዘመናት ሲከበር እንደኖረ ማኀበሩ ገልጿል።
ይህ ድንቅ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ደብዝዞና ለጠፋ ታቃርቦ የነበረ ሲሆን የአዳብና በከስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከአካባቢው የመንግስት መዋቅሮች ጋር በመሆን ባደረገው ጥረት ባህሉ ጥንታዊ ወጉና ቱባ ባህሉ ይዞ በከፍተኛ ሁኔታ በማንሰራራት በአሁን ሰዓት በአካባቢው ላይ በፌስቲቫልነት እየተከበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "አዳብና ፌስቲቫል" ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስተኛ ጊዜ በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ በተለያዩ መርሐግብሮች እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ይህ ፌስቲቫል በዋናነትም በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ኬላ ከተማ መስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም በአደባባይ በትልቅ ፕሮግራም እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
በአዳብና ፌስቲቫል ከ30 እስከ 100 ሺህ ጎብኚዎችን የሚጠበቁ ሲሆን በ50 እናቶች የተዘጋጀ 100 ኪሎ ክትፎንና 100 ኪሎ የክትፎ ቅቤ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ለማስፈር ስራዎች እየተሰራ እንደሆነ ተነግሯል።
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማኅበር አዳብና የጉራጌ የልጃገረዶችና ወንድ ወጣቶች ባህላዊ ጨዋታ መተጫጫ ፌስቲቫል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) እንዲመዘገብ ለማድረግ እየሠራ ይገኛል።
የአዳብና ባህል የልጃገረዶችና ወጣት ወንዶች ጨዋታና መተጫጫ ስነስርዓት ሲሆን ባህሉ በጥናት በተረጋገጠ መረጃ መሰረት 800 ዓመታት በፊት በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ አካባቢ ለዘመናት ሲከበር እንደኖረ ማኀበሩ ገልጿል።
ይህ ድንቅ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ደብዝዞና ለጠፋ ታቃርቦ የነበረ ሲሆን የአዳብና በከስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከአካባቢው የመንግስት መዋቅሮች ጋር በመሆን ባደረገው ጥረት ባህሉ ጥንታዊ ወጉና ቱባ ባህሉ ይዞ በከፍተኛ ሁኔታ በማንሰራራት በአሁን ሰዓት በአካባቢው ላይ በፌስቲቫልነት እየተከበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1