📌የመዓዛ ወርቁ አዲስ ድራማ ሊጀምር ነው
ከዚህ ቀደም "ወፌ ቆመች" እና "ደርሶ መልስ" በተሰኙ የሬድዮ እና ቴሌቪዥን ድራማዎችን ጨምሮ በበርካታ የሬድዮና ቴሌቪዥን ድራማዎች የምናውቃት ደራሲ መዓዛ ወርቁ "አላውቅም አናውቅም" የተሰኘ የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ በቅርቡ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከደራሲዋ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተከታታይ ድራማው ከሐሙስ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዲኤስትቪ አቦል ቻናል 465 ላይ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ከዚህ ቀደም "ወፌ ቆመች" እና "ደርሶ መልስ" በተሰኙ የሬድዮ እና ቴሌቪዥን ድራማዎችን ጨምሮ በበርካታ የሬድዮና ቴሌቪዥን ድራማዎች የምናውቃት ደራሲ መዓዛ ወርቁ "አላውቅም አናውቅም" የተሰኘ የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ በቅርቡ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከደራሲዋ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተከታታይ ድራማው ከሐሙስ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዲኤስትቪ አቦል ቻናል 465 ላይ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ መተላለፍ ይጀምራል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የዓለም የቱሪዝም ቀን በኢትዮጵያ !
የዓለም የቱሪዝም ቀን ከዛሬ መስከረም 7 እስከ መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስት ቀናት በኢትዮጵያ ይከበራል።
የተለያዩ የኢጋድ አባል ሀገራት፣ ክልሎችና የቱሪዝም ተዋንያን የሚሳተፉበት "Origins travel market" የተሰኘ አውደርዕይ እንደሚካሄድ ጠቅሷል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ቀኑን በማስመልከት መስከረም 7 2017 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ኹነት ማዘጋጀቱን ገልጿል።
በሁነት ዝግጅቱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት ይፋ እንደሚሆንም አመልክቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የዓለም የቱሪዝም ቀን ከዛሬ መስከረም 7 እስከ መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስት ቀናት በኢትዮጵያ ይከበራል።
የተለያዩ የኢጋድ አባል ሀገራት፣ ክልሎችና የቱሪዝም ተዋንያን የሚሳተፉበት "Origins travel market" የተሰኘ አውደርዕይ እንደሚካሄድ ጠቅሷል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ቀኑን በማስመልከት መስከረም 7 2017 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ኹነት ማዘጋጀቱን ገልጿል።
በሁነት ዝግጅቱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት ይፋ እንደሚሆንም አመልክቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ሠዓሊ ወንድወሰን ከበደ አፍሪካ መድረክ!
ሠዓሊ ወንድወሰን ከበደ የአፍሪካ የዘንድሮ 2024 ለፋሽን እና የጥበብ ሽልማት እውቅና ከሚያገኙ100 አፍሪካውያን ምርጥ ጥበበኞች አንዱ ሆኖ ተሰይሟል።
ይህ የሽልማት ዝግጅት ዘንድሮው ህዳር ወር ላይ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሠዓሊ ወንድወሰን ከበደ የአፍሪካ የዘንድሮ 2024 ለፋሽን እና የጥበብ ሽልማት እውቅና ከሚያገኙ100 አፍሪካውያን ምርጥ ጥበበኞች አንዱ ሆኖ ተሰይሟል።
ይህ የሽልማት ዝግጅት ዘንድሮው ህዳር ወር ላይ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ ከሀገር ተሰደዱ
ከሶስት ወራት በፊት ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ፤ ሀገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ሁለቱ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ በመንግስት የጸጥታ አባላት በተሰጣቸው “ለህይወታቸው የሚያሰጋ” “ማስጠንቀቂያ” እና ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሚደረግባቸው “ክትትል” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
ጋዜጠኛ በላይ እና በቃሉ 11 ቀናት የፈጀ “አስቸጋሪ ጉዞ” በማድረግ ከሀገር የወጡት፤ ባለፈው ሳምንት ሰኞ ጳጉሜ 4፤ 2016 መሆኑን አስረድተዋል። ሆኖም ጋዜጠኞቹ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ሀገር፤ “ከደህንነት ስጋት” ጋር በተያያዘ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ሁለቱ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገው የነበረው፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ባበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ነበር።
“አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው በቃሉ፤ ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አንድ ቀን በኋላ በቁጥጥር ስር ውሏል። ጋዜጠኛው በዚያው ዓመት ነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ተወስዶ ለዘጠኝ ወራት በእስር ላይ ቆይቷል።
እንደ በቃሉ ሁሉ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታስሮ የነበረው ጋዜጠኛ በላይ፤ “በየቀኑ በህይወት የመቆየት እና ያለመቆየት እድላችን ሁልጊዜ ጠባብ እንደሆነ እያሰብን ነው ያን ሁሉ ጊዜ የቆየነው” ሲል ይገልጻል። “ኢትዮ ኒውስ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ፤ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ላይ የቆየው ለሰባት ወራት ነው።
©️መረጀው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ከሶስት ወራት በፊት ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ፤ ሀገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ሁለቱ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ በመንግስት የጸጥታ አባላት በተሰጣቸው “ለህይወታቸው የሚያሰጋ” “ማስጠንቀቂያ” እና ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሚደረግባቸው “ክትትል” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
ጋዜጠኛ በላይ እና በቃሉ 11 ቀናት የፈጀ “አስቸጋሪ ጉዞ” በማድረግ ከሀገር የወጡት፤ ባለፈው ሳምንት ሰኞ ጳጉሜ 4፤ 2016 መሆኑን አስረድተዋል። ሆኖም ጋዜጠኞቹ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ሀገር፤ “ከደህንነት ስጋት” ጋር በተያያዘ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ሁለቱ ጋዜጠኞች ለእስር ተዳርገው የነበረው፤ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ባበቃው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ነበር።
“አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው በቃሉ፤ ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አንድ ቀን በኋላ በቁጥጥር ስር ውሏል። ጋዜጠኛው በዚያው ዓመት ነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ተወስዶ ለዘጠኝ ወራት በእስር ላይ ቆይቷል።
እንደ በቃሉ ሁሉ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታስሮ የነበረው ጋዜጠኛ በላይ፤ “በየቀኑ በህይወት የመቆየት እና ያለመቆየት እድላችን ሁልጊዜ ጠባብ እንደሆነ እያሰብን ነው ያን ሁሉ ጊዜ የቆየነው” ሲል ይገልጻል። “ኢትዮ ኒውስ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ፤ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ላይ የቆየው ለሰባት ወራት ነው።
©️መረጀው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌 የድምፃዊ አንዷለም ጎሳ"አያንቱ" አልበም
የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ "አያንቱ" የተሰኘው የአፋን ኦሮሞ የሙዚቃ አልበም መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ዩቲዩብን ጨምሮ በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል ተብሏል።
"አያንቱ" የሙዚቃ አልበም በውስጡ 16 ሙዚቃዎችን ያካተተ ሲሆን፣ 16ቱ የሙዚቃ ስራዎች የሀገራችንን የተለያዩ የሙዚቃ ስልቶችን ተጠቅመው የቀረቡ ናቸው።
አልበሙ በርካታ ሙዚቀኞችን እና ባለሙያዎችን አሳትፏል ከእነዚህም መካከል ኤፍሬም ብርቅነህ፣ ሚኪ ጃኖ፣ እዮብ ባልቻ፣ አንተነ (አቡዝ) እና ኤንዲ ቤተ ዜማ በሙዚቃ ቅንብር ተሳትፈዋል።
እንዲሁም በታዋቂው የሙዚቃ ባለሙያ አበጋዝ ሾይታ ማስተር ተደርጓል።
በግጥም እና ዜማ ዘርፍ ላሊሳ ኢንድሪስ፣ አቦማ ማርጋ ፣ አርቲስት አቢራሂም መሀመድ፣ ሞቲ አባ ዳሌ እና ፋጤ አኒያ፣ ናሆም መኩሪያ፣ ኢፊረም ብርቅነህ፣ ዘርዓ ብሩክ እና ኢሳያስ ተሳትፈዋል።
አርቲስት አንዱአለም ጎሳ የሙዚቃ አልበም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከ6 አመታት በላይ ፈጅቶበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ "አያንቱ" የተሰኘው የአፋን ኦሮሞ የሙዚቃ አልበም መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ዩቲዩብን ጨምሮ በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል ተብሏል።
"አያንቱ" የሙዚቃ አልበም በውስጡ 16 ሙዚቃዎችን ያካተተ ሲሆን፣ 16ቱ የሙዚቃ ስራዎች የሀገራችንን የተለያዩ የሙዚቃ ስልቶችን ተጠቅመው የቀረቡ ናቸው።
አልበሙ በርካታ ሙዚቀኞችን እና ባለሙያዎችን አሳትፏል ከእነዚህም መካከል ኤፍሬም ብርቅነህ፣ ሚኪ ጃኖ፣ እዮብ ባልቻ፣ አንተነ (አቡዝ) እና ኤንዲ ቤተ ዜማ በሙዚቃ ቅንብር ተሳትፈዋል።
እንዲሁም በታዋቂው የሙዚቃ ባለሙያ አበጋዝ ሾይታ ማስተር ተደርጓል።
በግጥም እና ዜማ ዘርፍ ላሊሳ ኢንድሪስ፣ አቦማ ማርጋ ፣ አርቲስት አቢራሂም መሀመድ፣ ሞቲ አባ ዳሌ እና ፋጤ አኒያ፣ ናሆም መኩሪያ፣ ኢፊረም ብርቅነህ፣ ዘርዓ ብሩክ እና ኢሳያስ ተሳትፈዋል።
አርቲስት አንዱአለም ጎሳ የሙዚቃ አልበም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከ6 አመታት በላይ ፈጅቶበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የአንጋፋው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃ/ማርያም ማስታወሻ ዝግጅት የፊታችን እሁድ በወመዘክር ይካሄዳል።
የዛሬ 30 ዓመት ህይወቱ ያለፈው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም በሙያ ባልደረቦቹ የማስታወሻ ዝግጅት ሊደረግለት ነው፡፡
የፊታችን እሁድ መስከረም 12 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ በሚከናወነው በዚህ ዝግጅት፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባልደረቦች ይታደማሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡
በማስታወሻ ዝግጅቱ ላይ፣ ስለ ጌታቸው ምስክርነት የሚሰጡት ጋዜጠኛ ሚሊዮን ተረፈ ፤ ጋዜጠኛ ዋጋዬ በቀለ እና ጋዜጠኛ ታዬ በላቸው ሲሆኑ በተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን የተዘጋጀ የ20 ደቂቃ የድምጽ ዘጋቢ ሥራም እንደሚደመጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የማስታወሻ ዝግጅቱ ሀሳብ አመንጪ እና አዘጋጅ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ሲሆን በዕለቱም ጋዜጠኝነትን የሚያጠኑ ተማሪዎች በመሰናዶው ላይ ይገኛሉ፡፡
አንጋፋው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬድዮ በጠቅላላው ከ 24 ዓመታት በላይ ያገለገለ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ በተለይም በዜና አቀራረብ እና አንባቢነት ለብዙዎች አርአያ የሆነም የሚከበር ጋዜጠኛ ነበር፡፡
የሚድያ ሰው ጌታቸው ኃይለማርያም፣ አሁን በአንጋፋነታቸው እውቅና የተቸራቸውን እንደ ነጋሽ መሀመድ፣ አለምነህ ዋሴ፣ ንግስት ሰልፉ እና ብርቱካን ሀረገወይንን የመሰሉ ባለሙያዎች ለሙያዊ ብቃት እንዲደርሱ በማሰልጠን እና ልምዱን በማካፈል የበኩሉን የተወጣ ባለሙያ ነበር፡፡ ዜና ፋይል የተሰኘውን ፎርማት ለመጀመረያ ጊዜ እንዳስተዋወቀ እና እንደፈጠረ የሚነገርለት ይህ ሰው በብስራተ ወልጌል የሬድዮ ጣቢያም ሙያዊ አደራውን ሲወጣ ነበር፡፡
©️መረጃው የተወዳጅ ሚዲያ ነው
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የዛሬ 30 ዓመት ህይወቱ ያለፈው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም በሙያ ባልደረቦቹ የማስታወሻ ዝግጅት ሊደረግለት ነው፡፡
የፊታችን እሁድ መስከረም 12 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ በሚከናወነው በዚህ ዝግጅት፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባልደረቦች ይታደማሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡
በማስታወሻ ዝግጅቱ ላይ፣ ስለ ጌታቸው ምስክርነት የሚሰጡት ጋዜጠኛ ሚሊዮን ተረፈ ፤ ጋዜጠኛ ዋጋዬ በቀለ እና ጋዜጠኛ ታዬ በላቸው ሲሆኑ በተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን የተዘጋጀ የ20 ደቂቃ የድምጽ ዘጋቢ ሥራም እንደሚደመጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የማስታወሻ ዝግጅቱ ሀሳብ አመንጪ እና አዘጋጅ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ሲሆን በዕለቱም ጋዜጠኝነትን የሚያጠኑ ተማሪዎች በመሰናዶው ላይ ይገኛሉ፡፡
አንጋፋው ጋዜጠኛ ጌታቸው ኃይለማርያም፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬድዮ በጠቅላላው ከ 24 ዓመታት በላይ ያገለገለ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ በተለይም በዜና አቀራረብ እና አንባቢነት ለብዙዎች አርአያ የሆነም የሚከበር ጋዜጠኛ ነበር፡፡
የሚድያ ሰው ጌታቸው ኃይለማርያም፣ አሁን በአንጋፋነታቸው እውቅና የተቸራቸውን እንደ ነጋሽ መሀመድ፣ አለምነህ ዋሴ፣ ንግስት ሰልፉ እና ብርቱካን ሀረገወይንን የመሰሉ ባለሙያዎች ለሙያዊ ብቃት እንዲደርሱ በማሰልጠን እና ልምዱን በማካፈል የበኩሉን የተወጣ ባለሙያ ነበር፡፡ ዜና ፋይል የተሰኘውን ፎርማት ለመጀመረያ ጊዜ እንዳስተዋወቀ እና እንደፈጠረ የሚነገርለት ይህ ሰው በብስራተ ወልጌል የሬድዮ ጣቢያም ሙያዊ አደራውን ሲወጣ ነበር፡፡
©️መረጃው የተወዳጅ ሚዲያ ነው
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ድምፃዊት አስቴር አወቀ፣ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ እና ሌሎች ሶስት ሴት ኢትዮጵያዊያኖች በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ሊሸለሙ ነው።
በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን የሚያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር ተሸላሚዎች ታውቀዋል። ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ሥነስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዜያት ተካሂዷል።
ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች አምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን ለማክበርና እውቅና ለመስጠት ዝግጅቱ ተጠናቋል፤ የዚህ አመት ተሸላሚዎች በሙሉ ሴቶች ናቸው። በስነ ጥበብ ዘርፍ ዝነኛዋ ድምፃዊት አስቴር አወቀና አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ በስፖርቱ ዘርፍ የማራቶንና የ5000 ሜትር የአለማችን ክብረወሰን ባለቤቶች ትዕግስት አሰፋና ጉዳፍ ፀጋዬ እንዲሁም በቢዝነስ ዘርፍ ርብቃ ሀይሌ ተሸላሚዎች ይሆናሉ።
በዕለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረጋላቸው በርካታ እንግዶች ይገኛሉ፤ ተሸላሚዎቹ ከግዛቶቹና ከተማዎቹ ተወካዮች የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከትላቸዋል።
በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ስራ የሚውል የሙዚቃ ዝግጅት በወጣቷ ድምፃዊት ራሄል ጌቱና በታዋቂው መሳሪያ ተጫዋች ሰላም ስዩም የሚቀርብ ይሆናል።
የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት ይካሄዳል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን የሚያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር ተሸላሚዎች ታውቀዋል። ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ሥነስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዜያት ተካሂዷል።
ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች አምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን ለማክበርና እውቅና ለመስጠት ዝግጅቱ ተጠናቋል፤ የዚህ አመት ተሸላሚዎች በሙሉ ሴቶች ናቸው። በስነ ጥበብ ዘርፍ ዝነኛዋ ድምፃዊት አስቴር አወቀና አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ በስፖርቱ ዘርፍ የማራቶንና የ5000 ሜትር የአለማችን ክብረወሰን ባለቤቶች ትዕግስት አሰፋና ጉዳፍ ፀጋዬ እንዲሁም በቢዝነስ ዘርፍ ርብቃ ሀይሌ ተሸላሚዎች ይሆናሉ።
በዕለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረጋላቸው በርካታ እንግዶች ይገኛሉ፤ ተሸላሚዎቹ ከግዛቶቹና ከተማዎቹ ተወካዮች የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከትላቸዋል።
በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ስራ የሚውል የሙዚቃ ዝግጅት በወጣቷ ድምፃዊት ራሄል ጌቱና በታዋቂው መሳሪያ ተጫዋች ሰላም ስዩም የሚቀርብ ይሆናል።
የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት ይካሄዳል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"እሺ አትለኝም ወይ" ሙዚቃ ነገ ይለቀቃል
የድምጻዊት ማህሌት ወንድሙ "እሺ አትለኝም ወይ" የተሰኘ አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሰዋሰው መተግበሪያ በኩል ለአድማጮች ይደርሳል። በዚህ ሙዚቃ ላይ በግጥም ወንድወሰን ይሁብ ፣ በዜማ ምህረትአብ ደስታ፣ሙዚቃ ቅንብር ፋኑ ጊዲቦ ተሳትፉበታል።
ድምጻዊት ማህሌት ከዚህ ቀደም "አምባሰል" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ለአድማጮች ማድረሷ አይዘነጋም።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊት ማህሌት ወንድሙ "እሺ አትለኝም ወይ" የተሰኘ አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሰዋሰው መተግበሪያ በኩል ለአድማጮች ይደርሳል። በዚህ ሙዚቃ ላይ በግጥም ወንድወሰን ይሁብ ፣ በዜማ ምህረትአብ ደስታ፣ሙዚቃ ቅንብር ፋኑ ጊዲቦ ተሳትፉበታል።
ድምጻዊት ማህሌት ከዚህ ቀደም "አምባሰል" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ለአድማጮች ማድረሷ አይዘነጋም።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌 የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ትዝታ" የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ይለቀቃል
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ትዝታ" የተሰኘው የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ይለቀቃል።
ሙዚቃው ላይ በግጥም ወንደሰን ይሁብ፣በዜማ አንተነህ ወራሽ፣ በቅንብር አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ተሳትፈውበታል።የሙዚቃው ቪዲዮው ዳይሬክተር ኤዲተር እመቤት ካሣ ነች።ይህ የሙዚቃ ስራ "ማያዬ" ከተሰኘው የሙዚቃ አልበም ውስጥ የተካተተ ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ትዝታ" የተሰኘው የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ በኩል ይለቀቃል።
ሙዚቃው ላይ በግጥም ወንደሰን ይሁብ፣በዜማ አንተነህ ወራሽ፣ በቅንብር አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ተሳትፈውበታል።የሙዚቃው ቪዲዮው ዳይሬክተር ኤዲተር እመቤት ካሣ ነች።ይህ የሙዚቃ ስራ "ማያዬ" ከተሰኘው የሙዚቃ አልበም ውስጥ የተካተተ ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌አርቲስት አዜብ ከግማሽ ቀን እስር በኃላ ተፈታለች
ሰሞኑን አርቲስት አዜብ ወርቁ "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት!" የሚል ጽሁፍ በማህበራዊ ሚዲያዋ ካጋራች በኋላ ጽሁፉ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርና በኋላም ከማህበራዊ ገጿ ጽሁፉን ማንሳቷን ማስታወቋ ይታወሳል።
በዚህ ጽሑፍ መነሻ ይሁን በሌላ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት አርቲስት አዜብ ወርቁ ዛሬ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ለግማሽ ቀን ያህል ታስራ እንደነበር ተሰምቷል።
ዛሬ በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜው ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ መለቀቋን ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሰሞኑን አርቲስት አዜብ ወርቁ "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት!" የሚል ጽሁፍ በማህበራዊ ሚዲያዋ ካጋራች በኋላ ጽሁፉ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርና በኋላም ከማህበራዊ ገጿ ጽሁፉን ማንሳቷን ማስታወቋ ይታወሳል።
በዚህ ጽሑፍ መነሻ ይሁን በሌላ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት አርቲስት አዜብ ወርቁ ዛሬ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ለግማሽ ቀን ያህል ታስራ እንደነበር ተሰምቷል።
ዛሬ በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜው ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ መለቀቋን ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ጉርሻና ቅምሻ" መጽሐፍ እሁድ ይመረቃል
በደራሲና ገጣሚ ማትያስ ከተማ የተፃፈዉ "ጉርሻና ቅምሻ" የተሰኘ አዲስ መፅሃፍ የሀገራችን ደራሲዎችና የኪነጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት እሁድ መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዝክር) አዳራሽ ውስጥ ይመረቃል።
በዕለቱም ደራሲ አበራ ለማ፣ ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ፣ፀሐፊተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደረሲ አበረ አዳሙ ፣ጋዜጠኛ ግሩም ተበጀ፣ አዲስ ዘገየ፣ ቤተማርያም ተሾመ እና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲና ገጣሚ ማትያስ ከተማ የተፃፈዉ "ጉርሻና ቅምሻ" የተሰኘ አዲስ መፅሃፍ የሀገራችን ደራሲዎችና የኪነጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት እሁድ መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዝክር) አዳራሽ ውስጥ ይመረቃል።
በዕለቱም ደራሲ አበራ ለማ፣ ደራሲ ኃ/መለኮት መዋዕል ፣ፀሐፊተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደረሲ አበረ አዳሙ ፣ጋዜጠኛ ግሩም ተበጀ፣ አዲስ ዘገየ፣ ቤተማርያም ተሾመ እና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ ፊልሞች በአውሮፓ ለእይታ ሊቀርቡ ነው።
በሐበሻቪው አዘጋጅነት በለንደን ለ5ተኛ ጊዜ እንዲሁም በማልታ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእይታ ይቀርባሉ ተብሏል።
ለእይታ ከሚቀርቡ ፊልሞች ውስጥ አፊኒ፣አባይ ወይስ ቬጋስ፣ዝምታዬ ፣ላምባዲና የተሰኙ ፊልሞች እንደሚገኙበት ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
አምስተኛው የፊልም ፌስቲቫል በለንደን እና የመጀመሪያው ፊልም ፌስቲቫል በማልታ ሊካሄድ ነው ።በዓመት አንድ ጊዜ በለንደን ፊልም ፌስቲቫል ዝግጅት ይደረጋል። ዘንድሮም ለ5ኛ ጊዜ ይህው ሁነት ይቀጥላል።
ለመጀመሪያ ጊዜም በደሴታማዋ ሀገር ማልታ የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ይካሄዳል።
ከሰሞኑ ቀንም ማልታ 60ኛ የነፃነት በዓሏን እያከበርች ትገኛለች። ሐበሻ ቪው ዝግጅቶችን አሰናድቷል።
ይህንንም ዝግጅት አስመልክቶ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በሀያት ሪጀንሲ የሽኝት መርሐግብር ተካሂዷል።
"ሐበሻ ቪው" በውጪ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ከኢትዮጵያ ሥነጥበብ ፣ ኪነጥበብ ፣ክውን ጥበባት ጋር የሚያገናኙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በሐበሻቪው አዘጋጅነት በለንደን ለ5ተኛ ጊዜ እንዲሁም በማልታ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእይታ ይቀርባሉ ተብሏል።
ለእይታ ከሚቀርቡ ፊልሞች ውስጥ አፊኒ፣አባይ ወይስ ቬጋስ፣ዝምታዬ ፣ላምባዲና የተሰኙ ፊልሞች እንደሚገኙበት ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
አምስተኛው የፊልም ፌስቲቫል በለንደን እና የመጀመሪያው ፊልም ፌስቲቫል በማልታ ሊካሄድ ነው ።በዓመት አንድ ጊዜ በለንደን ፊልም ፌስቲቫል ዝግጅት ይደረጋል። ዘንድሮም ለ5ኛ ጊዜ ይህው ሁነት ይቀጥላል።
ለመጀመሪያ ጊዜም በደሴታማዋ ሀገር ማልታ የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ይካሄዳል።
ከሰሞኑ ቀንም ማልታ 60ኛ የነፃነት በዓሏን እያከበርች ትገኛለች። ሐበሻ ቪው ዝግጅቶችን አሰናድቷል።
ይህንንም ዝግጅት አስመልክቶ መስከረም 9 2017 ዓ.ም በሀያት ሪጀንሲ የሽኝት መርሐግብር ተካሂዷል።
"ሐበሻ ቪው" በውጪ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ከኢትዮጵያ ሥነጥበብ ፣ ኪነጥበብ ፣ክውን ጥበባት ጋር የሚያገናኙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አፍሪካን እናክብር" ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው
የ2024 "አፍሪካን እናክብር" ወይም "አፍሪካን እናክብር" ፌስቲቫል ከጥቅምት 27 እስከ ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚከበር አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
አፍሪካ ያላትን ባህል፣ ሥነ ጥበብ፣ ቅርስ፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም የቢዝነስ ሀብቶቿን ለዓለም ለማስተዋወቅ ፌስቲቫሉ ጠቀሜታ እንዳለው ነው የተገለፀው።
በተጨማሪም የአፍሪካ ሴቶች እና ወጣቶች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ እና እንዲገኙ ዕድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል።
የተለያዩ ሥራ ፈጣሪ ባለቤቶችም ስራዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ያስችላል ተብሏል።
ፈስቲቫሉ ከፈረንጆቹ 2021 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዚህኛው ዓመት ለማክበር በጋራ እንደሚሰራ ታውቋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኤምባሲዎች በአዘጋጅነት ተሳትፈውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የ2024 "አፍሪካን እናክብር" ወይም "አፍሪካን እናክብር" ፌስቲቫል ከጥቅምት 27 እስከ ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚከበር አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
አፍሪካ ያላትን ባህል፣ ሥነ ጥበብ፣ ቅርስ፣ ቴክኖሎጂ እንዲሁም የቢዝነስ ሀብቶቿን ለዓለም ለማስተዋወቅ ፌስቲቫሉ ጠቀሜታ እንዳለው ነው የተገለፀው።
በተጨማሪም የአፍሪካ ሴቶች እና ወጣቶች እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ እና እንዲገኙ ዕድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል።
የተለያዩ ሥራ ፈጣሪ ባለቤቶችም ስራዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ያስችላል ተብሏል።
ፈስቲቫሉ ከፈረንጆቹ 2021 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዚህኛው ዓመት ለማክበር በጋራ እንደሚሰራ ታውቋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኤምባሲዎች በአዘጋጅነት ተሳትፈውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አዳብና ፌስቲቫል" ለ3ኛ ጊዜ ሊካሄድ ነው
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "አዳብና ፌስቲቫል" ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስተኛ ጊዜ በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ በተለያዩ መርሐግብሮች እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ይህ ፌስቲቫል በዋናነትም በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ኬላ ከተማ መስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም በአደባባይ በትልቅ ፕሮግራም እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
በአዳብና ፌስቲቫል ከ30 እስከ 100 ሺህ ጎብኚዎችን የሚጠበቁ ሲሆን በ50 እናቶች የተዘጋጀ 100 ኪሎ ክትፎንና 100 ኪሎ የክትፎ ቅቤ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ለማስፈር ስራዎች እየተሰራ እንደሆነ ተነግሯል።
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማኅበር አዳብና የጉራጌ የልጃገረዶችና ወንድ ወጣቶች ባህላዊ ጨዋታ መተጫጫ ፌስቲቫል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) እንዲመዘገብ ለማድረግ እየሠራ ይገኛል።
የአዳብና ባህል የልጃገረዶችና ወጣት ወንዶች ጨዋታና መተጫጫ ስነስርዓት ሲሆን ባህሉ በጥናት በተረጋገጠ መረጃ መሰረት 800 ዓመታት በፊት በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ አካባቢ ለዘመናት ሲከበር እንደኖረ ማኀበሩ ገልጿል።
ይህ ድንቅ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ደብዝዞና ለጠፋ ታቃርቦ የነበረ ሲሆን የአዳብና በከስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከአካባቢው የመንግስት መዋቅሮች ጋር በመሆን ባደረገው ጥረት ባህሉ ጥንታዊ ወጉና ቱባ ባህሉ ይዞ በከፍተኛ ሁኔታ በማንሰራራት በአሁን ሰዓት በአካባቢው ላይ በፌስቲቫልነት እየተከበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "አዳብና ፌስቲቫል" ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ለሶስተኛ ጊዜ በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ በተለያዩ መርሐግብሮች እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ይህ ፌስቲቫል በዋናነትም በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ኬላ ከተማ መስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም በአደባባይ በትልቅ ፕሮግራም እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
በአዳብና ፌስቲቫል ከ30 እስከ 100 ሺህ ጎብኚዎችን የሚጠበቁ ሲሆን በ50 እናቶች የተዘጋጀ 100 ኪሎ ክትፎንና 100 ኪሎ የክትፎ ቅቤ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ለማስፈር ስራዎች እየተሰራ እንደሆነ ተነግሯል።
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማኅበር አዳብና የጉራጌ የልጃገረዶችና ወንድ ወጣቶች ባህላዊ ጨዋታ መተጫጫ ፌስቲቫል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) እንዲመዘገብ ለማድረግ እየሠራ ይገኛል።
የአዳብና ባህል የልጃገረዶችና ወጣት ወንዶች ጨዋታና መተጫጫ ስነስርዓት ሲሆን ባህሉ በጥናት በተረጋገጠ መረጃ መሰረት 800 ዓመታት በፊት በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ አካባቢ ለዘመናት ሲከበር እንደኖረ ማኀበሩ ገልጿል።
ይህ ድንቅ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ደብዝዞና ለጠፋ ታቃርቦ የነበረ ሲሆን የአዳብና በከስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከአካባቢው የመንግስት መዋቅሮች ጋር በመሆን ባደረገው ጥረት ባህሉ ጥንታዊ ወጉና ቱባ ባህሉ ይዞ በከፍተኛ ሁኔታ በማንሰራራት በአሁን ሰዓት በአካባቢው ላይ በፌስቲቫልነት እየተከበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የደራሲ እስከዳር ግርማይ "የፈረንጅ ሚስት" መጽሐፍ በእንግሊዝኛ ተተረጎመ
የደራሲ እስከዳር ግርማይ "የፈረንጅ ሚስት" የተሰኘ መጽሐፍ "WHITE MAN'S WIFE"በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ እንደተተርጎመ ተወዳጅ ሚዲያ ዘግቧል።
የእስከዳር ግርማይ አዲሱ የእንግሊዝኛ መጽሀፏ እውነተኛ ታሪኮችን ይተርካል። በተለይም በተለያየ የኑሮ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሴቶችንና የውጭ ሀገር ዜጋ ያገባ ኢትዮጵያዊ ወንድን ከምሳሌ እና ኹነቶች ጋር እያጣቀሰ የዕለት ተዕለት ህይወታቸውን ያስቃኛል።
መጽሀፉ መጀመሪያ የተጻፈው ''የፈረንጅ ሚስት'' በሚል ርዕስ እንደመሆኑ ተደራሽነቱ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ማዕከል አድርጎ የተነሳ ነበር። ሆኖም ኢትዮጵያውያን ሴቶች ዜጎቻቸውን ሲያገቡ የሚያጋጥማቸውን እይታም ድንበር ተሻጋሪ እንደመሆኑ " WHITE MAN'S WIFE" ወደሚል ተተርጉሟል።
የመጽሀፍ ወደ እንግሊዝኛ መተርጎም የኢትዮጵያ ስነጽሁፍን ለአለምአቀፍ አንባቢያን ተደራሽ በማድረግ ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያዋጣ ይታመናል ተብሏል።
የፈረንጅ ሚስትን ወደ እንግሊዝኛ መጽሀፉን የተረጎመችው ራሷ ደራሲዋ ስትሆን፣ እንግሊዛዊው የሥነጽሁፍ ባለሙያው ክርስትያን ሀሪፎርድ መጽሀፉን በአርታኢነት ሲሠራው፣ አሳታሚው ጆርጅ ኦፍ ሚድልተን "ይህ የኢትዮጵያን ሴቶች ታሪክ ብቻ ሳይሆን ስለሁላችን እና ስለምርጫዎቻችን ነው" በማለት አስተያየታቸውን መግቢያው ላይ አስፍረውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የደራሲ እስከዳር ግርማይ "የፈረንጅ ሚስት" የተሰኘ መጽሐፍ "WHITE MAN'S WIFE"በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ እንደተተርጎመ ተወዳጅ ሚዲያ ዘግቧል።
የእስከዳር ግርማይ አዲሱ የእንግሊዝኛ መጽሀፏ እውነተኛ ታሪኮችን ይተርካል። በተለይም በተለያየ የኑሮ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሴቶችንና የውጭ ሀገር ዜጋ ያገባ ኢትዮጵያዊ ወንድን ከምሳሌ እና ኹነቶች ጋር እያጣቀሰ የዕለት ተዕለት ህይወታቸውን ያስቃኛል።
መጽሀፉ መጀመሪያ የተጻፈው ''የፈረንጅ ሚስት'' በሚል ርዕስ እንደመሆኑ ተደራሽነቱ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ማዕከል አድርጎ የተነሳ ነበር። ሆኖም ኢትዮጵያውያን ሴቶች ዜጎቻቸውን ሲያገቡ የሚያጋጥማቸውን እይታም ድንበር ተሻጋሪ እንደመሆኑ " WHITE MAN'S WIFE" ወደሚል ተተርጉሟል።
የመጽሀፍ ወደ እንግሊዝኛ መተርጎም የኢትዮጵያ ስነጽሁፍን ለአለምአቀፍ አንባቢያን ተደራሽ በማድረግ ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያዋጣ ይታመናል ተብሏል።
የፈረንጅ ሚስትን ወደ እንግሊዝኛ መጽሀፉን የተረጎመችው ራሷ ደራሲዋ ስትሆን፣ እንግሊዛዊው የሥነጽሁፍ ባለሙያው ክርስትያን ሀሪፎርድ መጽሀፉን በአርታኢነት ሲሠራው፣ አሳታሚው ጆርጅ ኦፍ ሚድልተን "ይህ የኢትዮጵያን ሴቶች ታሪክ ብቻ ሳይሆን ስለሁላችን እና ስለምርጫዎቻችን ነው" በማለት አስተያየታቸውን መግቢያው ላይ አስፍረውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አንድ ቃል" የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ይለቀቃል
ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ ከወር በፊት ከለቀቀው "አንድ ቃል" የሙዚቃ አልበም ውስጥ ለአልበሙ መጠሪያ ለሆነው "አንድ ቃል" ለተሰኘው ሙዚቃ የተሰራው የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ረቡዕ መስከረም 15 2017 ዓ.ም በራሱ ዩቲዩብ ቻናል እንደሚለቀቅ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በማህበራዊ ትስስር ገፁም"ከአዲሱ አልበሜ አንድ ቃልን በቪዲዮ ረቡዕ ወደ እናንተ እንደማደርስ ስገልፅላችሁ በደስታ ነው" ብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ ከወር በፊት ከለቀቀው "አንድ ቃል" የሙዚቃ አልበም ውስጥ ለአልበሙ መጠሪያ ለሆነው "አንድ ቃል" ለተሰኘው ሙዚቃ የተሰራው የሙዚቃ ቪዲዮ ነገ ረቡዕ መስከረም 15 2017 ዓ.ም በራሱ ዩቲዩብ ቻናል እንደሚለቀቅ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በማህበራዊ ትስስር ገፁም"ከአዲሱ አልበሜ አንድ ቃልን በቪዲዮ ረቡዕ ወደ እናንተ እንደማደርስ ስገልፅላችሁ በደስታ ነው" ብሏል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ማይንቴክስ ኤክስፖ በሕዳር ወር ይካሄዳል!
ሶስተኛው ማይንቴክስ የማዕድን እና የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ከሕዳር 14 እስከ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።
በኤክስፖው በርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉና ለሁነቱ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አመላክቷል።
ኤክስፖው ሀገር በቀል ድርጅቶች ምርታቸውን ለዓለም እንዲያስተዋውቁና እንዲሸጡ ምቹ እድል እንደሚፈጥር የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።
የማዕድን ሚኒስቴር በማዕድን እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች በኤክስፖው ላይ በመሳተፍ ምርት እና አገልግሎታቸውን እንዲያስተዋውቁ ጥሪውን አቅርቧል።
©️መረጃው አራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሶስተኛው ማይንቴክስ የማዕድን እና የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ከሕዳር 14 እስከ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።
በኤክስፖው በርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉና ለሁነቱ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አመላክቷል።
ኤክስፖው ሀገር በቀል ድርጅቶች ምርታቸውን ለዓለም እንዲያስተዋውቁና እንዲሸጡ ምቹ እድል እንደሚፈጥር የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።
የማዕድን ሚኒስቴር በማዕድን እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች በኤክስፖው ላይ በመሳተፍ ምርት እና አገልግሎታቸውን እንዲያስተዋውቁ ጥሪውን አቅርቧል።
©️መረጃው አራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ነው።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የድምጻዊ አዲስ ሙላት "ዘማሌ" ሙዚቃ ተለቀቀ
የድምጻዊ አዲስ ሙላት "ዘማሌ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ትላንትና ረቡዕ መስከረም 15 2017 ዓ.ም በድምጻዊው የዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮች ደርሷል።
በ"ዘማሌ" የሙዚቃ ስራ ላይ በግጥም እንዳሻው አለማየሁ፣ በዜማ አዲስ ሙላት፣ በሙዚቃ ቅንብር ሚካኤል ኃይሉ(ሚኪ ጃኖ) ተሳትፈዋል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ አዲስ ሙላት "ዘማሌ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ትላንትና ረቡዕ መስከረም 15 2017 ዓ.ም በድምጻዊው የዩቲዩብ ቻናል በኩል ለአድማጮች ደርሷል።
በ"ዘማሌ" የሙዚቃ ስራ ላይ በግጥም እንዳሻው አለማየሁ፣ በዜማ አዲስ ሙላት፣ በሙዚቃ ቅንብር ሚካኤል ኃይሉ(ሚኪ ጃኖ) ተሳትፈዋል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሁለተኛ ዓመት የመታሰቢያ መርሐግብር ተከናወነ !
ከሁለት ዓመት በፊት መስከረም 17 2015 ዓ.ም በሞት የተለየን ተወዳጁ ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሁለተኛ ዓመት መርሐግብር ዛሬ መስከረም 16 2017 ዓ.ም ተካሄዷል።
የህልፈቱን ሁለተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግም ቤተሰቦቹ የሞያ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበትም የመታሰቢያ ዝግጅቱ በቅድስት ስላሴ ካቴደራል ተከናውናል።
ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ በህይወት እያለ የሰራቸው የተጠናቀቁና እና በጅምር ላይ የነበሩ የማዲንጎ ሙዚቃዎችም አስፈላጊው ማስተካከያ ተደርጎላቸው ለህዝብ እንደሚቀርቡም ከተነገረ አንድ ዓመት ተቆጥሯል።
ድምጻዊ ማዲንጎ ሶስት የሙዚቃ አልበሞችን አበርክቷል "ስያሜ አጣሁላት" ፣ "አይደረግም" እና "ስወድላት" የአልበሞቹ ርዕሶች ናቸው ።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ከሁለት ዓመት በፊት መስከረም 17 2015 ዓ.ም በሞት የተለየን ተወዳጁ ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሁለተኛ ዓመት መርሐግብር ዛሬ መስከረም 16 2017 ዓ.ም ተካሄዷል።
የህልፈቱን ሁለተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግም ቤተሰቦቹ የሞያ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበትም የመታሰቢያ ዝግጅቱ በቅድስት ስላሴ ካቴደራል ተከናውናል።
ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ በህይወት እያለ የሰራቸው የተጠናቀቁና እና በጅምር ላይ የነበሩ የማዲንጎ ሙዚቃዎችም አስፈላጊው ማስተካከያ ተደርጎላቸው ለህዝብ እንደሚቀርቡም ከተነገረ አንድ ዓመት ተቆጥሯል።
ድምጻዊ ማዲንጎ ሶስት የሙዚቃ አልበሞችን አበርክቷል "ስያሜ አጣሁላት" ፣ "አይደረግም" እና "ስወድላት" የአልበሞቹ ርዕሶች ናቸው ።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የሳሌሚያ "ዓለም ብሬ" ሙዚቃ ተለቀቀ
በወጣቷ ድምጻዊት ሳሌሚያ በተለየ የሙዚቃ ቅርጽ የተሰራው "ዓለም ብሬ" የተሰኘ የሙዚቃ ከሰሞኑ በድምጻዊት "SALEMIA" የዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቋል።
የሳሌሚያ "አለም ብሬ" ሙዚቃ በእንግሊዘኛና አማርኛ የሰራችው የሙዚቃ ስራ ነው።
ለሙዚቃው የሙዚቃ ቪዲዮ የተሰርለት ሲሆን ዮናታን መስፍን ዳይሬክት አድርጎታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በወጣቷ ድምጻዊት ሳሌሚያ በተለየ የሙዚቃ ቅርጽ የተሰራው "ዓለም ብሬ" የተሰኘ የሙዚቃ ከሰሞኑ በድምጻዊት "SALEMIA" የዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቋል።
የሳሌሚያ "አለም ብሬ" ሙዚቃ በእንግሊዘኛና አማርኛ የሰራችው የሙዚቃ ስራ ነው።
ለሙዚቃው የሙዚቃ ቪዲዮ የተሰርለት ሲሆን ዮናታን መስፍን ዳይሬክት አድርጎታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የፍቅር ካቴና" ዛሬ በልዩ ፕሮግራም ይቀርባል!
"የፍቅር ካቴና" የተሰኘ ተውኔት ዛሬ መስከረም 17 2017 ዓ.ም በልዩ ዝግጅት ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ውስጥ ይቀርባል።
በአርቲስት ወይንሸት አበጀ ፕሮዲዩስ የተደረገው ይህ "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ድርሰትና ዝግጅቱ የአለልኝ መኳንንት ፅጌ ነው።በተውኔቱ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ሚኪ ተስፋዬ ፣ ወይንሸት አበጀ ፣አሸናፊ ማህሌት በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"የፍቅር ካቴና" የተሰኘ ተውኔት ዛሬ መስከረም 17 2017 ዓ.ም በልዩ ዝግጅት ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ውስጥ ይቀርባል።
በአርቲስት ወይንሸት አበጀ ፕሮዲዩስ የተደረገው ይህ "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ድርሰትና ዝግጅቱ የአለልኝ መኳንንት ፅጌ ነው።በተውኔቱ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ሚኪ ተስፋዬ ፣ ወይንሸት አበጀ ፣አሸናፊ ማህሌት በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1