Event Addis Media – Telegram
Event Addis Media
9.62K subscribers
6.11K photos
13 videos
4 files
4.74K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌የኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ የ50ኛ ዓመት ክብረበዓል የማጠቃለያ ፕሮግራም ተካሄደ

ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ ላለፉት አምስት አስርት ዓመታት ያስመዘገባቸውን ልዩ ልዩ ስኬቶችን በመዘከር የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት ክብረበዓሉን ሲያከብር ቆይቷል። ዛሬ ጥቅምት 12 2017 ዓ.ም የክብረበዓሉ የማጠቃለያ መርሐግብሩን በሸራተን አዲስ ሆቴል አካሂዷል።

ክብረ በዓል ተከታታይነት ያላቸው በርካታ ሁነቶችን በማከናወን ሲከበር የቆየ ሲሆን ድርጅቱ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች፣ የድርጅቱ ደጋፊዎችና ሰራተኞች እያበረከቱ ያለውን አስተዋጽኦ እውቅና ለመስጠት የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል።

ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ የሐምሳኛ ዓመት ክብረበዓሉን  በኤግዚቢሽን ፣ በፓናል ውይይት፣ በገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች እና የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ሲያከናውን ቆይቷል፡፡

እነዚህም እንቅስቃሴዎች ስራውን የበለጠ ለማስተዋወቅ፣ ድጋፍ ለማሰባሰብ እንዲሁም ግለሰቦችና ድርጅቶች ለእያንዳንዱ ህጻን ተንከባካቢ ቤተሰብና ብሩህ ተስፋ የማጎናጸፍ አላማ ዙሪያ እንዲሰለፉ በሚያበረታታ መልኩ የተቀረጹ ናቸው ተብሏል።

ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ የአለም አቀፉ ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች ፌዴሬሽን ብሄራዊ አባል የሆነ በህጻናት ደህንነትና ልማት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ፖለቲካዊም ሃይማኖታዊም ያልሆነ የልማት ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱ ከተመሰረተበት ከ1974 ዓ.ም ጀምሮ በህጻናት፣ ቤተሰቦቻቸውና በማህበረሰብ ላይ አዎንታዊ ለውጦችን በማምጣት ላይ የሚገኝ የልማት አጋር ነው።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የደራሲ ሕይወት እምሻው አዲስ መጽሐፍ

የደራሲ ሕይወት እምሻው"ቡና ቁርስ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ለአንባቢያን ይቀርባል።

ደራሲ ሕይወት ስለ መጽሐፏ የሚከተለውን ብላለች "ትንሽ ልጅ ሆኜ።ወንዶች ከሁዋላ የሱሪ ኪሳቸው አጠፍ አድርገው ሽጉጥ፣ ሴቶች ደግሞ ትንሽዬ ቦርሳቸው ውስጥ በቀላሉ ክትት የሚያደርጔቸው 'ሚጢጢ' መጽሐፍት ሳይ ደስ ይለኝ ነበር።

በመጠን ቅልብጭ ማለታቸው፣ለአያያዝ መቅለላቸው፣በአንድ 'ቁጭ' ፉት ስትሏቸው ጭልጥ ማለታቸው፣ አብሶ ለጀማሪ አንባቢ ምቹ መሆናቸው ያስደስተኝ ነበር።እንደ ታደሰ ሊበን " መስከረም' ዓይነቶቹን ነው የምላችሁ። 

ቅዳሜ ጥቅምት 16 ገበያ ላይ የምትውለው"  የቡና ቁርስ" ጢኒጥዬ መጽሐፌ እንዲህ ያለች ናት።

ከእንግዲህ ሰው "ስንት መጽሐፍ አሳተምሽ ?" ብሎ ሲጠይቀኝ "አራት ተኩል" የምለው ለዚህ ነው።

ቅዳሜ የቡና ቁርስን የማቀርብላችሁ " በባዶው" እንዳይመስላችሁ!

ለእርቃን ሩብ ጉዳይ ላይ ነጻ ውይይት፣ ሙዚቃ፣ ቡና እና የቡና ቁርስ አዘጋጅቼ ነው።

ቦታው የከተማ ማዕከል ( እስጢፋኖስ ቤተ ክርስትያን)ፊት ለፊት) ፣ ሰዓቱ ደግሞ ከስምንት እስከ አስር ተኩል ነው።

የእኔን ዝግጅቶች ታድማችሁ የምታውቁ አሳምራችሁ እንደምታውቁት ደቂቃ ሳናረፍድ ጀምረን ባልነው ሰዓት እንጨርሳለን"።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ዳናሽ” ፊልም ለእይታ ሊበቃ ነው

በአብርሃም ታደሰ ተደርሶ ዳይሬክት የተደረገው "ዳናሽ" ፊልም ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም  በዓለም ሲኒማ ተመርቆ ለእይታ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።

በ"ዳናሽ" ፊልም ሔኖክ በሪሁን፣ ኤደን አይሹሽም፣ጌታቸው ስለሺ፣ ምስክር ተስፋዬ እና ሌሎችም በትወና ተሳትፈዋል።

በኢነርጂ ፊልም ፕሮዳክሽን እና በቆንጆ ፒክቸርስ ተዘጋጅቶ በየሚ ፒክቸርስ አማካኝነት ለሕዝብ እንዲቀርብ የተሰናዳው ፊልም በዓይነቱ ለየት ያለ እና ጠንካራ ሃሳብ ይዞ የመጣ መሆኑን የፊልሙ አዘጋጅ አብርሃል ታደሰ ገልጸዋል፡፡

አጠቃላይ 3 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገበት እና 1 ሰዓት ከ46 ደቂቃ የሚፈጅ ርዝማኔ ያለው ፊልሙ ለኢትዮጵያ ፊልም ተመልካቾች የሚመጥን ሃሳብ በማንሳት የሚሞግት፣ ብሎም ለመልካም እሴቶቻችን ዘብ እንድንቆም የሚያበረታታ ስለመሆኑ አዘጋጁ አብርሃል ታደሰ አስታውቀዋል፡፡

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ዌብሳይት የመስራት ችሎት ላላቸው ዳጎስ ያለ ብር የሚያሸልም ውድድር ሊካሄድ ነው።

የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማቅረብ በአጭር ጊዜ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ በኢትዮጵያ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ እየሆነ የመጣው አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አ.ማ ከብልህ ማርኬቲንግ ጋር በመሆን ለረጅም ጊዜ ሲሰራበት የቆየውን የቴክኖሎጂ ውጤት ከ500 በላይ አበልፃጊዎችን በማሳተፍ ዘርፉን ለማበርታታት ፕሮጀክት ቀርጾ መንቀሳቀስ መጀመሩን ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ በሚገኘዉ ዋና መስሪያቤቱ ይፋ አደርጓል።

በዚህ የመክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ ዌብሳይት የመስራት ችሎት ላላቸው ዳጎስ ያለ ብር የሚያሸልም ውድድር ማዘጋጀቱንም ተቋሙ አስታውቋል።

የአሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አ.ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳንኤል በቀለ "ይህንን የፈጠራ ውድድር በዘጠና ቀን ዘመቻ ወደስራ ስናስገባ የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን የቴክሎጂ እድገት ካለበት ደረጃ በአጭር ጊዜ የከፍታ ማማ ላይ ለማድረስ አልመን ነው የምንሰራው " ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም የዌብ ዘርፎች ኢኮሜርስ፣ ቱሪዝም፣ ሆስፒታሊቲ፣ የሄልዝ ኬር፣ የተማሪዎች ሰርቪስ፣የማህበረሰባዊ ትስስር ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ማወቅ ተችሏል።

ይህም ፕሮጀክት ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር አንፃር፤ ለአገር ዉስጥ የምጣኔ ሀብት እድገትና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር እንደሚችል እና አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች በማካተት ለዌብ ዲዛይኑ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያላቸዉ ተብሌኖችና ዲዛይኖች እንዲፈጠሩ ለማየት እንደሚያስችል ተገልጿል።

ፎቶ: ተክሌ ማርኮን

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የገጣሚ ዮሐንስ ሞላ "በከንፈርሽ በራ'ፍ" መጽሐፍ ረቡዕ ይመረቃል።

የገጣሚ ዮሐንስ ሞላ "በከንፈርሽ በራ'ፍ" የተሰኘ  ርዕስ የተሰጠው አዲስ  የግጥም መጽሐፍ የፊታችን ረቡዕ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ከ11:00 ጀምሮ  አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመረቃል።

ገጣሚ ዮሐንስ ሞላ ከዚህ ቀደም "የብርሃን ልክፍት" እና "የብርሃን ሰበዞች" የተሰኙ መጻሕፍት አንባቢያን ማድረሱ አይዘነጋም።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት ናርዶስ አዳነ የሎዛ የሥነምግብ ማማከር ህክምና ተቋም ብራንድ አንባሳደር በመሆን ተሾመች።

አርቲስት ናርዶስ አዳነ የሎዛ የሥነምግብ ማማከር ህክምና ተቋም ብራንድ አንባሳደር በመሆን ለሁለት ዓመታት ስምምነት ፈፅማለች።

የጋራ ስምምነቱ ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም በኤልሶል ሆቴል ውስጥ ተካሄዷል።

ሎዛ የስነ ምግብ ማማከር ህክምና ተቋም ተላላፊ ያልሆኑ የጤና ችግሮችን በምግብ በማከም እንደ ስኳር እና ደም ብዛት ላሉ በሽታዎች ለተጠቁ ታካሚዎች ዘለቄታዊ መፍትሄ በመስጠት እያገለገለ ያለ ተቋም እንደሆነ በፊርማ ሥነሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የሕይወት ታሪክ" የተሰኘ አዲስ ተውኔት ለመድረክ የሚበቃበት ቀን ይፋ ሆነ።

ድርሰቱ እና ዝግጅቱ የነብዩ ባዬ እና የቢንያም ወርቁ የሆነው "የሕይወት ታሪክ" አዲስ ተውኔት ከጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአንጋፋው ብሔራዊ ቴአትር መቅረብ እንደሚጀምር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ይህ ተውኔት ከዚህ ቀደም በሸገር ራዲዮ በሬድዮ ድራማ መልክ ቀረቡ የነበረ ሲሆን አሁን በመድረክ ተውኔት ቅርጽ ተሰርቷል ተብሏል።

በ"ሕይወት ታሪክ" በተውኔት ላይ ቢንያም ወርቁ እና ፀደይ ፋንታሁን  ለሁለት ይተውናሉ።

ተውኔቱ በነባ ጥበባት እና ኮምኒኬሽን የቀረበ ነው።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ነገረ መጻሕፍት" ቅዳሜ ይካሄዳል!

በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት በዓመቱ የመጀመሪያው መሰናዶ የቦታ ለወጥ አድርጎ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 16 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

በዚህ በዓመቱ የመጀመሪያ መሰናዶ ላይ ደራሲ ተስፋዬ ማሞ እና ደራሲ ይታገሱ ጌትነት ተጋባዥ እንግዶች ሲሆኑ ለውይይት የሚቀርቡ መጻሕፍት ደግሞ "ከማዕበል ማዶ" እና "መንግስቱ ኃ/ማርያም:የስደተኛው መሪ ትረካዎች" ናቸው።የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አውደ ፋጎስ" የውይይት መድረክ እሁድ ይካሄዳል

48ኛው ዙር አውደ ፋጎስ የውይይት መድረክ እሁድ ይካሄዳል። በዚህኛው ዙር በርናባስ ሽፈራው "የማርክሳዊነት የገደል ማሚቶች " በሚል ርዕስ መነሻ ሀሳብ ያቀርባል።ይህም ውይይት እሁድ ጥቅምት 17 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አግልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የወር ወንበር" ውይይት ቅዳሜ ይካሄዳል!

"የወር ወንበር" ውይይት የፊታችን ቅዳሜ ይካሄዳል።በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በየወሩ የሚዘጋጅው "የወር ወንበር" መሰናዶ በዚህ ወር "ሳይንስ እና መኸዘብ" በሚል ርዕስ የፊታችን  ቅዳሜ ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት (ወመዘክር) ግቢ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ አዳራሽ ውስጥ ውይይት ይካሄዳል።በዚህ ውይይት ላይ ኤምሬትስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ የውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀርባሉ ተብሏል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የቅርብ ሩቅ" ተውኔት ዛሬ ለእይታ ይበቃል

በእሸቱ ዱብ ተደርሶ በተስፋዬ ገብረማርያም የተዘጋጀው "የቅርብ ሩቅ" ተውኔት ዛሬ ጥቅምት 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ለመድረክ ይበቃል።በተውኔቱ ላይ ሉሌ አሻጋሪ፣ሔኖክ በሪሁን፣ቅድስት ብሩክ፣ናትናኤል መኮንን፣ብሩክታዊት እሸቱና ሌሎችም በትወና ተሳትፈውበታል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌 "ሦስቱ አይጦች" ተውኔት ሊመረቅ ነው

በአራዳ ፊሊከስ ፕሮዲዩስ ተደርጎ በኢትዮጲያ ብሔራዊ ቲያትር በመታየት ላይ ያለውና በአርቲስት ኤልያስ ተስፋዬ ተፅፎ በአርቲስት ካሌብ ዋለልኝ እና በአርቲስት ህብረ ቀለመወርቅ የተዘጋጀው "ሦስቱ አይጦች” ተውኔት ሰኞ ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የኮርፖሬት ተቋማት ሃላፊዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት አንደኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ በታላቅ ድምቀት በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል።

በተውኔቱ ላይ ካሌብ ዋለልኝ ፣ህሊና ሲሳይ ፣ህብረ ቀለመወርቅ ፤ እንዳለ ብርሃኑ፣ ታሪክ አስተርአየ፣አስመላሽ ታምርአየሁ፣ ቸርነት ፍቃዱ ፣መርዕድ ተስፋዬ፣ ሔኖክ ዘርዓብሩክ በተዋናይነት ተሳትፈውበታል።

"ሦስቱ አይጦች" ተውኔት ከ20 ዓመታት በፊት "የተከፈለ ልብ" በሚል ርዕስ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተመድርኮ ነበር።

የተውኔቱ የምርቃ ሥነሥርዓትም የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ ይካሄዳል። እንዳትቀሩ ተብላችኋል።

ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ አሸንፏል

ሁለተኛውን የኢጋድ የ2024 የሚዲያ አዋርድ ኢትዮጵያዊው ወጣት ጋዜጠኛ ምስክር አወል አሸናፊ ሆኗል።

ጋዜጠኛ ምስክር "Narratives of Hope: Inspiring Peaceful, Secure, and Inclusive Future." በሚል ሃሳብ ላይ ተወዳድሮ ነው ከሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ጋዜጠኞች ቀዳሚ መሆንና ማሸነፍ የቻለው።
ሽልማቱንም በኬንያ እየተካሄደ ባለው የኢጋድ የሚዲያ አዋርድ ስነ ስርዓት ላይ ተቀብሏል።

ጋዜጠኛ ምስክር ቀደም ሲል በሸገር ራዲዮ የሰራ ሲሆን አሁን ደግሞ በኢቢሲ የብሄራዊ ሬዲዮ ጣቢያው ባልደረባ ነው።

መረጃው: የ https://news.1rj.ru/str/AhunawiMereja ነው።

ለትኩስ መረጃዎች "አሁናዊ" ቴሌግራም ይቀላቀሉ።
Channel name was changed to «Event Addis Media»