የጋዜጠኛ የኑስ መሐመድ መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል
የጋዜጠኛ የኑስ መሐመድ "የነፍስያ ድምጾች" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የግጥም መጽሐፍ ዛሬ ሕዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:30 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመረቃል።
በዚህ የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ አንጋፋ እና ወጣት የሥነጽሑፍ ባለሞያዎች ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የጋዜጠኛ የኑስ መሐመድ "የነፍስያ ድምጾች" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የግጥም መጽሐፍ ዛሬ ሕዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:30 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመረቃል።
በዚህ የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ አንጋፋ እና ወጣት የሥነጽሑፍ ባለሞያዎች ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የፍቅር ካቴና" ተውኔት በልዩ ዝግጅት ነገ ይቀርባል
ድርሰት እና ዝግጅቱ የአለልኝ መኳንት ፅጌ የሆነው "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ነገ እሁድ ህዳር 15 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሠዓት ጀምሮ በልዩ ዝግጅት በዓለም ሲኒማ ይታያል።
በተውኔቱ ላይ ድርብወርቅ ሰይፉ፣ ሚኪ ተስፋዬ ፣ወይንሸት አበጀ፣ አሸናፊ ማህሌት ይተውኑበታል።
የቴአትር ወዳጆች ዓለም ሲኒማ መጥታችሁ የእረፍት ቀናችሁን በፍቅር ካቴና ቲያትር እየተዝናናችሁ ጥሩ ጊዜን እንድታሳልፉ ተጋብዛችኋል ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ድርሰት እና ዝግጅቱ የአለልኝ መኳንት ፅጌ የሆነው "የፍቅር ካቴና" ተውኔት ነገ እሁድ ህዳር 15 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሠዓት ጀምሮ በልዩ ዝግጅት በዓለም ሲኒማ ይታያል።
በተውኔቱ ላይ ድርብወርቅ ሰይፉ፣ ሚኪ ተስፋዬ ፣ወይንሸት አበጀ፣ አሸናፊ ማህሌት ይተውኑበታል።
የቴአትር ወዳጆች ዓለም ሲኒማ መጥታችሁ የእረፍት ቀናችሁን በፍቅር ካቴና ቲያትር እየተዝናናችሁ ጥሩ ጊዜን እንድታሳልፉ ተጋብዛችኋል ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በአሜሪካ ኤምባሲ
ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል።
የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ፕሮግራሙ በተወዳጅ የፍቅር ዘፈኖቹ የሚታወቀውን ስመ-ጥር እና በአዲሱ የሙዚቃ አልበሙ ደግሞ ተወዳጅነትን ያተረፈውን ድምፃዊ የግጥም እና ዜማ ደራሲ አርቲስት ሚካኤል በላይነህን ጋብዟል::
የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች "ከሚኪ ጋራ በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ ማክሰኞ ሕዳር 17 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ገለጸዋል።
በዕለቱ ከአርቲስቱ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::
ፕሪስቴጅ አዲስ ከሚካኤል በላይነህ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ነገ ማክሰኞ ሕዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።
በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:https://bit.ly/SatchmoCenterMembership
መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል።
የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ፕሮግራሙ በተወዳጅ የፍቅር ዘፈኖቹ የሚታወቀውን ስመ-ጥር እና በአዲሱ የሙዚቃ አልበሙ ደግሞ ተወዳጅነትን ያተረፈውን ድምፃዊ የግጥም እና ዜማ ደራሲ አርቲስት ሚካኤል በላይነህን ጋብዟል::
የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች "ከሚኪ ጋራ በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ ማክሰኞ ሕዳር 17 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ገለጸዋል።
በዕለቱ ከአርቲስቱ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::
ፕሪስቴጅ አዲስ ከሚካኤል በላይነህ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ነገ ማክሰኞ ሕዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።
በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:https://bit.ly/SatchmoCenterMembership
መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ይህ "Event Addis Media" ነው 💥
የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችን ይወዳጁ+ያጋሩ!
ቴሌግራም:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ቲክቶክ:https://www.tiktok.com/@eventaddis1?_t=8rgsgcVSeW7&_r=1
Website:https://eventaddis.com/
Facebook:https://www.facebook.com/profile.php?id=100083170462851
አስተያየትዎን ይጻፉልን: @Tmanaye
የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችን ይወዳጁ+ያጋሩ!
ቴሌግራም:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ቲክቶክ:https://www.tiktok.com/@eventaddis1?_t=8rgsgcVSeW7&_r=1
Website:https://eventaddis.com/
Facebook:https://www.facebook.com/profile.php?id=100083170462851
አስተያየትዎን ይጻፉልን: @Tmanaye
📌"መንግሥቱ ኃይለማርያም:የስደተኛው መሪ ትረካዎች"መጽሐፍ ሁለተኛ እትም ለንባብ በቃ
በደራሲ ይታገሱ ጌትነት የተዘጋጀው "መንግሥቱ ኃይለማርያም:የስደተኛው መሪ ትረካዎች"መጽሐፍ ሁለተኛ ህትመት ለንባብ በቅቷል።
የዚህ መጽሐፍ የመጀመሪያው እትም በሀገር ውስጥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሽጦ ከገበያ ጠፍቶ ነበር። ዳግም ህትመቱ ከዛሬ አንስቶ በዋልያ አሳታሚ አማካኝነት በሁሉም የመጽሐፍት መደብር ውስጥ ያገኙታል።
በውጭ ሀገር መጽሐፉን ለማግኘት አማዞን ላይ በ https://a.co/d/6V7LBpt መጠቀም ይችላሉ።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲ ይታገሱ ጌትነት የተዘጋጀው "መንግሥቱ ኃይለማርያም:የስደተኛው መሪ ትረካዎች"መጽሐፍ ሁለተኛ ህትመት ለንባብ በቅቷል።
የዚህ መጽሐፍ የመጀመሪያው እትም በሀገር ውስጥ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሽጦ ከገበያ ጠፍቶ ነበር። ዳግም ህትመቱ ከዛሬ አንስቶ በዋልያ አሳታሚ አማካኝነት በሁሉም የመጽሐፍት መደብር ውስጥ ያገኙታል።
በውጭ ሀገር መጽሐፉን ለማግኘት አማዞን ላይ በ https://a.co/d/6V7LBpt መጠቀም ይችላሉ።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ጠይም ጤዛ" መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል
የጋዜጠኛና ገጣሚ ተሾመ ብርሃኑ "ጠይም ጤዛ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የግጥም መጽሐፍ ዛሬ ሕዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ይመረቃል ተብሏል።በዕለቱም አንጋፋው እና ወጣት የሥነጽሑፍ ባለሞያዎች ሀሳቦቻቸውን እንደሚያገሩ ተገልጿል።
"ጠይም ጤዛ" መጽሐፍ ሐምሳ የግጥም ስራዎችን በውስጥ የያዘ ሲሆን 94 ገፆች ተቀንብቦ በ300 የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።ጋዜጠኛና ገጣሚ ተሾመ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በ2011 ዓ.ም በሆሄ የሥነጽሑፍ ሽልማት ላይ የዓመቱ ምርጥ የግጥም መደብል አሸናፊ የሆነበት "ኮብላይ ዘመን" መጽሐፍን ለአንባቢያን አድርሷል።
በተጨማሪም በጀርመን ባህል ማዕከል (ጎተ)አወዳዳሪነት ከተለያዩ ደራሲዎች ጋር በጋራ በተሰናዳው "ሠላሳዎቹ" የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሐፍ ውስጥም ስራው ታትሞለታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የጋዜጠኛና ገጣሚ ተሾመ ብርሃኑ "ጠይም ጤዛ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የግጥም መጽሐፍ ዛሬ ሕዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ይመረቃል ተብሏል።በዕለቱም አንጋፋው እና ወጣት የሥነጽሑፍ ባለሞያዎች ሀሳቦቻቸውን እንደሚያገሩ ተገልጿል።
"ጠይም ጤዛ" መጽሐፍ ሐምሳ የግጥም ስራዎችን በውስጥ የያዘ ሲሆን 94 ገፆች ተቀንብቦ በ300 የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።ጋዜጠኛና ገጣሚ ተሾመ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በ2011 ዓ.ም በሆሄ የሥነጽሑፍ ሽልማት ላይ የዓመቱ ምርጥ የግጥም መደብል አሸናፊ የሆነበት "ኮብላይ ዘመን" መጽሐፍን ለአንባቢያን አድርሷል።
በተጨማሪም በጀርመን ባህል ማዕከል (ጎተ)አወዳዳሪነት ከተለያዩ ደራሲዎች ጋር በጋራ በተሰናዳው "ሠላሳዎቹ" የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሐፍ ውስጥም ስራው ታትሞለታል።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አሚን አሚንዬ" መጽሐፍ ቅዳሜ ይመረቃል
የገጣሚ መሐመድ እድሪስ ካሣ"አሚን አሚንዬ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ የግጥም መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ሕዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ይካሄዳል።
በዚህ የመጽሐፍ ምርቃት ላይ ሀሴን ከድር ፣ቴዎድሮስ ካሣ፣ረድኤት አሰፋ፣እሱባለው አበራ፣ሚካኤል ምናሴ፣መስፍን ወንድወሰን ፣ዮሴፍ ይድነቃቸው ፣ያስሚን ሰፋ፣ፈይሰል አሚን፣ሐብታሙ ሀደራ የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
ሙኒራ አብዱራህማን መድረኩን ትመራዋለች።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የገጣሚ መሐመድ እድሪስ ካሣ"አሚን አሚንዬ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ የግጥም መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ሕዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ይካሄዳል።
በዚህ የመጽሐፍ ምርቃት ላይ ሀሴን ከድር ፣ቴዎድሮስ ካሣ፣ረድኤት አሰፋ፣እሱባለው አበራ፣ሚካኤል ምናሴ፣መስፍን ወንድወሰን ፣ዮሴፍ ይድነቃቸው ፣ያስሚን ሰፋ፣ፈይሰል አሚን፣ሐብታሙ ሀደራ የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
ሙኒራ አብዱራህማን መድረኩን ትመራዋለች።
ለተጨማሪው:https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"መሀል ከተማ" ዛሬ ለእይታ ይበቃል
በኤርሚያስ ታደሰ የተዘጋጀውና "መሀል ከተማ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የአማርኛ ፊልም ዛሬ ሕዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ ሲኒማ ቤቶች ለእይታ ይበቃል።
ይህ ፊልም ሕዳር 20፣ 21፣ 22 በይፋ ይመረቃልም ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በኤርሚያስ ታደሰ የተዘጋጀውና "መሀል ከተማ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የአማርኛ ፊልም ዛሬ ሕዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ ሲኒማ ቤቶች ለእይታ ይበቃል።
ይህ ፊልም ሕዳር 20፣ 21፣ 22 በይፋ ይመረቃልም ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ደራሲና ተዋናይ ደሞዝ ጎሽሜ የክብር እንግዳ የሆነበት ስብሐቲዝም የሀሳብ ውይይት ዝግጅት እሁድ ይካሄዳል።
ደራሲና ተዋናይ ደሞዝ ጎሽሜ የክብር እንግዳ የሆነበት ስብሐቲዝም 79ተኛ መድረክ "ኢትዮጵያዊ ጥበብ" በሚል የሀሳብ ውይይት ይካሄዳል።
ውይይቱ እሁድ ሕዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይከናወናል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ደራሲና ተዋናይ ደሞዝ ጎሽሜ የክብር እንግዳ የሆነበት ስብሐቲዝም 79ተኛ መድረክ "ኢትዮጵያዊ ጥበብ" በሚል የሀሳብ ውይይት ይካሄዳል።
ውይይቱ እሁድ ሕዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይከናወናል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ የፍጻሜ ውድድር
የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ የፍጻሜ ውድድር ነገ እሁድ ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ስድስት ኪሎ በሚገኘው ያሬድ የሙዚቃ ት/ቤት ፕ/ር አሸናፊ ከበደ የሙዚቃ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል።
የቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ አይዶል ዝነኞች ከአዳዲሶቹ ምርጦች ጋር እሁድ በዓመቱ ኮከብ ልዩ ፕሮግራም ላይ ይገናኛሉ ተብሏል።
ዳግማዊት ፀሀዬ፣ ዳዊት አለማየሁ፣ ተመስገን ታፈሰ፣ አዝመራው ሙሉሠውና ሌሎች የአይዶል ፈርጦች አዳዲሶቹን ኮከቦች ያገኟቸዋል።
እሁድ ህዳር 22 በሚካሄደው የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ ኘሮግራም ላይ አርቲስቶቹ ልዩ ቆይታ ይኖራቸዋል።
1 ሚሊየን ብር በሚያሸልመው የዓመቱ የፍፃሜ ውድድር በሙዚቃ ድግስ ደምቆ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሁሉም ቻናሎች በመላው ዓለም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በቀጥታ ይተላለፋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ የፍጻሜ ውድድር ነገ እሁድ ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ስድስት ኪሎ በሚገኘው ያሬድ የሙዚቃ ት/ቤት ፕ/ር አሸናፊ ከበደ የሙዚቃ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል።
የቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ አይዶል ዝነኞች ከአዳዲሶቹ ምርጦች ጋር እሁድ በዓመቱ ኮከብ ልዩ ፕሮግራም ላይ ይገናኛሉ ተብሏል።
ዳግማዊት ፀሀዬ፣ ዳዊት አለማየሁ፣ ተመስገን ታፈሰ፣ አዝመራው ሙሉሠውና ሌሎች የአይዶል ፈርጦች አዳዲሶቹን ኮከቦች ያገኟቸዋል።
እሁድ ህዳር 22 በሚካሄደው የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ ኘሮግራም ላይ አርቲስቶቹ ልዩ ቆይታ ይኖራቸዋል።
1 ሚሊየን ብር በሚያሸልመው የዓመቱ የፍፃሜ ውድድር በሙዚቃ ድግስ ደምቆ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሁሉም ቻናሎች በመላው ዓለም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በቀጥታ ይተላለፋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የ"ቅኔ ሰርከስ"የሰርከስ ድግስ ዛሬ ይካሄዳል
የቅኔ ሰርከስ የሰርከስ ደግስ ልዩ ዝግጅት ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ ጎሮ አካባቢ በሚገኘው በቅኔ ሰርከስ ማዕከል ይካሄዳል።
ይህ የሰርከስ ዝግጅት መግቢያው ለአዋቂ 400 ብር ሲሆን ለህፃናት 200 ብር እንደሆነም ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የቅኔ ሰርከስ የሰርከስ ደግስ ልዩ ዝግጅት ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ ጎሮ አካባቢ በሚገኘው በቅኔ ሰርከስ ማዕከል ይካሄዳል።
ይህ የሰርከስ ዝግጅት መግቢያው ለአዋቂ 400 ብር ሲሆን ለህፃናት 200 ብር እንደሆነም ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ የፍፃሜ ውድድር አሸናፊ ዮሐንስ አምደወርቅ ሆኗል
የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ የፍፃሜ ውድድር አሸናፊ ዮሐንስ አምደወርቅ በመሆን ልዩ ዋንጫ፣ አንድ ሚሊዮን ብር እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ነፃ የትምህርት እድል አሸናፊ ሆኗል።
2ኛ ሚኪያስ ጌቱ
3ኛ ማቲያስ አንበርብር
4ኛ ብዙአየሁ ሰለሞን
ውጤቱ የ2 ዙር የዳኞች ውጤት እና ተመልካቾች በ8600 በፅሁፍ መልእክት የሰጡት ድምፅ ተደምሮ ነው አሸናፊው የተለየው ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ አይዶል የዓመቱ ኮከብ የፍፃሜ ውድድር አሸናፊ ዮሐንስ አምደወርቅ በመሆን ልዩ ዋንጫ፣ አንድ ሚሊዮን ብር እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ነፃ የትምህርት እድል አሸናፊ ሆኗል።
2ኛ ሚኪያስ ጌቱ
3ኛ ማቲያስ አንበርብር
4ኛ ብዙአየሁ ሰለሞን
ውጤቱ የ2 ዙር የዳኞች ውጤት እና ተመልካቾች በ8600 በፅሁፍ መልእክት የሰጡት ድምፅ ተደምሮ ነው አሸናፊው የተለየው ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"የዱር አበባ" መጽሐፍ ቅዳሜ ይመረቃል
የገጣሚ ቴዎድሮስ ካሣ "የዱር አበባ" የተሰኘ አዲስ የግጥም መፅሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ሕዳር 28 ከቀኑ 11:00 ጀምሮ መገናኛ(24) በሚገኘው ሞሰብ የሙዚቃ ማዕከል ቅጥር ግቢ ውስጥ በድምቀት ይመረቃል ።
በዕለቱም በዝግጅቱ ላይ ረድኤት ተረፈ፣ግሩም ተበጀ፣አልዳ ግዛቸው ፣ሰለሃዲን አሊ፣ምግባር ሲራጅ፣ፍቃዱ አየለኝ፣ሰይፉ ወርቁ ፣መዘክር ግርማ፣አንተነህ አክሊሉ፣አንዱ ጌታቸው፣እልፋገድ እምሻው ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የገጣሚ ቴዎድሮስ ካሣ "የዱር አበባ" የተሰኘ አዲስ የግጥም መፅሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ሕዳር 28 ከቀኑ 11:00 ጀምሮ መገናኛ(24) በሚገኘው ሞሰብ የሙዚቃ ማዕከል ቅጥር ግቢ ውስጥ በድምቀት ይመረቃል ።
በዕለቱም በዝግጅቱ ላይ ረድኤት ተረፈ፣ግሩም ተበጀ፣አልዳ ግዛቸው ፣ሰለሃዲን አሊ፣ምግባር ሲራጅ፣ፍቃዱ አየለኝ፣ሰይፉ ወርቁ ፣መዘክር ግርማ፣አንተነህ አክሊሉ፣አንዱ ጌታቸው፣እልፋገድ እምሻው ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ተወዳጇ አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ በሲትኮም ድራማ እየመጣች ነው
በተለያዩ የቴሌቪዥንና ሬድዮ ድራማዎች እንዲሁም ፊልሞችና ተውኔቶች ላይ የምናውቃትና ከቴሌቪዥን ድራማዎች ጠፍታ የቆየችው አንጋፋው አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ በአዲስ የቴሌቪዥን ሲትኮም ድራማ እየመጣች እንደሆነ ተሰምቷል።
አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ የምትሳተፍበት ሲትኮም ድራማ "ዞሮ መውጫዬ"የተሰኘ ርዕስ ያለው እንደሆነም ተገልጿል።
ይህ ሲትኮም ድራማ አርቲስት ሙሉዓለም ታደስ እና አርቲስት ሚካኤል ታምሬ የተጣምሩበት እንደሆነም ተነግሯል። ድራማው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን እንደሚተላለፍም ተሰምቷል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በተለያዩ የቴሌቪዥንና ሬድዮ ድራማዎች እንዲሁም ፊልሞችና ተውኔቶች ላይ የምናውቃትና ከቴሌቪዥን ድራማዎች ጠፍታ የቆየችው አንጋፋው አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ በአዲስ የቴሌቪዥን ሲትኮም ድራማ እየመጣች እንደሆነ ተሰምቷል።
አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ የምትሳተፍበት ሲትኮም ድራማ "ዞሮ መውጫዬ"የተሰኘ ርዕስ ያለው እንደሆነም ተገልጿል።
ይህ ሲትኮም ድራማ አርቲስት ሙሉዓለም ታደስ እና አርቲስት ሚካኤል ታምሬ የተጣምሩበት እንደሆነም ተነግሯል። ድራማው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን እንደሚተላለፍም ተሰምቷል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ለሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ ህክምና የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ የአንድ ቀን አውደርዕይና ጨረታ ተዘጋጀ
የሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ "ነፃነት" የተሰኘና ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየ የሥዕል አውደርዕይና ጨረታ የፊታችን ህዳር 26 ቀን 2017 ይካሄዳል ተብሏል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ በቅርቡ በስዊድን ለሚያደርገው ህክምና ወጪን ለመሸፈን ነጻነት የተሰኘ የስዕል ኤግዚብሽን ማዘጋጀቱን አስታውቋል።
በመጪው ሃሙስ ሕዳር 26 ቀን በሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ በሚካሄደው የሥዕል አውደርዕይና የሥዕል ጨረታ ፕሮግራም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የጥበብ ሰዎችና ሠአሊዎች ይገኛሉ ተብሏል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ እንደገለፀው ከዚህ የሥዕል አውደርዕይና የሥዕል ጨረታ ፕሮግራም የሚገኘው ገቢ በቅርቡ ስዊድን ሀገር ለሚያደርገው የእግር ህክምና ወጪው 3 ሚልየን ብር እንደሆነ ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ "ነፃነት" የተሰኘና ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየ የሥዕል አውደርዕይና ጨረታ የፊታችን ህዳር 26 ቀን 2017 ይካሄዳል ተብሏል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ በቅርቡ በስዊድን ለሚያደርገው ህክምና ወጪን ለመሸፈን ነጻነት የተሰኘ የስዕል ኤግዚብሽን ማዘጋጀቱን አስታውቋል።
በመጪው ሃሙስ ሕዳር 26 ቀን በሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ በሚካሄደው የሥዕል አውደርዕይና የሥዕል ጨረታ ፕሮግራም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የጥበብ ሰዎችና ሠአሊዎች ይገኛሉ ተብሏል።
ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ እንደገለፀው ከዚህ የሥዕል አውደርዕይና የሥዕል ጨረታ ፕሮግራም የሚገኘው ገቢ በቅርቡ ስዊድን ሀገር ለሚያደርገው የእግር ህክምና ወጪው 3 ሚልየን ብር እንደሆነ ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ
ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በይፋ ስራ ጀመረ
በኢትዮጵያ ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ የተባለ ተቋም የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ ስራ እንደጀመረ በዛሬው ዕለት በይፋ አስታውቋል።
ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ቴክኖ ሰርቭ ከተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን አብረው እንደሚሰሩም ገለጸዋል።
በይፋዊ የስራ ማጀመሪያ መርሐግብሩ ላይ እንደተገለፀው ጥምረቱ የስንዴ ዱቄት አምራች እና የምግብ ዘይት ፋብሪካዎችን በቫይታሚን በማበልፀግ የተመጣጠነ ምግብ ዕጥረትን ለመቀነስ እንደሚሰራ ተግልጿል።
ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ባለፈው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለ140 ፋብሪካዎች የቴክኒካል ድጋፍ እና ለተጨማሪ 40 ፋብሪካዎች ደግሞ ስልጠና መስጠቱንም ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ አሁንም አሳሳቢ የሆኑ የአመጋገብ ችግሮች እያጋጠሟት መሆኑ ተነግሯል።
የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሠረት ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ሕፃናት 22 በመቶ ከክብደታቸው በታች መሆኑም ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በይፋ ስራ ጀመረ
በኢትዮጵያ ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ የተባለ ተቋም የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ ስራ እንደጀመረ በዛሬው ዕለት በይፋ አስታውቋል።
ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ቴክኖ ሰርቭ ከተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን አብረው እንደሚሰሩም ገለጸዋል።
በይፋዊ የስራ ማጀመሪያ መርሐግብሩ ላይ እንደተገለፀው ጥምረቱ የስንዴ ዱቄት አምራች እና የምግብ ዘይት ፋብሪካዎችን በቫይታሚን በማበልፀግ የተመጣጠነ ምግብ ዕጥረትን ለመቀነስ እንደሚሰራ ተግልጿል።
ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ባለፈው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለ140 ፋብሪካዎች የቴክኒካል ድጋፍ እና ለተጨማሪ 40 ፋብሪካዎች ደግሞ ስልጠና መስጠቱንም ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ አሁንም አሳሳቢ የሆኑ የአመጋገብ ችግሮች እያጋጠሟት መሆኑ ተነግሯል።
የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሠረት ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ሕፃናት 22 በመቶ ከክብደታቸው በታች መሆኑም ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የኹለተኛው ቤተ-መቅደስ ዳሰሳ" እሁድ ይመረቃል
"የኹለተኛው ቤተ-መቅደስ ዳሰሳ"የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን እሁድ ይመረቃል ተብሏል።
በቢንያም ታደሰ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከ9:30 ጀምሮ ሳር ቤት በሚገኘው በኢቫንጀሊካል ቴኦሎጂካል ኮሌጅ(ETC) ይመረቃል።በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ፕ/ር አባ ዳንኤል አሰፋን ጨምሮ የተለያዩ ኃይማኖት ተቋማት መሪዎች እንደሚገኙ ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"የኹለተኛው ቤተ-መቅደስ ዳሰሳ"የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን እሁድ ይመረቃል ተብሏል።
በቢንያም ታደሰ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከ9:30 ጀምሮ ሳር ቤት በሚገኘው በኢቫንጀሊካል ቴኦሎጂካል ኮሌጅ(ETC) ይመረቃል።በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ፕ/ር አባ ዳንኤል አሰፋን ጨምሮ የተለያዩ ኃይማኖት ተቋማት መሪዎች እንደሚገኙ ተገልጿል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የወር ወንበር" ውይይት ቅዳሜ ይካሄዳል!
"የወር ወንበር" ውይይት የፊታችን ቅዳሜ ይካሄዳል።በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በየወሩ የሚዘጋጅው "የወር ወንበር" መሰናዶ በዚህ ወር "ሐተታ ፀንሰ ሐሳባዊነት" በሚል ርዕስ የፊታችን ቅዳሜ ሕዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት (ወመዘክር) ግቢ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ አዳራሽ ውስጥ ውይይት ይካሄዳል።በዚህ ውይይት ላይ ሠዓሊና ቀራጲ በቀለ መኮንን የውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀርባሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"የወር ወንበር" ውይይት የፊታችን ቅዳሜ ይካሄዳል።በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በየወሩ የሚዘጋጅው "የወር ወንበር" መሰናዶ በዚህ ወር "ሐተታ ፀንሰ ሐሳባዊነት" በሚል ርዕስ የፊታችን ቅዳሜ ሕዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት (ወመዘክር) ግቢ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ አዳራሽ ውስጥ ውይይት ይካሄዳል።በዚህ ውይይት ላይ ሠዓሊና ቀራጲ በቀለ መኮንን የውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀርባሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ነገን አብረን እንሳል" አውደርዕይ ነገ ይከፈታል
በስልሳ ተጽዕኖ ፈጣሪ አካልጉዳተኛ ሠዓሊያን የተዘጋጀው የሥዕል አውደርዕይ ነገ አርብ ህዳር 27 ቀን 2017 ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት ውስጥ የክብር እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይከፈታል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በስልሳ ተጽዕኖ ፈጣሪ አካልጉዳተኛ ሠዓሊያን የተዘጋጀው የሥዕል አውደርዕይ ነገ አርብ ህዳር 27 ቀን 2017 ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት ውስጥ የክብር እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይከፈታል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ደራሲና ገጣሚ ደበበ ሰይፉ ያነባቸው የነበሩት 650 የግል መጻሕፍት ለአብርሆት ቤተመፅሀፍት ሊበረከቱ ነው፡፡
ህይወቱ ካለፈ 24 ዓመት ያለፈው የገጣሚ ፣ተመራማሪና የዩኒቨርሲቲ መምህር ደበበ ሰይፉ የግል መፅሀፎች ለአብርኾት ቤተመፅሀፍት ሊበረከቱ እንደሆነ ተሰማ።
በጥልቅ አንባቢነቱ የተመሰከረለት ደበበ ሰይፉ ከ650 በላይ የመጻህፍት ዐይነቶች ነበሩት ህዳር 27 2017 ዓ.ም መፅሀፎቹ ለአብርሆት ይበረከታሉ ተብሏል፡፡
ገጣሚ ደበበ ሰይፉ ከ 1960ዎቹ ጀምሮ በቴአትር እና በሥነ ፅሁፍ መምህርነት ያገለገለ ሲሆን የህይወት ታሪኩም በተወዳጅ ሚድያ በሲዲ በድምፅ ዶክመንተሪ ተሠርቶ መመረቁ ይታወቃል። "የብርሀን ፍቅር" እና "ለራስ የተጻፈ ደብዳቤ" የተሰኙ የግጥም መድበሎንችም ያስነበበን የኪነ ጥበብ ሰው ነበር።
ይህንኑ የመፅሀፍ ርክክብ ምክንያት በማድረግ የደበበ ሰይፉ ቤተሰቦች ከተወዳጅ ሚድያ ጋር የጀመሩት የማህበራዊ ሚድያ የንባብ ዘመቻ እንደሚከናወን ለማወቅ ተችሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ህይወቱ ካለፈ 24 ዓመት ያለፈው የገጣሚ ፣ተመራማሪና የዩኒቨርሲቲ መምህር ደበበ ሰይፉ የግል መፅሀፎች ለአብርኾት ቤተመፅሀፍት ሊበረከቱ እንደሆነ ተሰማ።
በጥልቅ አንባቢነቱ የተመሰከረለት ደበበ ሰይፉ ከ650 በላይ የመጻህፍት ዐይነቶች ነበሩት ህዳር 27 2017 ዓ.ም መፅሀፎቹ ለአብርሆት ይበረከታሉ ተብሏል፡፡
ገጣሚ ደበበ ሰይፉ ከ 1960ዎቹ ጀምሮ በቴአትር እና በሥነ ፅሁፍ መምህርነት ያገለገለ ሲሆን የህይወት ታሪኩም በተወዳጅ ሚድያ በሲዲ በድምፅ ዶክመንተሪ ተሠርቶ መመረቁ ይታወቃል። "የብርሀን ፍቅር" እና "ለራስ የተጻፈ ደብዳቤ" የተሰኙ የግጥም መድበሎንችም ያስነበበን የኪነ ጥበብ ሰው ነበር።
ይህንኑ የመፅሀፍ ርክክብ ምክንያት በማድረግ የደበበ ሰይፉ ቤተሰቦች ከተወዳጅ ሚድያ ጋር የጀመሩት የማህበራዊ ሚድያ የንባብ ዘመቻ እንደሚከናወን ለማወቅ ተችሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌አርቲስት ማስተዋል ወንደሰን የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመርጣለች
የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ የፕሬዝዳንትና ስራ አስፈፃሚ ምርጫ አካሂዷል።
ኢ/ር ሃይለእየሱስ ፍስሀ የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ሆነው ሲመረጡ፤ አርቲስት ማስተዋል ወንደሰን የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመርጣለች።
ፌዴሬሽን አመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በጊዮን ሆቴል ሲያካሂድ ለቀጣይ አራት አመታት የሚመሩትን ፕሬዝዳንትና ስራ አስፈፃሚዎችንም መርጧል።
አንጋፋዋ አርቲስት ሀረገወይን አሰፋ ፣አቶ ሲሳይ ዳኜ ፣ደ/ር ወገኔ ዋልተንጉስ ፣አቶ ኢሳያስ ታፈሰ ፣አቶ ሸሀመለ በቀለ፣አቶ በለጠ ወልዴ፣ ወ/ሮ አሰፋሽን ስራ አስፈፃሚ ውስጥ ተካተዋል።
ፌዴሬሽኑ አለብኝ የሚለውን የገንዘብ እጥረት ለመቅረፍ አርቲስቶችን ወደ ስራ አስፈፃሚ በማምጣት የማርኬቲንግ ስራዎችን ለመስራት እንዳሰበ ለማወቅ ተችሏል።
ቀደም ተብሎ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ላይ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ፕሬዚዳንት እንዲሆን ግብዣ ቀርቦለት ሳይቀበለው እንደቀረም ከታማኝ ምንጭ ለመረዳት ተችሏል።
በቀጣይ ተመራጮችን በባላገሩ ሜዳ ፕሮግራም ላይ ይዘን እንቀርባለን።
Via:- ባላገሩ ስፖርት
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ የፕሬዝዳንትና ስራ አስፈፃሚ ምርጫ አካሂዷል።
ኢ/ር ሃይለእየሱስ ፍስሀ የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ሆነው ሲመረጡ፤ አርቲስት ማስተዋል ወንደሰን የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመርጣለች።
ፌዴሬሽን አመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በጊዮን ሆቴል ሲያካሂድ ለቀጣይ አራት አመታት የሚመሩትን ፕሬዝዳንትና ስራ አስፈፃሚዎችንም መርጧል።
አንጋፋዋ አርቲስት ሀረገወይን አሰፋ ፣አቶ ሲሳይ ዳኜ ፣ደ/ር ወገኔ ዋልተንጉስ ፣አቶ ኢሳያስ ታፈሰ ፣አቶ ሸሀመለ በቀለ፣አቶ በለጠ ወልዴ፣ ወ/ሮ አሰፋሽን ስራ አስፈፃሚ ውስጥ ተካተዋል።
ፌዴሬሽኑ አለብኝ የሚለውን የገንዘብ እጥረት ለመቅረፍ አርቲስቶችን ወደ ስራ አስፈፃሚ በማምጣት የማርኬቲንግ ስራዎችን ለመስራት እንዳሰበ ለማወቅ ተችሏል።
ቀደም ተብሎ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ላይ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ፕሬዚዳንት እንዲሆን ግብዣ ቀርቦለት ሳይቀበለው እንደቀረም ከታማኝ ምንጭ ለመረዳት ተችሏል።
በቀጣይ ተመራጮችን በባላገሩ ሜዳ ፕሮግራም ላይ ይዘን እንቀርባለን።
Via:- ባላገሩ ስፖርት
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1